✝️መዝሙረ ዳዊት ክፍል 7✝️
✝️መዝሙር ፭
መዝሙር 5 ስለትሩፋን የተጻፈ ነው፡፡ ትሩፋን የሚላቸው አሥሩ ነገድ ተማርከው በኢየሩሳሌም የቀሩ ሁለቱ ነገድ ናቸው፡፡ አንድም ሁሉም ተማርከው አበው አልቀው የቀሩ ውሉድ ናቸው፡፡ አቤቱ ልመናዬን ስማኝ፡፡ ጌታ ሆይ የእኔ ንጉሤም ፈጣሪዬም አንተ ነህ፡፡ እግዚኦ ምርሐኒ በጽድቅከ፡፡ ሰውን መበደል እግዚአብሔርን ማሳዘን ነው፡፡
✝️መዝሙር ፮
ዳዊት በቤርሳቤህ ምክንያት ያስገደለው ኦርዮ የጌታ ምሳሌ ነው፡፡ ኦርዮ ጦማረ ሞቱን ይዞ ከኢየሩሳሌም ወደ አራቦት እንደሄደ ጌታም ከሊቶስጥራ ወደ ቀራንዮ መስቀሉን ተሸክሞ ሄዷልና፡፡ በቀድሞው ዘመን ነቢያት ዘመነ ሣህል ወርኀ ሰላም ነው ሲሉ ኩፋር ለብሰው ኩፋር ጠምጥመው በአምባላይ ፈረስ ተቀምጠው መነሳንስ ይዘው ይታያሉ፡፡ ዘመነ ፀብዕ ወርኀ ኀዘን ነው ሲሉ ከል ለብሰው ከል ጠምጥመው ዘገር ይዘው ይታያሉ፡፡ ዳዊት ኦርዮን በማስገደሉ ተጸጽቶ ጉድጓድ ምሶ አመድ ነስንሶ ማቅ ለብሶ ንስሓ ገባ፡፡ በእንባው የበቀለ ሰርዶ ሰውነቱን ተብትቦ ይዞት ብላቴኖቹ በመቀስ እያረፉ አውጥተውታል፡፡ ዳዊት በነፍሱ ይቅር ሲባል በሥጋው ግን ኃጢአት ያለፍዳ አይነፃምና ልጁ እንዲያሳድደው ሆኗል፡፡
© በትረ ማርያም አበባው
🌹የዩቲዩብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።
🌻የፌስቡክ ገጼ Betremariam Abebaw https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።
✝️መዝሙር ፭
መዝሙር 5 ስለትሩፋን የተጻፈ ነው፡፡ ትሩፋን የሚላቸው አሥሩ ነገድ ተማርከው በኢየሩሳሌም የቀሩ ሁለቱ ነገድ ናቸው፡፡ አንድም ሁሉም ተማርከው አበው አልቀው የቀሩ ውሉድ ናቸው፡፡ አቤቱ ልመናዬን ስማኝ፡፡ ጌታ ሆይ የእኔ ንጉሤም ፈጣሪዬም አንተ ነህ፡፡ እግዚኦ ምርሐኒ በጽድቅከ፡፡ ሰውን መበደል እግዚአብሔርን ማሳዘን ነው፡፡
✝️መዝሙር ፮
ዳዊት በቤርሳቤህ ምክንያት ያስገደለው ኦርዮ የጌታ ምሳሌ ነው፡፡ ኦርዮ ጦማረ ሞቱን ይዞ ከኢየሩሳሌም ወደ አራቦት እንደሄደ ጌታም ከሊቶስጥራ ወደ ቀራንዮ መስቀሉን ተሸክሞ ሄዷልና፡፡ በቀድሞው ዘመን ነቢያት ዘመነ ሣህል ወርኀ ሰላም ነው ሲሉ ኩፋር ለብሰው ኩፋር ጠምጥመው በአምባላይ ፈረስ ተቀምጠው መነሳንስ ይዘው ይታያሉ፡፡ ዘመነ ፀብዕ ወርኀ ኀዘን ነው ሲሉ ከል ለብሰው ከል ጠምጥመው ዘገር ይዘው ይታያሉ፡፡ ዳዊት ኦርዮን በማስገደሉ ተጸጽቶ ጉድጓድ ምሶ አመድ ነስንሶ ማቅ ለብሶ ንስሓ ገባ፡፡ በእንባው የበቀለ ሰርዶ ሰውነቱን ተብትቦ ይዞት ብላቴኖቹ በመቀስ እያረፉ አውጥተውታል፡፡ ዳዊት በነፍሱ ይቅር ሲባል በሥጋው ግን ኃጢአት ያለፍዳ አይነፃምና ልጁ እንዲያሳድደው ሆኗል፡፡
© በትረ ማርያም አበባው
🌹የዩቲዩብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።
🌻የፌስቡክ ገጼ Betremariam Abebaw https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።