አልፊቅሁል ኢስላሚያህ[الفقه الإسلامية]


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: not specified


ይህ ቻናል በኡስታዝ ሸምሱ ነስሮ (አቡ ኢብራሂም) ፊቅሂ ነክ ትምህርቶች የሚለቀቁበት ነው።

Related channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
not specified
Statistics
Posts filter


✔️  ዘካተል_ፊጥር
                          زكاة الفطر

                 ክፍል _አንድ
  የዘካተል_ፊጥር ግዴታነት(ዋጅብነት)

  ⬅️ زكاة الفطر فرض بالسنة والإجماع

《ዘካተል ፊጥር: በቀደምት ሙስሊም ሙሁራን  ግዴታ መሆኑ በሙሉ ድምፅ ስምምነት ላይ ተደርሶበታል(ኢጅማዕ ተደርጎበታል።》

⬅️ قال العراقي رحمه الله  فيه وجب ركاة الفطر وهو مجمع عليه إليه إلا ممن شذ

➡️ አልዒራቂይ አላህ ይዘንላቸውና 《ዘካተል ፊጥር ግዴታ(ዋጅብ) በመሆኑ ላይቀደምት ሙስሊም ሊቃውንቶች በአንድ ድምፅ ተስማምተውበታል(ኢጅማዕ ተደርጎበታል።)

⬅️ قال إبن المنذر أجمع عوام أهل العلم. على ذلك

ኢብኑል ሙንዚር አላህ ይዘንላቸውና ዘካተል ፊጥር ግዴታ(ዋጅብ) ለመሆኑ አጠቃላይ ሙስሊም ሊቃውንቶች ተስማምተውበታል(ኢጅማዕ አድርገውበታል)

⬅️ قال إسحاق إبن راهويه هو كالإجماع من أهل العلم.

ኢስሐቅ  ኢብኑ ራወይህ አላህ  ይዘንላቸውና
《የዘካተል ፊጥር ግዴታነት አንደ አጠቃላይ የሙስሊም ሊቃውንቶች ስምምነት(እንደ ኢጀማዕ) የሚቆጠር ያህል ነው።》ብለዋል።

⬅️ قال الخطابي رحمه الله قال به عامة أهل العلم

《ኸጣቢይ አላህ ይዘንላቸውናየዘካተል ፊጥር ግዴታነት(ዋጅብነት) የአጠቃላይ የሙስሊም ሊቃውንት ስምምነት(ኢጅማዕ) ነው።》ብለዋል።

📚የሸኽ ዐብድል ዐዚዝ አረይስ የቴሌግራም ቻናል

✍ አቡ ኢብራሂም

ሚያዚያ 07/08/2015ዓ ል
ረመዷን 24/09/1444 ዓ ሂ

https://telegram.me/alfikhul_islamiyah


✔️ ኢዕቲካፍ(إلإعتكاف)

እውን ከሶስቱ(ከ3ቱ) መስጂዶች(ከመስጂደል ሐረም መካ፣ ከመስጂደ ነበዊ መዲና እና ከአቅሷ ቁድስ ፍልስጤን) ውጪ ኢዕቲካፍ ተደንግጓልን????

⬅️《وَلا تُباشِروهُنَّ وَأَنتُم عاكِفونَ فِي المَساجِدِ تِلكَ حُدودُ اللَّهِ فَلا تَقرَبوها كَذلِكَ يُبَيِّنُ اللَّهُ آياتِهِ لِلنّاسِ لَعَلَّهُم يَتَّقونَ》
📚سورة البقرة(187)
↪️《መስጂዶች ውስጥ ኢዕቲካፍ ተቀምጣችሁ ባለቹበት ለሚስቶቻቹህ ተቃራኒ ፆታዊ እንክብካቤ አታድርጉላቸው ይህ የአላህ የክልክልነት ወሰን ነውና እንዳትዳፈሩት(እንዳትሻገሩ)።
አላህ አንቀፆችን በዚህ መልኩ የሚያብራራላቹህ እንዲትጠነቀቁት(እንድትፈሩት) ነው።》
📚ሱረቱል በቀራ(187)
⬅️عن حذيفة رضي الله عنه
↪️ሁዘይፋህ ኢብኑል የማኒ አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና
⬅️قال رسول الله ﷺ:
↪️ነብዩ ﷺ ………
⬅️《"لا اعتكاف إلا في المساجد الثلاثة . المسجد الحرام, والمسجد النبوي, والمسجد الأقصى, 》
↪️ከሶስቱ መስጂዶች ማለትም መካ ከሚገኘው ከመስጂደል ሀረም፣መዲና ከሚገኘው ከመስጂደነበዊይ እና ፍልስጤን ከሚገኘው ከመስጂድል አቅሷ ውጪ ኢዕቲካፍ የለም።》ብለዋል።
📚أخرجه الطحاوي والإسماعيلي والبيهقي بإسناد صحيح عن حذيفة ابن اليمان رضي الله عنه، وهو
مخرج في "الصحيحة" رقم ٢٧٨٦،
📚ይህን ሀዲስ ኢማሙል በይሀቂይ  በጠንካራ(በሰሒሕ) ደረጃ ሲዘግቡት፣
📚ኢማሙ ጣሃዊያህ እና ኢስማዒሊይ በጠንካራ(በሰሒሕ) ደረጃ ዘግበውታል።
⬅️مع الآثار الموافقة له مما ذكرنا أعلاه، وكلها صحيحة
↪️ሌሎችም የዚህን ሀዲስ ትክክለኝነት የሚደግፉ የቀደምቶች(የሰለፎች) ገለፃና ጥቆማ ያለ ሲሆን
📚 السلسة الصحيحة ٢٧٨٦.
📚ኢማሙ አልባኒ ይህን ሀዲስ ሲልሲለቱ አሰሒሐህ ሐዲስ ቁጥር(2786) ላይ
ጠንካራ(ሰሒሕ) ሐዲስ ነው ብሎታል።
⬅️ قال العلامة الإمام الألباني -رحمه الله-:
↪️ኢማሙ አልባኒይ አላህ ይዘንላቸውና ከዚህ ሐዲስ በመነሳት…
⬅️المساجد التي يُعْتَكَفَ فيها
➡️ኢዕቲካፍ ስለሚቻልባቸው(ስለተደነገገባቸው) መስጂዶች ሲያብራሩ…

⬅️وقفت على حديث صحيح صريح يخصص "المساجد" المذكورة في الآية -«ولا تباشروهن وأنتم عاكفون في المساجد»-(١) بالمساجد الثلاثة: المسجد الحرام, والمسجد النبوي, والمسجد الأقصى, وهو قوله ﷺ:
"لا اعتكاف إلا في المساجد الثلاثة"(٢)
➡️《ቁርአን ላይ መስጂዶች በሚል የመጣው ኢቲካፍ የሚቻልባቸው መስጂዶች በዚህ የነብዩ ﷺ ጠንካራ(ሰሂህ) ሀዲስ ሚተሮገም በመሆኑ ኢዕቲካፍ የተደነገገላቸው መስጂዶች ሶስቱ መስጂዶች ማለትም መካ የሚገኘው ካዕባህ የሚገኝበት መስጂልሀረም፣መዲና የሚገኘው የነብዩ ﷺ መስጂድ)መስጂዱ ነበዊይ እና ፍልጤን ቁድስ ከተማ የሚገኘው መስጂደል አቅሷ ብቻ ናቸው።》

⬅️وقد قال به من السلف فيما اطلعت حذيفة بن اليمان, وسعيد بن المسيب, وعطاء, إلا أنه لم يذكر المسجد الأقصى,
➡️ይህንን ኢዕቲካፍ በሶስቱ መስጂዶች ብቻ የተደነገገ መሆኑንና ከሶስቱ መስጂዶች ውጪ የሌለ መሆኑን  ከቀደምቶች(ከሰለፎች) ሰዒድ ኢብኑ ሙሰየብ ፣ ዓጣእ እና ሌሎችም የተቀበሉት ሲሆን
➡️ከዚህ ዘመን ሙስሊም ሙሁራን ደግሞ አቡ ኡሳማህ ሰሊም ዒዲኒል ሒላሊይ ይገኙበታል።

⬅️وقال غيرهم بالمسجد الجامع مطلقا, وخالف آخرون فقالوا: ولو في مسجد بيته.
➡️《ሌሎች ይህን ሀዲስ ባለመቀበል በማንኛውም ጀማዕ በሚሰገድበት መስጂድ ውስጥ ኢዕቲካፍ ይቻላል ያሉ ሲሆን ሌሎች ደግሞ ቤታችን ውስጣ ባለች መስጂድ(መስገጂያ ስፍራ(ሙሰላ) ውስጥ እንኳን ይቻላል።》 ብለዋል።

⬅️《ولا يخفى أن الأخذ بما وافق الحديث منها هو الذي ينبغي المصير إليه, والله سبحانه وتعالى أعلم.》

➡️በመሆኑም ይላሉ  ሸይኽ አልባኒ ➡️《ከነብዩ ﷺ ሒዲስ ጋር የሚስማማው አባባል ኢዕቲካፍ በሶስቱ መስጂዶች ማለትም በመስጂደል ሀረም፣በመስጂደ ነበዊይ እና በመስጂደል አቅሷ ብቻ የተደነገገ መሆኑ ስለሆን ራስን በነብዩ ﷺ ሀዲስ ላይ መግታት ተገቢ ነው።》ብለዋል።

⬅️《من رأى أنه لااعتكاف إلا في ثلاثة مساجد :
عن عبد الرزاق عن الثوري عن واصل الأحدب عن إبراهيم قال جاء حذيفة إلى عبد الله فقال الا أعجبك من ناس عكوف بين دارك ودار الأشعري قال عبد الله فلعلهم أصابوا وأخطأت فقال حذيفة ما أبالي أفيه أعتكف أو في بيوتكم هذه إنما الاعتكاف في هذه المساجد الثلاثة مسجد الحرام ومسجد المدينة والمسجد الأقصى وكان الذين اعتكفوا فعاب عليهم حذيفة في مسجد الكوفة الأكبر》
➡️ሁዘይፈተል የማኒ አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና ዐብደላህ ኢብኑ መስዑድ ዘንድ በመምጣ
➡️《በአንተና በአቡል ሀሰነል አሽዓሪይ መስጂዶች ውስጥ ኢዕቲካፍ የገቡ ሰዎችን እንዴት ዝም ትላለህ ነብዩ ﷺ ከሶስቱ መስጂዶች ከመስጂደልሀረም፣ከመስጂነበዊይ እና ከመስጂደልአቅሷ ውጪ ኢዕቲካፍ የለም እንዳሉ እያወክ ሲለው ዓብደላ ኢብኑ መስዑድም አንተ ዘንግተህ እነሱ ደግሞ አስታውሰው ከሆነስ በማለት መልሶለታል።》
➡️ሌላው መታወቅ ያለበት ነገር ነብዩ ﷺ ከመስጂደነበዊይ(ከመዲና መስጂድ) ውጪ ኢዕቲካፍ አልገቡም ነበር።
📚 من سلسلة الهدى والنور
📚ምንጭ:
📚ሲልሲለቱልሁዳ ወኑር

📚للعلامة المحدث الشيخ الألباني -رحمه الله-
سئل عن الاعتكاف وأين يكون؟
الصوتية على الرابط:
👉ለበለጠ መረጃ ሼኽ አልባኒ ኢዕቲካፍ የት የት መስጂድ መግባት እንደሚቻል የገለፁበትን ድምፅ ቀጥሎ አለሎትና ያድምጡ

✍አቡ ኢብራሂም

ሚያዚያ 03/08/2015 ዓ ው
ረመዷን 20/09/1444 ዓ ሂ

http://telegram.me/abuibrahim0102030405
📚http://www.alalbany.net/alalbany/audio/484/484_04.mp3


✔️   ረመዷንና የፆም ህግጋት

                   ክፍል_ ሁለት

          የፍጡር(ማፍጠሪያ)ወቅት
                         እና
            ሲፈጠር የሚባል ዚክር

⬅️《 ثم أتموا الصيام إلى الليل》
📚 سورة البقرة(187)
↪️ አምላካችን አላህ ሱረቱል በቀራ ቁጥር 187 ላይ(ፆምን እስከምሽት ድረስ በመፆም አሙሉ።》 ብሎናል።

➡️ በዚህ የቁርአን አንቀፅ ውስጥ ምሽት በሚል የተገለፀው ትክከለኛ ወቅት በሚቀጥለው ትክክለኛ(ሰሒህ) ሐዲስ ተብራርቷል።

⬅️ وعن عمر بن الخطاب رضي الله عنه قال قال رسول الله ﷺ 《إذا أقبل الليل من ها  هنا، وأدبر النهار من ها هناوغربت الشمس فقد أفطر الصائم》
📚 متفق عليه
↪️ዑመር ኢብኑል ኸጣብ አላህ መልካም ስራውን ይውደድለትና በዘገበው ሐዲስ ነብዩﷺ《ምሽቱ ከዚህ በኩል ሲመጣ፣ ከዚህ በኩል  ደግሞ ቀኑ ሲሄድና ፀሐይ ስትጠልቅ ፆመኛ ያፍጥር።》ብለዋል
ስለዚህ ትክከለኛው የፉጥር ወቅት ፀሐይ እንደጠለቀች ነው።

➡️ ስለሆነም ፆመኞች ልብ ልንለው የሚገባው ነገር ፀሐይ ከመጥለቋ በፊት መብላት፣ መጠጣትና ወሲባዊ ግንኙነት መፈፀም ፆምን ሚያበላሽ መሆኑንና ፀሐይ ከጠለቀች በኀላ በቶሎ አለማፍጠር የተጠላ ሲሆን ከዚህም ባለፈ ክልክል(ሐራም) ይሆናል።

⬅️ وعن ابن عمر رضي الله عنه قال كان رسول الله ﷺ  إذا أفطر قال《ذهب الظمأ وابتلت العروق وثبت الأجر إن شاء الله》
📚 أخرجه أبو داود في سننه برقم (2357). وصححه الألباني رحمه الله

➡️ፆመኞች ሲያፈጥሩ ሊሉት(ሊያነቡት) የሚገባ ዚክር የተደነገገ ሲሆን ከመጡት ዚክሮች ውስጥ ትክክለኝነቱ በሐዲስ ሊቃውንት የታመነበት ይህ ከላይ የተጠቀሰው ሲሆን ንባቡም
↪️《ዘሀበ_ዘማኡ, ወብተለቲል_ዑሩቁ ወሰበተል_አጅሩ ኢንሻአላህ።》

ትርጉሙም:
↪️《ጥማቱም ተወገድ፣ጉሮሮዎችም(የደም ስሮችም) ረጠቡ  በአላህ መልካም ፍቃድ ምንዳውም ተረጋገጠ?》ማለት ነው።
📚ይህን ሐዲስ አቡዳውድ በሱነናቸው ቀጥር(2357) ላይ ሲዘግቡት ኢማሙ 📚አልባኒይ ትክክለኛ(ሰሒህ) ሐዲስ ነው ብለውታል።

ይህንንም ሐዲስ ራሱ ደካማ ነው ያሉ የሐዲስ ሊቃውንተ  አልጠፉም።

✍ አቡ ኢብራሂም

መጋቢት  16/07/2015ዓ ል
ረመዷን 02/09/1444ዓ ሂ

https://telegram.me/alfikhul_islamiyah


✔️ ረመዷን እና የፆም ህግጋት

                   ክፍል_ አንድ

     የሱሑር ማብቂያና ፆም የመጀመሪያ
                  ትክክለኛው ሰዓት

⬅️《وكلوا واشربوا حتى يتبين لكم الخيط الأبيض من الخيط الأسود من الفجر 》
📚 سورة البقرة(187)
↪️ አምላካችን አላህ 《በረመዷን ለሊት ነጭ ክር ከጥቁር ክር እስከሚለይ ድረስ ንጋጋት(የሱብሒ ወቅት) እስኪረጋገጥ ድረስ ብሉም ጠጡም።》
📚ሱረቱል በቀራ(187)

⬅️ وعن عائشة رضي الله عنها أن بلال رضي الله عنه كان يؤذن بليل،فقال رسول الله ﷺ 《 كلوا واشربوا حتى يؤذن ابن أم مكتوم، فإنه لا يؤذن حتى يطلع الفجر》
📚متفق عليه
↪️ ዓኢሻ አላህ መልካም ስራዋን ይውደድላትና ነብዩﷺ《ቢላል ገና ሳይነጋ በለሊት ነው አዛን የሚለው ስለዚህ ኢብኑ ኡሚ መኽቱም አዛን እስከሚል ድረስ ብሉም ጠጡም
እሱ ፈጅር(ንጋት) እስከሚገባ ድረስ አዛን አይልምና።》ብለዋል።

⬅️ وعن أبي هريرة رضي الله عنه قال قال رسول الله ﷺ:《إذا سمع أحدكم النداء والإناء على يده فلا يضعه حتى يقضي حاجته منه》
📚أخرجه أبو داود برقم(2350)
📚وصححه الأللاني رحمه الله
↪️ አቡ ሁረይራህ (ረዲየላሁ ዐንሁ)《አንድ ሰው ሱሁር እየበላ የሱብሒ አዛን ቢባልበት በእጁ  ያለውን የምግብ እቃ ሳያስቀምጥ መብላት ያለበትን ይብላ።》ብለዋል።
📚ኢማሙል አልባኒይ ትክክለኛ(ሰሒሕ) ሐዲስ ነው ብሎታል።

➡️ ይህን ሐዲስ ከላይ ከተጠቀሰው ሐዲስና የቁርአን አንቀፅ ጋር በጥምረት ሲተረጎም
አንድ ሰው ሱሁር እየበላ አዛን ከተባለበት አዛኑ የተባለው ፈጅር ሳይገባ ከሆነ ተመጋቢው መመገቡን ሳያቋርጥ መብላት ያለበትን ያህል መብላት ይችላል።

➡️ ይሁንና አዛን የተባለው ፈጅር ከገባ በኋላ(ፈጅር ላይ) ከሆነ ተመጋቢው በቀጥታ መመገቡን ቀጥ አድርጎ ማቆም አለበት።
ምክንያቱም ቁርአን ውስጥ 《ብሉም ጠጡም የተባልነው ፈጅር መግባቱን እስከምናረጋግጥ ብቻ ነውና።

➡️ ስናጠቃልል ሱሁር መብላት የሚቻለው ፈጅር(ፈጅረሳዲቅ)(እውነተኛው ንጋጋት)(የሱብሒ ሰላት ወቅት) እስኪገባ ድረስ ነው።

👌ልብ እንበል ፈጅር ከገባ በኋላ ጥቂትም ቢሆን ሱሁር መብላት አይቻልም።

👌አንድ ሰው ፈጅር ከገባ በኋላ ከበላ ወይም ከጠጣ የዛን ቀን ፆም የለውምና የዛን ቀን ፆም ምትክ በሌላ ቀን መክፈል(ቀዷ ማውጣት) አለበት።

✍ አቡ ኢብራሂም

መጋቢት 14/07/2015ዓ ል
ረመዷን 01/09/1444 ዓ ሂ

https://telegram.me/alfikhul_islamiyah


✔️ የረመዳን አቀባበል

➡️ ከረመዳን አቀባበል አኳያ ሰዎች በሁለት ይከፈላሉ ።

⬅️قسام الناس في إستقبال شهر رمضان
⬅️قال الشيخ سليمان الرحيلي حفظه الله:
➡️ሸይኽ ሱለይማ አሩሀይሊይ አላህ ይጠብቃቸውና…
https://b.top4top.net/m_12102u71p1.mp3
⬅️والناس في استقباله أقسام:
➡️《ሰዎች ለረመዳን ካላቸው ጉጉትና አቀባበል እንዲሁም አጠቃቀም አንፃር በሁለት ይከፈላሉ።》

⬅️فهل أنت من القسم الفَرِح بحضوره، لأنّه يزداد به قُربًا وزُلفى إلى ربّه -جل وعلا-؟
➡️《ለመሆኑ አንተ(ቺ) ከሁለቱ ከየተኞቹ ነህ(ሽ)??!!!!!!!!!!!
➡️《የረመዳን ወር በመምጣቱ እጅግ ተደስተው ከሚቀበሉትና በተገቢ መንገድ ሊጠቀሙበት ቀድመው በቂ ዝግጅት ከሚያደርጉት???  ውይስ……???》
⬅️《 وهذا شأن المؤمنين،……》
➡️《የአማኞች(የሙእሚኖች) ባህሪ የምንዳ መሸመቺያ፣ወንጀልን ማስማሪያና ወደ ፈጣሪያቸው አላህ መቃረቢያ የሆነ የዒባዳ አይነት፣ወቅትና ቦታ የማግኘቱ እድል ባጋጠማቸው አጋጣሚ ሁሉ እጅጉን ተደስተው በእድሉ ለመጠቀም ደፋ ቀና ማለታቸው ነው።》

⬅️،{ يَا أَيُّهَا النَّاسُ قَدْ جَاءَتْكُم مَّوْعِظَةٌ مِّن رَّبِّكُمْ وَشِفَاءٌ لِّمَا فِي الصُّدُورِ وَهُدًى وَرَحْمَةٌ لِّلْمُؤْمِنِينَ (57) قُلْ بِفَضْلِ اللَّهِ وَبِرَحْمَتِهِ فَبِذَٰلِكَ فَلْيَفْرَحُوا هُوَ خَيْرٌ مِّمَّا يَجْمَعُون
📚َ (58)}[يونس58-57].
➡️ልቅናው እጅጉን የላቀው አላህ ይህንን በተመለከተ……
➡️《እናንተ የሰው ልጆች ሆይ አዕምሮ ውስጥ ላለ የተሳሳተ አመለካከት ፍቱን መፍትሄ የሆነ፣ለአማኞች(ለሙእሚኖች) መመሪያና እዝነት የሆነ መመከሪያ(መገፀጪያ) መፅሐፍ(ቁርአን) መቶላቹሀል።》
በመሆኑም በአላህ ችሮታ(ተጨማሪ ስጦታ) ማለትም በቁርአን እና በእዝነቱ(በነብዩ ﷺ መላክ) አማኞች(ሙእሚኖች) ይደሰቱ(ሊደሰቱ ይገባል)።》ይለናል።
📚ሱረቱ ዩኑስ(57_58)

⬅️《وعلى رأس هؤلاء حبيبنا ورسولنا صلى الله عليه وسلم ، يقول ابن عباس رضي الله عنه  : كان رسول الله صلى الله عليه وسلم أجود الناس، وكان أجود ما يكون في رمضان حين يلقاه جبريل في كل ليلة فيُدارسه القرآن.》
➡️《እውነት የነብዩ ﷺ ተከታዮች ከሆን…
ዓብደላህ ኢብኑ አባስ እንደዘገቡት(ነብዩ ﷺ በጣም ቸር የነበሩ ሲሆን በእጅጉ ቸርነታቸው የሚንረው ደግሞ የረመዳን ወር መግባትን ተከትሎ ነበር።》ብለዋል።

⬅️《وصِنفٌ -يا عباد الله- يفرح برمضان، لا للعبادة والقُرب من الرحمن، وإنما من أجل حلاوة
السّهَر في رمضان، ومن أجل العادات، ومن أجل المسلسلات وبرامج الفضائيّات، فتراه يسأل عند قدوم رمضان: ما هي المسلسلات التي ستُعرَض؟ وما هي المُسابَقات التي يُدعَى
الناس للمشاركة فيها؟ ونحو هذا، وهذا -يا عباد الله- دليل على ضعف الإيمان ومرض القلب.》
➡️《ሌለኞቹ ግን በረመዳን መምጣት አነሰም በዛም ተደሳቾች ሲሆኑ ነገር ግን የሚደሰቱት ረመዳ ይዞት የመጣውን ግዙፍ የምንዳ አይነት ጠንክሮ  ለመሸመት ሳይሆን በዘልማድ በረመዳን ወር ውስጥ የሚኖረውን የቤት ውስጥና የመስጂዶች ድምቀት፣የምግብ ዝግጅት፣በየቴሌቪዢን ስርጭቶች ረመዳንን የተመለከቱ ተከታታይ ድራማና የተለያዩ ውደድሮችን ለመከታተልና በዋዛ ግዜውን ላማባከን ሲሉ ነው።》

➡️ይህ በቀጥታ የኢማን ድክመት ምልክት ነውና
በፍጥነት ራሳችንን በማረም ከውዲሁ በራሳችን ላይ የእርምት እርምጃ በመውስድ የባህሪ ለውጥ በማምጣት ረመዳንን ለተደነገገለት አላማና ግብ ልናውለውና በአግባቡ ልንጠቀምበት ይገባል።》
📚المصدر
📚 للإستماع والتحميل على الرابط :

መጋቢት 12/07/2015ዓ ል
ሻዕባን 29/08/1444ዓ ሂ

✍ አቡ ኢብራሂም

https://telegram.me/alfikhul_islamiyah


✔️  ጂናየቱ ተመዩዕ
                جناية التميع على المنهاج السلفي
ጂናየቱት ተመዪዕ(ዲንን ማንኮታኮት) በሰለፊያህ ጎዳና  ላይ ያለው አደጋ!!!!!!!!!!

                      ክፍል  አምስት

⬅️ إن العالم  إذا اجتهد وأخطأ لا يكون خطؤه منهجا يجب سلوكه على الناس،هو مأجور على آجتهده هذا وسعه لا يكلف الله نفسا إلا وسعها لكن أن ينتهج خطؤه ويتخذ مسلكا ودينا فليس ذالك بسديد، بل ولا صواب ولا حق، فلخطأ خطأ.
↪️《አንድ ሙስሊም ሊቅ(የዲን ዓሊም) አንድ ዲናዊ ጭብጥን በጥልቀት መርምሮ ብይን ከሰጠና ብይኑ ስህተት ከሆነ ብይን ሰጪው ይመነዳበታል ምክንያቱም በአቅሙ ልክ መርምሯልና አላህም ከአቅም በላይ አያስገድድምና ይሁን እንጂ ብይኑን ተቀብሎ መስራትም ሆነ እንደትክክለኛ የዲን መንገድ አድርጎ መያዝ አይቻልም ለምን ቢባል ስህተት ስህተት እንጂ ትክክል ሊሆን ስለማይችል።》

✍ አቡ ኢብራሂም

ጥር 01/05/2015 ዓ ል
http://telegram.me/abuibrahim0102030405


👉ሀይድ(የወር አበባ) ላይ ያለች ሴት ቁርአን መንካትም ሆነ መቅራት ክልክል(ሐራም) ይሆንባታልን???????
በፍፁም ሐራም አይሆንባትም!!!!!!

አንድ ሙስሊም ሴት ሀይድ(የወር አበባ) ላይ ስትሆን ሐራም የሚሆኑባት ነገሮች አራት ነገሮ ብቻና ብቻ ናቸው !!!!!!!!!።

✔️ ሴት ልጅ ሀይድ(የወር አበባ) ላይ ሆና ቁርአን መንካትም ሆነ መቅራት ትችላለችን????

⬅️ الرَّاجِحُ فِي حُكْمِ قِرَاءَةِ الحَائِضِ لِلْقُرْآنِ مِنْ حِفْظِهَا وَمِنَ المُصْحَفِ
ሴት ልጅ ሀይድ(የወር አበባ) ላይ ሆና ቁርአን የመንካትም ሆነ የመቅራት ትክክለኛው ብይን!!!

⬅️ يجيبكَ الشَّــيخُ العلّامــة عــبيد الجَــابِري رحمه الله :
ሸይኽ ዑበይዲል ጃቢሪይ አላህ ይዘንላቸውና እንዲህ ብለው ፍንትው ያለ ብይን(ፈትዋ) ሰጥ ተዋል።
⬅️《 وها هنا مسألة هل يجوز للمسلمة أن تقرأ القرآن وهي حائض؟

👉 ሸይኽ ዑበይዲል ጃቢሪይ አላህ ይዘንላቸውና《ሴት ልጅ ሀይድ(የወር አበባ) ላይ ሆኗ ቁርአን በቃሏ መቅራት ትችላለችን? ቁርአንስ መንካት ትችላለችን?》ተብለው ተጠይቀው ሲመልሱ…

وها هنا يُفرَّق بين حالين:
⬅️ الأولى: إذا كانت عن ظهر قلب فهذه لا إشكال فيها إن شاء الله، وكذلك إذا كانت تقرأ القرآن من خلال كتاب تفسير مثل تفسير ابن كثير، تفسير ابن جرير، تفسير ابن أبي حاتم وغيرها،

1ኛ:ሀይድ ላይ ያለች ሴት ቁርአን ሳትይዝ በአዕምሮዋ(በቃሏ) መቅራቷና ከተፉሲርና ከሌሎች ኪታቦች ውስጥ ተፅፎ የሚገኝን የቁርአን አንቀፆችን ማንበቧ መቻሉ በፍፁም አጠያያቂ አይደለም። ስለዚህ ትችላለች።》

وإنما الخلاف الكبير إذا كانت تقرأ من المصحف، فمن أهل العلم من شدَّد في هذا، ومنعها إلا أن تكون بحائل –خِرقة- تجعلها على يدها أو القُفاز وهو الذي يسمِّيه العامة الجونتي – الظاهر أنها لفظة أعجمية- المعروف في لغة العرب وأهل الإسلام القفاز، ثم تفرَّعت عنها مسألة أُخرى قالوا لا تمسُّ الصفحات بل تقلبها بشيء مثل عود أو مرسام أو غير ذلك، وهذا في الحقيقة تَشديدٌ لا دليل عليه أبدًا،
《ሀይድ(የወር አበባ) ላይ ያለች ሴት ቁርአንን በጨርቅ ሸፍና ወይም ጓንት በእጇ አጥልቃ ወይም የቁርአኑን ገፆች በእንጨት እየገለፀች ካልሆነ በቀር ያለምንም መሸፈኛ በቀጥታ በእጇ መንካት አትችልም የሚል የጠነከረ አቋም ያላቸው ሙስሊም ሊቃውንት አሉ ይሁንና ይህ አለአግባብ ማክረር ነው።》

والصواب أنها تقرأ القرآن عن ظهر قلب أو من المصحف وتمسّه بيدها لأن النجاسة في مكان محدود وبقية جسمها طاهر، والله أعلم 》.
《ትክክሉና በማስረጃ የተደነገገው ግን ሀይድ(የወር አበባ) ላይ ያለች ሴት ልጅ ቁርአንን በቃልዋም መቅራት ትችላለች እንደዚሁም ቁርአንን(ሙስሐፍን) ያለምንም መሸፈኛ በቀጥታ በእጇ መንካትና መዳበስ ትችላለች።》

📚المَــصْدَرُ
[ اللقاء 25 من لقاءات الجمعة 8 جمادى الأولى 1436هـ
ሀሳቡን ስናጠቃልል
ሴት ልጅ ሀይድ(የወር አበባ) ላይ እያለች የማይፈቀዱላት(ሐራም የሚሆኑባት) ነገራት አራት ነገራት ብቻ እና ብቻ ናቸው።

1ኛ:ወሲባዊ ግንኙነት(ጂማዕ)

﴿وَيَسأَلونَكَ عَنِ المَحيضِ قُل هُوَ أَذًى فَاعتَزِلُوا النِّساءَ فِي المَحيضِ وَلا تَقرَبوهُنَّ حَتّى يَطهُرنَ فَإِذا تَطَهَّرنَ فَأتوهُنَّ مِن حَيثُ أَمَرَكُمُ اللَّهُ إِنَّ اللَّهَ يُحِبُّ التَّوّابينَ وَيُحِبُّ المُتَطَهِّرينَ﴾
سورة البقرى(222)
《ስለ ሀይድ(የወር አበባ) ይጠይቁሀል እሱ(የሀይድ) ደም ነጃሳ ነውና ወንዶች በሀይድ ወቅት ሴቶችንእንዳይቀርቧቸው(ጂማዕ(ወሲባዊ )ግንኙነት) እንዳያደርጓቸው።》
ሱረቱል በቀራ (222)

2ኛ:መስገድ 3ኛ:መፆምና

- وعن أبي سعيدٍ الخدري  قال: قال رسولُ الله ﷺ: أليس إذا حاضَتِ المرأةُ لم تُصَلِّ ولم تَصُمْ؟. متَّفقٌ عليه
አቢ ሰዒዲንል ኹድሪይ በዘገቡት ሐዲስ ነብዩ 《 ሴት ልጅ ሀይድ ላይ ከሆነች አትሰግድምም አትፆምም አይደም እንዴ?》ብለዋል
ኢማሙ ቡኻሪይ እና ሙስሊም ተስማምተውበታል።
ይህ ሀዲስ ተራ ቁጥር አንድና ሁለት ላይ ለተጠቀሱት ብይኖች ማስረጃ ነው።

4ኛ:ካዕባን መጠወፍ ናቸው።
عن عائشة رضي الله عنها قالت: لَمَّا جِئنا سَرِفَ حِضْتُ، فقال النبي صلى الله عليه وسلم: ((افعَلي ما يفعَلُ الحاجُّ، غير ألَّا تطوفي بالبيتِ حتى تطهُرِي))؛ متفق عليه
《እናታችን አዒሻህ አላህ ስራዋን ይውደድላትና ሀጀተል ወዳዕ(የመሰናበቻው ሐጅ ላይ ሰሪፍ ሚባል ቦታ ስደርስ ሀይዴ መጣ ያኔ ነብዩ《ካዕባን እንዳትጠውፊ እንጂ ሀጃጆች የሚተገብሩትን ዒባዳህ በሙሉ ተግብሪ ብለዋታል።》

👉 ሀይድ ላይ ያለች ሴት ዒባዳህ ክልክል ቢሆንባት ኖሮ ነብዩ ካዕባን ከመጠውፍ ውጭ ያለውን የሐጅ ተግባር ተግብሪ ባላሏት ነበር።

✍ አቡ ኢብራሂም

የካቲት 09//06/2015ዓ ል

https://telegram.me/alfikhul_islamiyah


Video is unavailable for watching
Show in Telegram


✔️ ✔️ ሱናህ
                             السنة      

⬅️ جاء رجل  للصحابي الجليل عبد الله ابن عباس رضي الله عنه وقال《 أوصني قال عليك بتقوى الله والإستقامة إتبع ولا تبتدع》📚 شرح السنة(214)

《 አንድ ሰው ወደ ታላቁ ሶሐባ ወደ ዓብደላህ ኢብኑ ዓባስ መጥቶ ምከሩኝ ሲላቸው እሳቸውም: አላህን በመፍራት እና በዲን ላይ በመፅና አደራህን በኢስላም ውስጥ የተደነገገውን ተከተል እንጂ ያልተደነገገን አዲስ እንግዳ መጤን ነገር ከመተግበር ተጠንቀቅ።》 ብለውታል።

📚ሸርሑ ሱና(214)

✍ አቡ ኢብራሂም

ጥቅምት 13/02/2015 ዓ ል

http://telegram.me/abuibrahim0102030405


✔️ ኢርሻዱል በሪያህ

إرشاد البرية إلى شرعية الإنتساب للسلفية ودحض الشبه البدعية》
《 ኢርሻዱል በሪያህ ኢላ ሸርዒየቲል ኢንቲሳቢ ሊሰለፊያ》
ክፍል ሰባት

መቅድም (المقدمة)

ولقد أحسن الإمام الأصبهان عند ما قال《 وكان السبب في إتفاق أهل الحديث أنهم أخذوا الدين من الكتاب والسنة وطريق النقل، فأورثهم الاتفاق والائتلاف،
ኢማሙ ሐሰነል በስሪይ አላህ ይዘንላቸውና 《 ሱኒዮች በትክክለኛው የዲን አስተምህሮት በሱና ላይ በአንድ ላይ ያለምንም መጣረስ የመጓዛቸው ምስጢር ዲናቸውን ከቁርአንና ከትክክለኛ(ሰሒህ) ሐዲስ በትክክለኛው ከሱና ሊቃውንት ቅብብሎሽ የያዙ መሆናቸው ሲሆን።

وأهل البدعة أخذو ا الدين من المعقولات والآراء فأورثهم الافتراق والاختلاف.》
إرشاد البرية إلى شرعية الانتساب إلى
📚السلفية(12_13)

የቢዳዓ አራማጆች ደግሞ በኢስላም ውስጥ በቁርአንና በትክክለኛ ሐዲስ ያልተደነገገን የስዎችንና የቡድኖችን አመለካከት በማራመዳቸው ምክንያት ይህ የተሳሳተ አካሄዳቸው መለያየትንና መከፋፈልን አውረሷቸዋል።》ብለዋል።

📚 ኢርሸዱል በሪያህ(12_13)

ግንቦት 26/09/2014 ዓ ል

ዙልቃዕዳ 03/11/1443 ዓ ል

✍ አቡ ኢብራሂም

http://telegram.me/abuibrahim0102030405


ኢርሻዱል በሪያህ

إرشاد البرية إلى شرعية الإنتساب للسلفية ودحض الشبه البدعية》
《 ኢርሻዱል በሪያህ ኢላ ሸርዒየቲል ኢንቲሳቢ ሊሰለፊያ》
ክፍል ስድስት

መቅድም (المقدمة)

قال أبو عبد السلام حسن بن قاسم الحسني الريمي السلفي في إرشاد البريته
አቡ ዓብድሰላም ሐሰን ቢን ቃሲም......

و هكذا قام بالدعوة من بعده صحابته الكرام رضوان الله عليهم
የትክክለኛው የኢስላም አስተምህሮት ሱና(ሰለፊያ) ከነብዩ ﷺ በወኋላ በተከበሩት በነብዩ ﷺ ሷሐቦች ሲተገበርና ሲሰበክ(ዳዕዋ) ሲደር የቆየ ሲሆን

ثم في عصرنا هذا من أمثال الشيخ ابن باز رحمه الله والشيخ ابن عثيمين، والشيخ الفوزان، والشيخ ربيع المدخلي، والشيخ، محمد أمان الجامي رحمه الله، والشيخ الألباني رحمه الله، والشيخ مقبل بن هادي الوادعي رحمه الله، والشيخ حمدي بن عبد المجيد السلفي، وغيرهم ممن ترسم خطاهم… كلهم يدعون إلى منهج واحد وعقيدة واحدة.
አሁን ላይ ደግሞ እንደ ሸይክ ኢብኑ ባዝ፣ኢብኑ ዑሰይሚን፣ሸይክ ፈውዛን ፣ሸይክ ረቢዕ አልመድኸሊይ፣ ሸይክ አልባኒ፣ሸይክ ሙቅቢል፣ ሸይኽ ሀምዲ ኢብኑ ዐብድል መጂድ እና ሌሎችም ወደ ተውሒድ መንገን በሚጣሩ ሱኒይ ኢማሞች የሚመራ ሚንሀጅ ነው።

ኢርሸዱል በሪያህ(12)

ግንቦት 23/09/2014 ዓ ል

ሸዋል 30/10/1443 ዓ ል

አቡ ኢብራሂም

http://telegram.me/abuibrahim0102030405


ሱና
السنة
قال عمر بن.عبد العزيز رحمه الله《 لا تكن ممن يتبع الحق إذا وافق هواه ويخالفه إذا خالف هواه》فتاوى بن تينية(480/10)

《ዑመር ኢብኑ ዐብድል ዐዚዝ አላህ ይዘንላቸውና
ሐቅን ሲመስለው(ከዝንባሌውና ከስሜቱ ጋር ሲገጥምለት) የሚቀበልና ሳይመስለው(ከዝንባሌውና ከስሜቱ ጋር ሳይገጥምለት ) ሲቀር ማይቀበል ሰው እንዳትሆን።》ብለዋል።

ኢብኑ ተይሚያህ(10/480)

ግንቦት 19/09/2014 ዓ ል

አቡ ኢብራሂም

http://telegram.me/abuibrahim0102030405


✔️ ሱና
✔️ السنة

⬅️ قال العلامة الشيخ ربيع هادي المدخلي حفظه الله
《فلا تتحقق السلفية والسنية حتى تفارق أهل البدع والتحزب قلبا وقالبا》
📚 مجموع الردود(276)

ሸይኽ ረቢዕል መድኸሊይ አላህ ይጠብቃቸውና 《 ከቢዳዓ አራማጆች እና ከሒዝቢዮች(ቡድንተኞች) ጋር በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ አንዳች ግንኙነት እስካለ ግዜ ድረስና ሱኒዮች(ሰለፊዮች) ነን የሚሉ ወገኖች ከቢዳዓ አራማጆች እና ከሒዝቢዮች(ከቡድንቶች) ጋር በሪኦተ አለማዊም(በአስተሳሰባዊም) ይሁን በተግባራዊ ነገሮች ላይ ሙሉ በሙሉ ያላቸውን ግንኙነት እስካላቋረጡ ድረስ ሱኒይነትና ሰለፊይነት በፍፁም ሊኖር አይችልም ከንቱ ምኞትም ብቻ ነው።

📚 መጅሙዕ አሩዱዱ(276)

ግንቦት 13/09/2014 ዓ ል

ሸዋል 21/10/1443 ዓ ሂ

✍ አቡ ኢብራሂም

http://telegram.me/abuibrahim0102030405


✔️ ኢርሻዱል በሪያህ

إرشاد البرية إلى شرعية الإنتساب للسلفية ودحض الشبه البدعية》
《 ኢርሻዱል በሪያህ ኢላ ሸርዒየቲል ኢንቲሳቢ ሊሰለፊያ》
ክፍል አምስት

መቅድም (المقدمة)

قال أبو عبد السلام حسن بن قاسم الحسني الريمي السلفي في إرشاد البريته
አቡ ዓብድሰላም ሐሰን ቢን ቃሲም......

و هكذا قام بالدعوة من بعده صحابته الكرام رضوان الله عليهم
የትክክለኛው የኢስላም አስተምህሮት ሱና(ሰለፊያ) ከነብዩ ﷺ በወኋላ በተከበሩት በነብዩ ﷺ ሷሐቦች ሲተገበርና ሲሰበክ(ዳዕዋ) ሲደር የቆየ ሲሆን

ثم تلاهم التابعون وأتباعهم من أمثالهم: الحسن البصري وسعيد بن المسيب وعروة بن الزبير، وعبد الله بن المبارك، ومالك بن أنس والليث بن سعد،
ታዓቢዮች ደግሞ የሷሐቦችን እግር ተክትለው ሱናን(ሰለፊያን) ተግብራው ሰብከዋል።

والشافعي، وأبي إسحاق الفزاري، ووكيع بن الجراح، وإسماعيل بن علية، والسفيانين، والأوزاعي، وأحمد بن حنبل، والبخاري، ومسلم، والترمذي وأبي داود، والنسائي، وبن ماجه، وبن تيمية، وبن القيم، وبن كثير، ومحمد بن عبد الوهاب، وأبنائه وأحفاده، والشوكاني

ታዓቢዮችን ተከትለው በየዘመኑ የነበሩ ታላላቅ ሙስሊም ሊቃውንትና የዲን መሪዎች እንደነ ኢማሙ ሻፊዒይ፣ አቡ ኢስሐቅ አልፈዛሪዩ፣ ወኪዕ ኢብኑል ጀራሕ፣ ኢስማዒል ኢብኑ ዑለያህ፣ ሁለቱ ሱፊያኖች፣ ኢማሙል አውዛዒይ፣ አህመድ ኢብኑ ሀንበል፣ ኢማሙል ቡኻሪይ፣ ሙስሊም፣ ቲርሚዚይ፣ አቡ ዳውድ፣ ነሰኢ፣ ኢብኑ ማጅህ፣ ኡብኑ ተይሚያህ፣ ኢብኑልቀይም፣ ሸይኽ ሙሀመድ ዐብዱልወሀብ፣ የእሳቸው ልጆችና የልጅ ልጆች ኢማሙ ኢማሙ ሸውካኒ በየዘመናቸው ሱናን ሲተገብሩ ፣ሲያስተገብሩና ሲያሰራጩ ኖረው ለተተኪያቸው ኦርጂናሊቲውን እንደጠበቀ አስተላልፈዋ።

📚 ኢርሸዱል በሪያህ(12)

ግንቦት 10/09/2014 ዓ ል

ሸዋል 17/10/1443 ዓ ል

✍ አቡ ኢብራሂም

http://telegram.me/abuibrahim0102030405




✔️ ሸዋል ፍች(ትንሿ ፍች) የሚባል በዓል በኢስላም አለን????

✔️ ሸዋል ፍች(ትንሿ ፍች) በኢስላም
(በቁርአንና በሐዲስ) እይታ

⬅️ فإن الله شرع للمسلمين عيدين عيد الفطر وعيد الأضحى.

《አላህ በኢስላም ውስጥ ሁለት አመታዊ በዓልንና አንድ ሳምንታዊ በዓልን ብቻ ነው የደነገገው። ለዚህም ማስረጃው…

⬅️ ودليل ذلك ما رواه أبو داود في سننه عن أنس رضي الله عنه قال قدم رسول الله صلى الله عليه وسلم المدينة ولهم يومان يلعبون فيهما فقال: "ما هذان اليومان؟ قالوا: كنا نلعب فيهما في الجاهلية فقال يا رسول إن الله قد أبدلكم بهما خيراً منهما يوم الأضحى ويوم الفطر "
رواه أبوا داود.

《ነብዩ ﷺ ወደ መዲና በተሰደዱበት ወቅት የመዲና ነዋሪዎች አደባባይ ወጥተው በመጨፈር የሚያከብሯቸው ሁለት አመታዊ በዓላት(ዒዶች) ነበሯቸው።
ነብዩﷺ እነዚህ ሁለት የምታከብሯቸው ቀናት ምንድናቸው ብለው ሲጠይቋቸው የመዲና ነዋሪዎችም ከድንቁርና(ከጃሂሊያ) ዘመን ጀምሮ እናከብራቸው ነበር አሏቸው ነብዩም ﷺ አላህ እነዚህን ሁለት አመት_በዓሎችን በተሻለ ሌላ ሁለት አመት_በዓላት(ኢዶች) ቀይሮላቹሀል እነሱም ዒደል ፊጥርና ዒደል አድሐ ናቸው። ብለዋቸዋል።》
አቡዳውድ ዘግበውታል።

➡️ ከዚህ የምንረዳው በኢስላም ውስጥ የተደነገጉ አመታዊ በዓላት ሁለት ብቻ እንደሆኑና እነሱም ዒደልፊጥርና ዒደል አድሐ ብቻ እንደሆኑ ነው።

➡️ ሳምንታዊው ዓመት_በዓል ደግሞ አንድ ብቻ ሲሆን እሱም የጁምዓ እለት ነው።

➡️ እውነታው ይህ ሆኖ ሳለ ህዝበ ሙስሊሙ ዘንድ ግን በቁርአንም ሆነ በትክክለኛ(በሰሒህ) ሐዲስ ያልተደነገጉ ኢ_ኢስላማዊ በዓላት ሲከበሩ ይስተዋላል።

➡️ ከእነዚህ በኢስላም ካልተደነገጉ በዓላት መካከል መውሊድ፣ሸዋል ፍችና ዐሹራ ናቸው።

➡️ እነዚህ ሶስቱ በዓላት መውሊድ፣ሸዋል ፍችና ዐሹራ በቁርአንና በትክክለኛ ሐዲስ(በሰሒህ) ያልተነገጉ ነገር ግን ሰዎች ስሜታቸውን በመከተል የፈበረኳቸው የአላህ ሳይሆኑ የሰዎች በዐላት ናቸው።

➡️ ይህ ማለት መውሊድ፣ዐሹራ እና ሸዋል ፍች ኢስላማዊ በዐላት ሳይሆኑ ኢ_ኢስላማዊ በዐላትና ኢስላም ውስጥ ከሚተገበሩ ከቢዳዓ ተግባራት ዋና ዋናዎቹ ናቸው።

➡️ እስኪ ነብዩ ﷺ ኹጥባ ሲያነቡ ሁሌም ሳያነቡ ማያልፏትን ዐረፍተ ነገርን እናስታውስ…

⬅️ وشر الامور محدثاتها وكل محدثة بدعة وكل بدعة ضلالة وكل ضلالة في النار》

《በዲን ውስጥ የነገራቶች ሁሉ መጥፎ(ሸር) ተግባር ማለት ከመሰረቱ በዲን ያልነበረና ወደ በወኋላ አዲስ የሚፈጠር መጤ ነገር ነው፣ አዲስ ነገር ሁሉ ደግሞ መጤ(ሰርጎ ገብ) ነው፣ በዲን ውስጥ ከጅምሩ ያልነበረ አዲስ መጤ ተግባር ደግሞ ጥመት ነው፣ እያንዳንዱ የጥመት ተግባር ደግሞ የእሳት ድርሻ ነው(ለእሳት የሚያበቃ ነው》ብለዋል።

➡️ መውሊድ፣ዓሹራና ሸዋል ፍች በቁርአንና በትክክለኛ ሐዲስ እስካልተደነገገ ድረስ ማንም አለ ብሎ ይናገር ማን ንግግሩ ውድቅ(ረድ) ሊደረግ ግድ ነው።

⬅️ عن أم المؤمنين عائشة رضي الله عنها قالت : قال رسول الله صلى الله عليه وسلم : ( من أحدث في أمرنا هذا ما ليس منه فهو رد ) رواه البخاري ومسلم ،

《ዓኢሻህ አላህ መልካም ስራዋን ይውደድላትና ባስተላለፈችው ሐዲስ ነብዩ ﷺ《በዚህ ዲናችን ውስጥ ከጅምሩ ያልነበረን ነገር ያስገኘ ሰው ያ ያስገኘው ነገር ሊስተባበል(ረድ) ሊደረግ የሚገባ ነው።》ብለዋል።

📚ኢማሙ ቡኻሪይ እና ሙስሊም ዘግበውታል።

⬅️ وفي رواية لمسلم : ( من عمل عملاً ليس عليه أمرنا فهو رد ) .

《በሌላ የነብዩ ﷺ ንግግር《አንድ ሰው የእኛ ትእዛዝ የሌለበትን ነገር በዲን ውስጥ ከተገበረ ይህ ተግባሩ ሊስተባበል(ውድቅ) ሊደረግ የሚገባ ተግባር ነው።》 ብለዋል።

📚ሙስሊም ዘግበውታል።

➡️ ነገ በአብዛሀኛው ባህልን ዲን አድርገው በሚገነዘቡና ዲንን በባህላዊ መንገድ በዘልማድ በሚያራምዱ የህብረተሰባችን ክፍል ዘንድ የሚከበረው የሸዋል ፍች በዲን ስም ከሚከበሩ ሰው ሰራሽ አመት_ በዓሎች(ዒዶች) መካከል አንዱና ዋነኛው ሲሆን ይህንን የቢዳዓ በዓልን የሚያከብሩ ሰዎች ከዲን የሚፃረር ባህላዊ እምነት እያከበሩ መሆናቸውን በሚገባ ሊያውቁ ይገባል።

➡️ ማንኛውም ከዲን ተፃራሪ አስተምህሮትና ተግባር ደግሞ በኢስላም ውስጥ አፍራሽ አመለካከት ነው።

👌በመሆኑም በቁርአንና በትክክለኛ የነብዩ ﷺ ሐዲስ የተደነገገውን ብቻ በመከተልና በመተግበር እንዲሁም በቁርአንና በትክክለኛ(በሰሒህ) በነብዩ ﷺ ሐዲስ ያልተደነገገን ነገር በሙሉ በመፀየፍና በመራቅ የትክክለኛው የኢስላም አስተምህሮት የሱና(የሰለፊያህ) ተከታይና አራማጅ መሆን የእያንዳንዱ ሙስሊም የነፍስ ወከፍ ግዴታ ነወ።

✍ አቡ ኢብራሂም

ሚያዚያ 27/08/2014ዓ ል

ሸዋል 05/10/1443 ዓ ሂ

http://telegram.me/abuibrahim0102030405


✔️ የሸዋል ፆምን የተመለከቱ ህግጋቶች

ክፍል ሁለት

ማስገንዘቢያ!!!!!!!!!!!!!!!!!!

⬅️أن الرسول ﷺ قال من صام رمضان ثم أتبعه ستاً من شوال  كان كصيام الدهر
↪️ነብዩ ﷺ ስለሸዋል ፆም ሲነገሩ የረመዳንን ወር ሙሉ ፆሞ ከሸዋል ወር ደግሞ ስድስት ቀን ያስከተለ አመቱን ሙሉ እንደ ፆመ ነው ሚቆጠርለት ብለዋል።

➡️ሙስሊም ሙሁራን ይህንን ሀዲስ በመንተራስ
1ኛ:《ሱመ》የምትለው የዐረብኛ አያያዥ ቃል ተራኺ(ቅድመ ተከተልን) አመልካች ስለሆነች ረመዷንን ሙሉ ፆሞ ስድስት ቀን ከሸዋል ወር ፆም ካስከትለ ከላይ የተጠቀሰውን የአንድ አመት ሙሉ ፆም ጀዛእ የሚያገኝ ሲሆን የረመዷንን ወር ፆም ሳያሟላና ማለትም ያጓደለውን ሳያሟላ ስድስት ቀን የሸዋል ፆምን ቢያስከትልም ግን ከላይ የተጠቀሰውን ጀዛእ አያገኝም ያሉ አሉ ምክንያቱም የረመዳንን ወር ሙሉ ፆሞ ከዛው ስድስት ቀን ከሸዋል የሚለውን ቅድመተከተል አላሟላምና።

➡️በመሆኑም በተለያየ ምክንያት ረመዷን ያጓደልን አለያም ሙሉ በሙሉ ያልፆምን ሰዎች የረመዷን ቀዷ በመክፈል ላይ ቅድሚያ እንስጥ።
2ኛ:《ሚን》ከፊልነትን ስለምታመላክት ማለትም ከሸዋል ወር ውስጥ ስድስት ቀን ያስከተለ የሚልን መልእክት ስለምታስተላልፍ ከዒደልፊጥር በበነጋው ጀምሮ ለተከታታይ ስድስት ቀን ወይም ከሙሉው ሸዋል ወር በተበታተነ መልኩም ቢሆን መፃም ይችላል ብለዋል። ﷺ

➡️ይህ ብያኔያቸው(ሁክማቸው) ትክክል ሆኖ ሳለ ወደ ሀገራችን ተጨባጭ ስንመለስ የተወሰነው የህዝባችን ክፍል የዒዱ እለት ማግስትንና ቀጣዩንም ቀን ጨምሮ ዒድ ገና አላለቀም በሚል የሸዋል ፆምን ለተከታታይ አንድ፣ሀለትና ሶስት ቀናት ሳይፆሙ ይቀሩና ከዛው ዘግይተው ይጀምሩና አብዛኛ ከዒድ ማግስት ጀምሮ ለተከታታይ ስድስት ቀናት ሲፆሙ የነበሩት የህብረተሰባችን ክፍል የሸዋልን ፆም ጨርሰው እንደወትሮው መብላትና መጠጣት ሲጀምሩ ዘግይተው መፆም የጀመሩት ወገኖቻችን ግን ከፆሙዋት ሶስትና አራት ቀን በቀር ያልፆሙትን ሁለትና ሶስት ቀን በቀር ያልፆሙትን ሁለትና ሶስት ቀናት ሳይተኩ የሸዋል ወር ይጠናቀቃል።

➡️ስለዚህ ወንድምና እህቶች ጎብዘን ለተከታታይ ስድስት ቀን በመፆም አለያም በተበታተነ መልኩ ከሆነ ደግሞ የሸዋል ወር ሳያልቅ ስድስት ቀን ቆጥርን በመፆም የተጠቀሰውን ጀዛእ ተሽቀዳድመን እንፈስ።

✍አቡ ኢብራሂም

ሚያዚያ 26/08/2014 ዓ ው
ሸዋል 03/10/1443 ዓ ሂ

https://telegram.me/alfikhul_islamiyah


የሸዋል ፆም ህግጋት

ክፍል አንድ

➡️ቀዷ መክፈል ወይስ ሸዋል መፆም ይቀድማል?????

➡️ የረመዳን ክፍያም(ቀዷም) ሆነ ሌላ የግዴታ ክፍያ (ቀዷ) ፆም እያለብን ሸዋልንም ሆነ ሌላ ማንኛውንም የሱና (ተጨማሪ) ፆም መፆም ነው ያለብን ወይስ ያለብንን የክፍያ ፆም(የቀዷ ፆም)
መክፈል ነው ያለብን????።

⬅️ ﻗﻀﺎﺀ ﺭﻣﻀﺎﻥ مقدم من التطوع بصيام بشوال
⬅️وجاء رجل الى رسول الله
ﻓﻘﺎﻝ :
⬅️《ﻳﺎ ﺭﺳﻮﻝ ﺍﻟﻠﻪ ﺇﻥ ﺃﻣﻲ ﻣﺎﺗﺖ ﻭﻋﻠﻴﻬﺎ ﺻﻮﻡ ﺷﻬﺮ ﺃﻓﺄﻗﻀﻴﻪ ﻋﻨﻬﺎ؟》
⬅️ﻗﺎﻝ : ‏( ﻧﻌﻢ ﺩﻳﻦ ﺍﻟﻠﻪ ﺃﺣﻖ ﺃﻥ ﻳﻘﻀﻰ ‏) ﺭﻭﺍﻩ ﺍﻟﺒﺨﺎﺭﻱ ﻭﻣﺴﻠﻢ،.
↪️አንድ ሰው ወደ ነብዩ ﷺ
ዘንድ መጣና እናቴ የአንድ ወር ሙሉ ያልፆመችው የግዴታ(የረመዳን) ፆም እያለባት ሞተች እኔ ልክፈልላት? ብሎ ሲጠይቃቸው
➡️ነብዩም ﷺ
አዎ ክፈልላት ያለተከፈለ የአላህ እዳ ከምንም ነገር በፊትና ቅድሚያ መከፈሉ ተገቢና አማራጭ ማይኖረው ግዴታ ነው ብለው።》 መልሰውለታል።
📚ይህን ሀዲስ
📚ኢማሙ ቡኻሪይና ሙስሊም መዝግበውታል።
⬅️وقال النبي قال الله تعالى في حديث القدسي
《وما تقرب إلي عبدي بشيء احب إلي مما افترضته عليه 》
📚رواه البخا ي
↪️ነብዩﷺ
ሀዲሰልቁይ ላይ እንደገለፁት አላህ እንዲህ አለ ብለዋል
➡️《ባሪያዬ ግዴታ ያደረኩበትን አምልኮ(ዒባዳህ) ከመተግበር የላቀ ወደኔ የሚቃረብበት ትልቅና ወደኔም ተወዳጅ የሆነ የዲን ተግባር የለም።》
📚ይህን ሀዲስ
📚ኢማሙ ቡኻሪይ መዝግበውታል።
▪قال ابن رجب رحمه الله :
⬅️《فمن كان عليه قضاء من شهر رمضان فليبدأ بقضائه في شوال فإنه أسرع لبراءة الذمة .》
📚 لطائف المعارف : (٢٢٣
↪️ኡብኑ ረጀብ አላህ ይዘንላቸውና
➡️「አንድ ሰው የረመዳን የክፍያ ፆም(ቀዷ) ካለበት የሸዋልን ፆም ፆሞ ከዛው ያለበትን የረመዳን የቀዷ ክፍያ ይክፈል ወይስ መጀመሪያ በቀጥታ የረመዳንን የቀዷ ክፍያ ይክፈል???」ተብለው ተጠይቀው ሲመልሱ:
➡️《መጀመሪያ ረመዳን ላይ ያጠፋውን ቁጥር ያህል ቀናት በሸዋል ቀናቶች አስቀድሞ ይክፈልና ቀዳውን ከፍሎ ሲጨርስ የሸዋል ወር ካላለቀ ሸዋልን ስድስት ቀን መፆም ይችላል ብለዋል።》
📚ለጣኢፉል አልመዓሪፍ(223)

➡️በመሆኑም በተለያየ አጋጣሚ ያልፆምነው የረመዳን እዳ ያለብን ወንዶችም ሆን ሴቶች ከሸዋልም ሆነ ከሌሎች የተጨማሪ(ሱና) ፆሞች አስቀድመን ያልፆምነውን የረመዳን እዳ በመክፈል ላይ መጎበዝና መበርታት አለብን።

✍አቡ ኢብራሂም

ሚያዚያ 25/08/2014 ዓ ል
ሸዋል 01/10/1443 ዓ ሂ

https://telegram.me/alfikhul_islamiyah




✔️ ዘካተል_ፊጥር

زكاة الفطر

ክፍል _አንድ

የዘካተል_ፊጥር ግዴታነት(ዋጅብነት)

⬅️ زكاة الفطر فرض بالسنة والإجماع

《ዘካተል ፊጥር: በቀደምት ሙስሊም ሙሁራን ግዴታ መሆኑ በሙሉ ድምፅ ስምምነት ላይ ተደርሶበታል(ኢጅማዕ ተደርጎበታል።》

⬅️ قال العراقي رحمه الله فيه وجب ركاة الفطر وهو مجمع عليه إليه إلا ممن شذ

➡️ አልዒራቂይ አላህ ይዘንላቸውና 《ዘካተል ፊጥር ግዴታ(ዋጅብ) በመሆኑ ላይቀደምት ሙስሊም ሊቃውንቶች በአንድ ድምፅ ተስማምተውበታል(ኢጅማዕ ተደርጎበታል።)

⬅️ قال إبن المنذر أجمع عوام أهل العلم. على ذلك

ኢብኑል ሙንዚር አላህ ይዘንላቸውና ዘካተል ፊጥር ግዴታ(ዋጅብ) ለመሆኑ አጠቃላይ ሙስሊም ሊቃውንቶች ተስማምተውበታል(ኢጅማዕ አድርገውበታል)

⬅️ قال إسحاق إبن راهويه هو كالإجماع من أهل العلم.

ኢስሐቅ ኢብኑ ራወይህ አላህ ይዘንላቸውና
《የዘካተል ፊጥር ግዴታነት አንደ አጠቃላይ የሙስሊም ሊቃውንቶች ስምምነት(እንደ ኢጀማዕ) የሚቆጠር ያህል ነው።》ብለዋል።

⬅️ قال الخطابي رحمه الله قال به عامة أهل العلم

《ኸጣቢይ አላህ ይዘንላቸውናየዘካተል ፊጥር ግዴታነት(ዋጅብነት) የአጠቃላይ የሙስሊም ሊቃውንት ስምምነት(ኢጅማዕ) ነው።》ብለዋል።

📚የሸኽ ዐብድል ዐዚዝ አረይስ የቴሌግራም ቻናል

✍ አቡ ኢብራሂም

ሚያዚያ 18/08/2014 ዓ ል
ረመዷን 25/09/1443 ዓ ሂ

https://telegram.me/alfikhul_islamiyah

20 last posts shown.

363

subscribers
Channel statistics