በአማራ ክልል በተፈጠረው የሰላም እጦት ምክንያት የወረርሽኝ በሽታዎች እየተስፋፉ ነው ተባለ
ረቡዕ ጥቅምት 06 ቀን 2017 (አዲስ ማለዳ) በአማራ ክልል በተፈጠረው የጸጥታ ችግር ምክንያት “ቀደም ሲል በቁጥጥር ስር ውለው የነበሩ የጤና ችግሮች በወረርሽኝ መልክ እየመጡ ነው” ተባለ
ይህ የተገለጸው በአማራ ክልል የሚገኙ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፎረም ባዘጋጀው ውይይት ወቅት ነው።
መንገዶች ይዘጋሉ፣ ወገኖች ያለ ስጋት ወደ ጤና ተቋማት ሄደው መታከም አይችሉም ተብሏል፤ የታጠቁ ወገኖችን የጤና አገልግሎቱን የሚጠብቁ ሕጎችን እንዲያከብሩ ተጠይቋል፡፡
ታመው መታከም የማይችሉ ወገኖች በርካቶች ናቸው፤ ስለ ምን ካሉ ሕሙማን በነጻነት ወደ ሕክምና ቦታ መሄድ አይችሉም፣ የጤና ባለሙያዎችም በነጻነት ሕክምና አይሰጡምና ነው ማለታቸውም ተካቷል።
አሁን ባለው ችግር የጤና አገልግሎት ለመስጠት አስቸጋሪ መኾኑንም ተመላክቷል፡፡
ረቡዕ ጥቅምት 06 ቀን 2017 (አዲስ ማለዳ) በአማራ ክልል በተፈጠረው የጸጥታ ችግር ምክንያት “ቀደም ሲል በቁጥጥር ስር ውለው የነበሩ የጤና ችግሮች በወረርሽኝ መልክ እየመጡ ነው” ተባለ
ይህ የተገለጸው በአማራ ክልል የሚገኙ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፎረም ባዘጋጀው ውይይት ወቅት ነው።
መንገዶች ይዘጋሉ፣ ወገኖች ያለ ስጋት ወደ ጤና ተቋማት ሄደው መታከም አይችሉም ተብሏል፤ የታጠቁ ወገኖችን የጤና አገልግሎቱን የሚጠብቁ ሕጎችን እንዲያከብሩ ተጠይቋል፡፡
ታመው መታከም የማይችሉ ወገኖች በርካቶች ናቸው፤ ስለ ምን ካሉ ሕሙማን በነጻነት ወደ ሕክምና ቦታ መሄድ አይችሉም፣ የጤና ባለሙያዎችም በነጻነት ሕክምና አይሰጡምና ነው ማለታቸውም ተካቷል።
አሁን ባለው ችግር የጤና አገልግሎት ለመስጠት አስቸጋሪ መኾኑንም ተመላክቷል፡፡