በሶማሊላንድ ፕሬዜዳንታዊ ምርጫ ሙሴ ቢሂ በሰፊ ልዩነት ተሸነፉ
ማክሰኞ ህዳር 10 ቀን 2017 (አዲስ ማለዳ) በሶማሊላንድ በፕሬዜዳንታዊ ምርጫ ሙሴ ቢሂ በሰፊ ልዩነት ሲሸነፉ አብዲራህማን ሞሐመድ አብዱላሂ " ኢሮ " አሸነፈዋል።
የዋደኒ ፓርቲ እጩ ሆነው የቀረቡት አብዲራህማን ኢሮ ባለፈው ሳምንት የተካሄደውን የሶማሌላንድ ፕሬዜዳንታዊ ምርጫ እንዳሸነፉ የምርጫ ኮሚሽኑ ዛሬ አሳውቋል።
በምርጫው ፕሬዜዳንት ሙሴ ቢሂ አብዲ እንዲሁም ፋይሰል አሊ ዋርቤ ተሳታፊ የነበሩ ቢሆንም ድል ሳይቀናቸው ቀርቷል።
የኢሮ ፓርቲ ምርጫውን 63.92 በመቶ ድምፅ በማግኘት ነው ያሸነፈው። የተሰናባቹ ፕሬዜዳንት ሙሴ ቢሂ ፤ ኩልሚዬ ፓርቲ 34.81% ነው ያገኘው።
ሶማሌላንድ ከሶማሊያ ተገንጥላ እራሷን እንደ ነጻ ሀገር የምትቆጥር ስትሆን ላለፉት በርካታ አመታት ከሶማሊያ ፌዴራል መንግሥት ጋር ምንም አይነት ግንኙነት የላትም።
ማክሰኞ ህዳር 10 ቀን 2017 (አዲስ ማለዳ) በሶማሊላንድ በፕሬዜዳንታዊ ምርጫ ሙሴ ቢሂ በሰፊ ልዩነት ሲሸነፉ አብዲራህማን ሞሐመድ አብዱላሂ " ኢሮ " አሸነፈዋል።
የዋደኒ ፓርቲ እጩ ሆነው የቀረቡት አብዲራህማን ኢሮ ባለፈው ሳምንት የተካሄደውን የሶማሌላንድ ፕሬዜዳንታዊ ምርጫ እንዳሸነፉ የምርጫ ኮሚሽኑ ዛሬ አሳውቋል።
በምርጫው ፕሬዜዳንት ሙሴ ቢሂ አብዲ እንዲሁም ፋይሰል አሊ ዋርቤ ተሳታፊ የነበሩ ቢሆንም ድል ሳይቀናቸው ቀርቷል።
የኢሮ ፓርቲ ምርጫውን 63.92 በመቶ ድምፅ በማግኘት ነው ያሸነፈው። የተሰናባቹ ፕሬዜዳንት ሙሴ ቢሂ ፤ ኩልሚዬ ፓርቲ 34.81% ነው ያገኘው።
ሶማሌላንድ ከሶማሊያ ተገንጥላ እራሷን እንደ ነጻ ሀገር የምትቆጥር ስትሆን ላለፉት በርካታ አመታት ከሶማሊያ ፌዴራል መንግሥት ጋር ምንም አይነት ግንኙነት የላትም።