ስለ ጌጠኛ ልብስ - የመጨረሻ
እኅቴ ሆይ! እስኪ ንገሪኝ፤ የትኛው ትመርጫለሽ? እግዚአብሔር እንዲወድሽ ነውን ወይስ ሰው ይወድሽ ዘንድ ነው? በምግባር በትሩፋት ብታጌጪ እግዚአብሔር ይወድሻል፡፡ ጌጠኛ ልብስን ብትወጂ ግን ዘማውያን ይወዱሻል፤ እግዚአብሔርም ይጠላሻል፡፡ እግዚአብሔር የሚወደው ጌጠኛ ልብስን ሳይኾን ጌጠኛ ነፍስን ነውና፡፡ ዘማውያን ግን ጌጠኛ ነፍስን ሳይኾን ጌጠኛ አፍአዊ ሰውነትን ይወዳሉ፡፡
እናንተ ሴቶች ሆይ! እንግዲህ ከወንዶች ይልቅ እናንተን እንደወደድኳችሁ፣ በእውነተኛው ትሩፋት ታጌጡ ዘንድ እንደምደክም፣ ዘማውያን ከሚወዷችሁ እግዚአብሔር እንዲወዳችሁ እንደምተጋ አስተዋላችሁን?
እግዚአብሔር የሚወዳት ሴትስ ምን ትመስላለች? መላእክትን ትመስላለች፡፡ አንድ ምድራዊ ንጉሥ የሚወዳት ሴት ከኹሉም ይልቅ ደስተኛ ከኾነች ልዑል እግዚአብሔር ፈጽሞ የሚወዳት’ማ ክብሯ እንደ ምን ይበዛ ይኾን? ዓለሙን ኹሉ እስከ ምጽአት ድረስ ስትገዢ ብትኖሪ ይህን ክብር የሚተካከል የለም ብዬ በእውነት ያለ ሐሰት እነግርሻለሁ፡፡
እንግዲያው ተወዳጆች ሆይ! ማለፍ መለወጥ በሌለባት በመንግሥተ ሰማያት ጸጋንና ክብርን እናገኝ ዘንድ በምግባር በትሩፋት እናጊጥ፡፡ በዚህ ዓለም የሚኖረን ውበትና ጌጥ ድንገት ታይቶ የሚጠፋ ነው፡፡ የማይቻል ቢኾንም ምንም በሽታ፣ ኀዘን፣ ብስጭት፣ ይህም የመሳሰለ ኹሉ ባያገኘን እንኳን የዚህ ዓለም ውበትና ጌጥ ሃያ ዓመት ነው፡፡ በወዲያኛው ዓለም የሚሰጠው የሚገኘው ክብር ግን በዝቶ ሲሰጥ ይኖራል እንጂ መቼም ቢኾን መች አያልፍም፡፡ አይለወጥም፡፡ እርጅና የለምና ቆዳው አይጨማደድም፡፡ ደዌ ሥጋ ደዌ ነፍስ አያገኘውም፡፡ ኀዘን አያወይበውም፡፡ በዚያ የምናገኘው ክብር፣ ውበት፣ ጌጥ ከዚህ ኹሉ የተለየ ነው፡፡ በዚህ ዓለም የምናገኘው ክብርና ውበት ግን የሚጠፋው ገና ከመምጣቱ ነው፡፡ ቢመጣ እንኳን አድናቂዎቹ ብዙ አይደሉም፡፡ ትሩፋትን ጌጥ ያደረጉ ሰዎች አያደንቁትም፡፡ የሚያደንቁት አመንዝሮች ናቸው፡፡
ስለዚህ ከዚህ ዓለም ከኾነው ክብር ልንለይ ይገባናል፡፡ መንግሥተ ሰማያትን እንወርስ ዘንድ ልንፈልገው የሚገባን ትሩፋትን ነው፡፡
(የክርስቲያን መከራ እና ሌሎች ቅዱስ ዮሐንስ_አፈወርቅ እንደአስተማረው ገጽ 47-55➛ገብረ እግዚአብሔር ኪደ የተረጎመው)
እኅቴ ሆይ! እስኪ ንገሪኝ፤ የትኛው ትመርጫለሽ? እግዚአብሔር እንዲወድሽ ነውን ወይስ ሰው ይወድሽ ዘንድ ነው? በምግባር በትሩፋት ብታጌጪ እግዚአብሔር ይወድሻል፡፡ ጌጠኛ ልብስን ብትወጂ ግን ዘማውያን ይወዱሻል፤ እግዚአብሔርም ይጠላሻል፡፡ እግዚአብሔር የሚወደው ጌጠኛ ልብስን ሳይኾን ጌጠኛ ነፍስን ነውና፡፡ ዘማውያን ግን ጌጠኛ ነፍስን ሳይኾን ጌጠኛ አፍአዊ ሰውነትን ይወዳሉ፡፡
እናንተ ሴቶች ሆይ! እንግዲህ ከወንዶች ይልቅ እናንተን እንደወደድኳችሁ፣ በእውነተኛው ትሩፋት ታጌጡ ዘንድ እንደምደክም፣ ዘማውያን ከሚወዷችሁ እግዚአብሔር እንዲወዳችሁ እንደምተጋ አስተዋላችሁን?
እግዚአብሔር የሚወዳት ሴትስ ምን ትመስላለች? መላእክትን ትመስላለች፡፡ አንድ ምድራዊ ንጉሥ የሚወዳት ሴት ከኹሉም ይልቅ ደስተኛ ከኾነች ልዑል እግዚአብሔር ፈጽሞ የሚወዳት’ማ ክብሯ እንደ ምን ይበዛ ይኾን? ዓለሙን ኹሉ እስከ ምጽአት ድረስ ስትገዢ ብትኖሪ ይህን ክብር የሚተካከል የለም ብዬ በእውነት ያለ ሐሰት እነግርሻለሁ፡፡
እንግዲያው ተወዳጆች ሆይ! ማለፍ መለወጥ በሌለባት በመንግሥተ ሰማያት ጸጋንና ክብርን እናገኝ ዘንድ በምግባር በትሩፋት እናጊጥ፡፡ በዚህ ዓለም የሚኖረን ውበትና ጌጥ ድንገት ታይቶ የሚጠፋ ነው፡፡ የማይቻል ቢኾንም ምንም በሽታ፣ ኀዘን፣ ብስጭት፣ ይህም የመሳሰለ ኹሉ ባያገኘን እንኳን የዚህ ዓለም ውበትና ጌጥ ሃያ ዓመት ነው፡፡ በወዲያኛው ዓለም የሚሰጠው የሚገኘው ክብር ግን በዝቶ ሲሰጥ ይኖራል እንጂ መቼም ቢኾን መች አያልፍም፡፡ አይለወጥም፡፡ እርጅና የለምና ቆዳው አይጨማደድም፡፡ ደዌ ሥጋ ደዌ ነፍስ አያገኘውም፡፡ ኀዘን አያወይበውም፡፡ በዚያ የምናገኘው ክብር፣ ውበት፣ ጌጥ ከዚህ ኹሉ የተለየ ነው፡፡ በዚህ ዓለም የምናገኘው ክብርና ውበት ግን የሚጠፋው ገና ከመምጣቱ ነው፡፡ ቢመጣ እንኳን አድናቂዎቹ ብዙ አይደሉም፡፡ ትሩፋትን ጌጥ ያደረጉ ሰዎች አያደንቁትም፡፡ የሚያደንቁት አመንዝሮች ናቸው፡፡
ስለዚህ ከዚህ ዓለም ከኾነው ክብር ልንለይ ይገባናል፡፡ መንግሥተ ሰማያትን እንወርስ ዘንድ ልንፈልገው የሚገባን ትሩፋትን ነው፡፡
(የክርስቲያን መከራ እና ሌሎች ቅዱስ ዮሐንስ_አፈወርቅ እንደአስተማረው ገጽ 47-55➛ገብረ እግዚአብሔር ኪደ የተረጎመው)