💖የጥያቄዎች መልስ ክፍል 46💖
▶️፩."በሞቱም የገደላቸው ሙታን በሕይወት ሳለ ከገደላቸው በዙ" ይላል (መሳ.16፥30)። ሶምሶን የጌታቻን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ምሳሌ ተደርጎ ሲነገር እሰማለሁና ከዚህ ጥቅስ አንጻር ቢያብራሩልኝ።
✔️መልስ፦ ሶምሶን የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ምሳሌ ነው። ከዚህ በፊት ግን መረዳት ያለብን ምሳሌ ከሚመሰልለት ያነሰ መሆኑን ነው። ይህንን ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ተናግሮታል። የሀገራችን ሊቃውንትም ይህንን ለማስገንዘብ ምሳሌን ዘየሐጽጽ ብለው ይቀጽሉለታል። አንድ ነገር ለአንድ ነገር በጥቂት ነገር ስለተመሳሰለ ምሳሌ ሊመሰል ይችላል። ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህች ምድር በሥጋ እየተመላለሰ ሲያስተምር አጋንንትን ከሰዎች ያስለቅቃቸው ነበረ። ነገር ግን በዚህች ምድር ሲመላለስ ካጠፋቸው አጋንንት ይልቅ በመስቀል ላይ ተሰቅሎ ያጠፋቸው አጋንንት ይበዛሉ። ሶምሶንም በሕይወተ ሥጋ ሳለ ካጠፋቸው ሰዎች ይልቅ በሞቱ ያጠፋቸው ይበዛሉ። በሌላ መልኩ ሶምሶን ከሞተ አንበሳ አፍ ሳይጸየፍ ማር በልቷል። ከአህያ መንጋጋ የመነጨ ውሃንም ሳይጸየፍ ጠጥቷል። ጌታም የሰውን ሥጋ ሳይጸየፍ ተዋሕዶ ሰውን አድኖታል። በዚህና በዚህ ሶምሶን የጌታ ምሳሌ ነው ይባላል።
▶️፪. "የእስራኤልም ልጆች ወጥተው በእግዚአብሔር ፊት እስከ ማታ ድረስ አለቀሱ እግዚአብሔርንም ከወንድሞቻችን ከብንያም ልጆች ጋራ ለመዋጋት ዳግመኛ እንቀርባለን ብለው ጠየቁ። እግዚአብሔርም በእነርሱ ላይ ውጡ አለ" ይላል። ግን እግዚአብሔር አዟቸው ከሆነ እንዴት ተሸነፉ?
✔️መልስ፦ እግዚአብሔር በሚያውቀው ከእነርሱም መሞት የነበረባቸው ክፉዎች ሰዎች ስለነበሩ እንዲሸነፉ አድርጓቸዋል። ከእነርሱ መሞት የነበረባቸው ሰዎች ከሞቱ በኋላ በሦስተኛው ግጥሚያ እንዲያሸንፉ አድርጓል።
▶️፫. “የተቀረጸ ምስልና ቀልጦ የተሠራ ምስል አድርጌ ከእጄ ስለ ልጄ ለእግዚአብሔር እቀድሰዋለሁ” ይላል (መሳ.17፥3)። ይህች ሴት ጣዖት የምታመልክ ናት ወይስ እግዚአብሔርን?
✔️መልስ፦ ይህች ሴት ጣዖት አምላኪ ናት። ጣዖቷን እግዚአብሔር እያለችው ነው። ነገር ግን እርሷ ጣዖቷን እግዚአብሔር ወይም አምላክ ብትለውም ከወርቅ ጥፍጥፍ የሠራችው ጣዖት ነው።
▶️፬. “ሰውየውም ሚካ የአምላክ ቤት ነበረው” ይልና “ሚካም ሌዋዊ ካህን ስለ ሆነልኝ እግዚአብሔር መልካም እንዲሠራልኝ አሁን አውቃለሁ አለ” ይላል (መሳ.17፥13)። ሚካ እግዚአብሔርን ያመልክ ነበር ወይ?
✔️መልስ፦ መልሱ ከዚህ ከፍ ብሎ እንደተመለሰው ጥያቄ ነው። የሚያመልኩትን ጣዖት በራሳቸው እግዚአብሔር እያሉት ነው እንጂ ሚካም ያመልክ የነበረው ጣዖትን ነበረ። ሌዋዊውም የጣዖት አገልጋይ ሆኖ ክብሩን አዋረደ እንጂ የጣዖትም የእግዚአብሔርም አገልጋይ አልሆነም። ሚካ የጣዖት አገልጋይ ካህን ሆነ እንጂ።
▶️፭. “እስከዚያም ቀን ድረስ ለዳን ነገድ በእስራኤል ነገዶች መካከል ርስት አልደረሳቸውም ነበርና በዚያ ዘመን የሚቀመጡባት ርስት ይሹ ነበር” ይላል (መሳ.18፥1)። ለሁሉም እስራኤላውያን ነገዶች ርስት ደርሷቸው ሳለ ለምን ለዳን ነገዶች ርስት አልደረሳቸውም ተባለ?
✔️መልስ፦ የዳን ወገኖች ከነገደ ሮቤል ጋር በዮርዳኖስ ማዶ መውረሳቸውን መጽሐፈ ኢያሱን ስንማማር አይተናል። ነገር ግን የወረሱት ብዙ ስላልነበረ ሌላ ተጨማሪ ርስት መፈለጋቸውን ለመግለጽ ከዚህ ላይ ርስት አልደረሳቸውም ተብሎ ተገልጿል።
▶️፮. አንድ ሰው ሌዋዊ ሆኖ እንዴት ከይሁዳ ነገድ ሊሆን ይችላል? (መሳ.17፥7)።
✔️መልስ፦ በብሉይ ኪዳን ሕግ መሠረት ክህነት ከነገደ ሌዊ ለሚወለዱ ሰዎች እንዲሠጥ ሥርዓት ተሠርቷል። ከዚህ ላይ የተጠቀሰው ሰውም ካህነ ጣዖት እንጂ ካህነ እግዚአብሔር አይደለም። ካህንን ሌዋዊ ማለት ልማድ ስለሆነ ምንም እንኳ የጣዖት አገልጋይ ካህን ቢሆንም ሌዋዊ ተብሏል።
▶️፯. መሳ.21፥14 "በዚያም ጊዜ የብንያም ልጆች ተመለሱ፤ ከኢያቢስ ገለዓድም ሴቶች ያዳኗቸውን ሴቶች አገቧቸው። ነገር ግን የሚበቁ ሴቶች አላገኙም" ይላል። ካገቧቸው በኋላ እንዴት ነው የሚበቁ አልተገኙም የሚባለው?
✔️መልስ፦ የሚበቁ ሴቶች አላገኙም ማለት ወንዶች በዝተው ሴቶች አንሰው ስለነበረ። ከተጋቡ በኋላ ሴቶች አንሰው ሳያገቡ የቀሩ ወንዶች ነበሩ ለማለት ነው።
▶️፰. መሳ.16፥18 "ደሊላም የልቡን ሁሉ እንደ ገለጠላት ባየች ጊዜ፦ የልቡን ሁሉ ገልጦልኛልና ይህን ጊዜ ደግሞ ኑ ብላ ላከችና የፍልስጥኤማውያንን መኳንንት ጠራች። የፍልስጥኤማውያን መኳንንትም ብሩን በእጃቸው ይዘው ወደ እርሷ መጡ" ይላል። እንደበፊቱ እንዳላታለላት በምን እርግጠኛ ሆና ነው የልቡን ነግሮኛል ያለችው?
✔️መልስ፦ ይህንን የምታውቀው ደሊላ ናት። ደሊላ በምን ከልቡ እንደነገራት እንዳወቀች ተጽፎ አላገኘሁም አላውቀውም።
▶️፱. መሳ.18፥5 "እነርሱም፦ የምንሄድበት መንገድ የቀና መሆኑን እናውቅ ዘንድ እባክህ እግዚአብሔርን ጠይቅልን አሉት" ይላል። እነርሱ ስለምን ጣዖትን ታገለግላለህ ብለው መገሠጽ እያለባቸው እንዴት ጭራሽ ከካህነ ጣዖት እግዚአብሔርን እንዲጠይቅላቸው ያስባሉ?
✔️መልስ፦ ጣዖታቸውን እንደ አምላክ ስላዩት እግዚአብሔር አሉት እንጂ ከዚህ የተጠቀሰው ዋናው ፈጣሪ እግዚአብሔር አይደለም። አለመሆኑም ዝቅ ብሎ የጣዖት ዕቃዎችን ወሰዱ ተብሎ በመገለጹ ይታወቃል። እነርሱም በጣዖት የሚተማመኑ ነበሩ። ሰውየውም የጣዖት አገልጋይ ነበረ።
▶️፲. መሳ.19፥29 "ወደ ቤቱም በመጣ ጊዜ ካራ አነሣ፥ ዕቁባቱንም ይዞ ከአጥንቶቿ መለያያ ላይ ለአሥራ ሁለት ቈራርጦ ወደ እስራኤል አገር ሁሉ ሰደደ" ይላል። ሳይቆርጥ ለአንዱ ነገድ ቢልክ ዜናው በ12ቱ ነገድ ይሠማ የለምን ለምን ከ12 ቆራርጦ ለ12 ነገድ መላክ አስፈለገ?
✔️መልስ፦ ለሁሉም አጽንዖት ለመስጠትና በእስራኤል ሀገር እንዲህ ያለ ግፍ ተደረገ ለማለት ለ12 ቆራርጦ ለእያንዳንዱ ነገድ ልኮታል። ለአንዱ ነገድ ከመላክ ለ12 ነገድ መላክ ለመልእክቱ የበለጠ ጉልበት ይሰጠዋልና ነው።
▶️፲፩. ሶምሶን እንዴት አራት ጊዜ ተታለለ? የእግዚአብሔር እቅድ ወይስ የእርሱ እንዝህላልነት?
✔️መልስ፦ በሰዎች መታለል ውስጥ የእግዚአብሔር እቅድ የለም። የእግዚአብሔር እቅድ ሁሉ መልካም ነገርና ጽድቅ ነው። ስለዚህ ሶምሶን የተሰጠውን ነጻ ፈቃድ ተጠቅሞ በራሱ እንዝህላልነት አራት ጊዜ ተሸወደ ተታለለ ማለት ነው። እንጂ እግዚአብሔር እንዲታለል አላደረገውም።
▶️፲፪. "ይህን ብር የተቀረጸ ምስልና ቀልጦ የተሠራ ምስል አድርጌ ከእጄ ስለ ልጄ ለእግዚአብሔር እቀድሰዋለሁ፤ አሁንም ለአንተ እመልሰዋለሁ አለች" ይላል (መሳ.17፥3)። ምስል ብሎ ለእግዚአብሔር እቀድሰዋለሁ ይላልና ግልፅ ቢያደርጉልኝ።
✔️መልስ፦ ጣዖቷን እንደ አምላክ ስላየችው እግዚአብሔር አለችው እንጂ ልጅቷ የሠራቸው ምስል ጣዖት ነው።
▶️፲፫. "ድንግል ልጄና የእርሱም ዕቁባት፥ እነሆ፥ አሉ፥ አሁንም አወጣቸዋለሁ፤ አዋርዷቸው እንደ ወደዳችሁም አድርጉባቸው፤ ነገር ግን በዚህ ሰው ላይ እንደዚህ ያለ ኃጢአት አታድርጉ አላቸው" ይላል (መሳ.19፥24)። ሽማግሌው ሰውየውን ብቻ አድኖ ዕቁባቱን ግን አሳልፎ የሰጣትና ለሞት የዳረጋት ለምንድን ነው?
▶️፩."በሞቱም የገደላቸው ሙታን በሕይወት ሳለ ከገደላቸው በዙ" ይላል (መሳ.16፥30)። ሶምሶን የጌታቻን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ምሳሌ ተደርጎ ሲነገር እሰማለሁና ከዚህ ጥቅስ አንጻር ቢያብራሩልኝ።
✔️መልስ፦ ሶምሶን የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ምሳሌ ነው። ከዚህ በፊት ግን መረዳት ያለብን ምሳሌ ከሚመሰልለት ያነሰ መሆኑን ነው። ይህንን ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ተናግሮታል። የሀገራችን ሊቃውንትም ይህንን ለማስገንዘብ ምሳሌን ዘየሐጽጽ ብለው ይቀጽሉለታል። አንድ ነገር ለአንድ ነገር በጥቂት ነገር ስለተመሳሰለ ምሳሌ ሊመሰል ይችላል። ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህች ምድር በሥጋ እየተመላለሰ ሲያስተምር አጋንንትን ከሰዎች ያስለቅቃቸው ነበረ። ነገር ግን በዚህች ምድር ሲመላለስ ካጠፋቸው አጋንንት ይልቅ በመስቀል ላይ ተሰቅሎ ያጠፋቸው አጋንንት ይበዛሉ። ሶምሶንም በሕይወተ ሥጋ ሳለ ካጠፋቸው ሰዎች ይልቅ በሞቱ ያጠፋቸው ይበዛሉ። በሌላ መልኩ ሶምሶን ከሞተ አንበሳ አፍ ሳይጸየፍ ማር በልቷል። ከአህያ መንጋጋ የመነጨ ውሃንም ሳይጸየፍ ጠጥቷል። ጌታም የሰውን ሥጋ ሳይጸየፍ ተዋሕዶ ሰውን አድኖታል። በዚህና በዚህ ሶምሶን የጌታ ምሳሌ ነው ይባላል።
▶️፪. "የእስራኤልም ልጆች ወጥተው በእግዚአብሔር ፊት እስከ ማታ ድረስ አለቀሱ እግዚአብሔርንም ከወንድሞቻችን ከብንያም ልጆች ጋራ ለመዋጋት ዳግመኛ እንቀርባለን ብለው ጠየቁ። እግዚአብሔርም በእነርሱ ላይ ውጡ አለ" ይላል። ግን እግዚአብሔር አዟቸው ከሆነ እንዴት ተሸነፉ?
✔️መልስ፦ እግዚአብሔር በሚያውቀው ከእነርሱም መሞት የነበረባቸው ክፉዎች ሰዎች ስለነበሩ እንዲሸነፉ አድርጓቸዋል። ከእነርሱ መሞት የነበረባቸው ሰዎች ከሞቱ በኋላ በሦስተኛው ግጥሚያ እንዲያሸንፉ አድርጓል።
▶️፫. “የተቀረጸ ምስልና ቀልጦ የተሠራ ምስል አድርጌ ከእጄ ስለ ልጄ ለእግዚአብሔር እቀድሰዋለሁ” ይላል (መሳ.17፥3)። ይህች ሴት ጣዖት የምታመልክ ናት ወይስ እግዚአብሔርን?
✔️መልስ፦ ይህች ሴት ጣዖት አምላኪ ናት። ጣዖቷን እግዚአብሔር እያለችው ነው። ነገር ግን እርሷ ጣዖቷን እግዚአብሔር ወይም አምላክ ብትለውም ከወርቅ ጥፍጥፍ የሠራችው ጣዖት ነው።
▶️፬. “ሰውየውም ሚካ የአምላክ ቤት ነበረው” ይልና “ሚካም ሌዋዊ ካህን ስለ ሆነልኝ እግዚአብሔር መልካም እንዲሠራልኝ አሁን አውቃለሁ አለ” ይላል (መሳ.17፥13)። ሚካ እግዚአብሔርን ያመልክ ነበር ወይ?
✔️መልስ፦ መልሱ ከዚህ ከፍ ብሎ እንደተመለሰው ጥያቄ ነው። የሚያመልኩትን ጣዖት በራሳቸው እግዚአብሔር እያሉት ነው እንጂ ሚካም ያመልክ የነበረው ጣዖትን ነበረ። ሌዋዊውም የጣዖት አገልጋይ ሆኖ ክብሩን አዋረደ እንጂ የጣዖትም የእግዚአብሔርም አገልጋይ አልሆነም። ሚካ የጣዖት አገልጋይ ካህን ሆነ እንጂ።
▶️፭. “እስከዚያም ቀን ድረስ ለዳን ነገድ በእስራኤል ነገዶች መካከል ርስት አልደረሳቸውም ነበርና በዚያ ዘመን የሚቀመጡባት ርስት ይሹ ነበር” ይላል (መሳ.18፥1)። ለሁሉም እስራኤላውያን ነገዶች ርስት ደርሷቸው ሳለ ለምን ለዳን ነገዶች ርስት አልደረሳቸውም ተባለ?
✔️መልስ፦ የዳን ወገኖች ከነገደ ሮቤል ጋር በዮርዳኖስ ማዶ መውረሳቸውን መጽሐፈ ኢያሱን ስንማማር አይተናል። ነገር ግን የወረሱት ብዙ ስላልነበረ ሌላ ተጨማሪ ርስት መፈለጋቸውን ለመግለጽ ከዚህ ላይ ርስት አልደረሳቸውም ተብሎ ተገልጿል።
▶️፮. አንድ ሰው ሌዋዊ ሆኖ እንዴት ከይሁዳ ነገድ ሊሆን ይችላል? (መሳ.17፥7)።
✔️መልስ፦ በብሉይ ኪዳን ሕግ መሠረት ክህነት ከነገደ ሌዊ ለሚወለዱ ሰዎች እንዲሠጥ ሥርዓት ተሠርቷል። ከዚህ ላይ የተጠቀሰው ሰውም ካህነ ጣዖት እንጂ ካህነ እግዚአብሔር አይደለም። ካህንን ሌዋዊ ማለት ልማድ ስለሆነ ምንም እንኳ የጣዖት አገልጋይ ካህን ቢሆንም ሌዋዊ ተብሏል።
▶️፯. መሳ.21፥14 "በዚያም ጊዜ የብንያም ልጆች ተመለሱ፤ ከኢያቢስ ገለዓድም ሴቶች ያዳኗቸውን ሴቶች አገቧቸው። ነገር ግን የሚበቁ ሴቶች አላገኙም" ይላል። ካገቧቸው በኋላ እንዴት ነው የሚበቁ አልተገኙም የሚባለው?
✔️መልስ፦ የሚበቁ ሴቶች አላገኙም ማለት ወንዶች በዝተው ሴቶች አንሰው ስለነበረ። ከተጋቡ በኋላ ሴቶች አንሰው ሳያገቡ የቀሩ ወንዶች ነበሩ ለማለት ነው።
▶️፰. መሳ.16፥18 "ደሊላም የልቡን ሁሉ እንደ ገለጠላት ባየች ጊዜ፦ የልቡን ሁሉ ገልጦልኛልና ይህን ጊዜ ደግሞ ኑ ብላ ላከችና የፍልስጥኤማውያንን መኳንንት ጠራች። የፍልስጥኤማውያን መኳንንትም ብሩን በእጃቸው ይዘው ወደ እርሷ መጡ" ይላል። እንደበፊቱ እንዳላታለላት በምን እርግጠኛ ሆና ነው የልቡን ነግሮኛል ያለችው?
✔️መልስ፦ ይህንን የምታውቀው ደሊላ ናት። ደሊላ በምን ከልቡ እንደነገራት እንዳወቀች ተጽፎ አላገኘሁም አላውቀውም።
▶️፱. መሳ.18፥5 "እነርሱም፦ የምንሄድበት መንገድ የቀና መሆኑን እናውቅ ዘንድ እባክህ እግዚአብሔርን ጠይቅልን አሉት" ይላል። እነርሱ ስለምን ጣዖትን ታገለግላለህ ብለው መገሠጽ እያለባቸው እንዴት ጭራሽ ከካህነ ጣዖት እግዚአብሔርን እንዲጠይቅላቸው ያስባሉ?
✔️መልስ፦ ጣዖታቸውን እንደ አምላክ ስላዩት እግዚአብሔር አሉት እንጂ ከዚህ የተጠቀሰው ዋናው ፈጣሪ እግዚአብሔር አይደለም። አለመሆኑም ዝቅ ብሎ የጣዖት ዕቃዎችን ወሰዱ ተብሎ በመገለጹ ይታወቃል። እነርሱም በጣዖት የሚተማመኑ ነበሩ። ሰውየውም የጣዖት አገልጋይ ነበረ።
▶️፲. መሳ.19፥29 "ወደ ቤቱም በመጣ ጊዜ ካራ አነሣ፥ ዕቁባቱንም ይዞ ከአጥንቶቿ መለያያ ላይ ለአሥራ ሁለት ቈራርጦ ወደ እስራኤል አገር ሁሉ ሰደደ" ይላል። ሳይቆርጥ ለአንዱ ነገድ ቢልክ ዜናው በ12ቱ ነገድ ይሠማ የለምን ለምን ከ12 ቆራርጦ ለ12 ነገድ መላክ አስፈለገ?
✔️መልስ፦ ለሁሉም አጽንዖት ለመስጠትና በእስራኤል ሀገር እንዲህ ያለ ግፍ ተደረገ ለማለት ለ12 ቆራርጦ ለእያንዳንዱ ነገድ ልኮታል። ለአንዱ ነገድ ከመላክ ለ12 ነገድ መላክ ለመልእክቱ የበለጠ ጉልበት ይሰጠዋልና ነው።
▶️፲፩. ሶምሶን እንዴት አራት ጊዜ ተታለለ? የእግዚአብሔር እቅድ ወይስ የእርሱ እንዝህላልነት?
✔️መልስ፦ በሰዎች መታለል ውስጥ የእግዚአብሔር እቅድ የለም። የእግዚአብሔር እቅድ ሁሉ መልካም ነገርና ጽድቅ ነው። ስለዚህ ሶምሶን የተሰጠውን ነጻ ፈቃድ ተጠቅሞ በራሱ እንዝህላልነት አራት ጊዜ ተሸወደ ተታለለ ማለት ነው። እንጂ እግዚአብሔር እንዲታለል አላደረገውም።
▶️፲፪. "ይህን ብር የተቀረጸ ምስልና ቀልጦ የተሠራ ምስል አድርጌ ከእጄ ስለ ልጄ ለእግዚአብሔር እቀድሰዋለሁ፤ አሁንም ለአንተ እመልሰዋለሁ አለች" ይላል (መሳ.17፥3)። ምስል ብሎ ለእግዚአብሔር እቀድሰዋለሁ ይላልና ግልፅ ቢያደርጉልኝ።
✔️መልስ፦ ጣዖቷን እንደ አምላክ ስላየችው እግዚአብሔር አለችው እንጂ ልጅቷ የሠራቸው ምስል ጣዖት ነው።
▶️፲፫. "ድንግል ልጄና የእርሱም ዕቁባት፥ እነሆ፥ አሉ፥ አሁንም አወጣቸዋለሁ፤ አዋርዷቸው እንደ ወደዳችሁም አድርጉባቸው፤ ነገር ግን በዚህ ሰው ላይ እንደዚህ ያለ ኃጢአት አታድርጉ አላቸው" ይላል (መሳ.19፥24)። ሽማግሌው ሰውየውን ብቻ አድኖ ዕቁባቱን ግን አሳልፎ የሰጣትና ለሞት የዳረጋት ለምንድን ነው?