💙💙 የጥያቄዎች መልስ ክፍል 109 💙💙
▶️፩. ቢትወደድ የሚለው ቃል ፍች ምንድን ነው?
✔️መልስ፦ ቢትወደድ ማለት በንጉሡ ከሁሉ በላይ የሚወደድ ባለሥልጣን ማለት ነው።
▶️፪. ዮዲ.፲፪፥፰ ላይ "ሌሊትም ወጥታ በምንጩ ውሃ ትጠመቅ ነበር" ይላል የምን ጥምቀት ነው?
✔️መልስ፦ ለምን ትጠመቅ እንደነበረ ምክንያቱን መጽሐፍ ቅዱሱ አይገልጽም። የልጅነት ጥምቀት እንዳልሆነ ግን ይታወቃል። የልጅነት ጥምቀት የተሰጠው ከጌታ ልደት በኋላ ነውና።
▶️፫. የብሉይ ኪዳን ሰዎች ግድያን እንደጽድቅ መውሰዳችን ራሳችን በመረዳት ወይስ እግዚአብሔር ጽድቅ ነው ብሎ ነው?
✔️መልስ፦ በብሉይ ኪዳን በግፍ መግደል ኃጢአት ነበር። ነገር ግን በግፍ የገደለ ሰውን መግደል ፍትሓዊ ስለነበረ እንደጽድቅ ይቆጠር ነበር።
▶️፬. ዮዲ.፲፩፥፲፱ ላይ "በመካከሏም ዙፋንህን ትዘረጋለህ እረኛቸውም እንደበተናቸው በጎች ፈጽመህ ትከብባቸዋለህ ውሻም አይጮህብህም" የሚለው ሽንገላ አይሆንም?
✔️መልስ፦ ጠላትን ለማጥፋት እና ከጠላት ለመዳን መስሎ መቅረብ ሽንገላ አይሆንም። ዮዲት የእስራኤልን ጠላት ሆሎፎርኒስን ለማጥፋት ሰላማዊ መስላ ቀርባ ገድለዋለች። ዳዊት ከንጉሥ አንኩስ ለመዳን እብድ መስሎ ታይቷል። ንጹሓንን ለማጥፋት ንጹሕ መስሎ መቅረብ ነው ሽንገላ።
▶️፭. ጾመ ድኅነት እና ጾመ ዮዲት የዕለት ግንኙነት አለው?
✔️መልስ፦ ጾመ ድኅነት በሐዲስ ኪዳን የመጣ ጾም ነው። ይኸውም ረቡዕ እና ዓርብን መጾም ነው። ጾመ ዮዲት በብሉይ ኪዳን የነበረና ዮዲት የጾመችው ጾም ነው። ስለዚህ በዘመን አይገናኙም።
▶️፮. ዮዲ.16፥20-21 ከፍርድ ቀን በኋላ የሥጋ ቅጣት አለ እንዴ?
✔️መልስ፦ በትንሣኤ ጊዜ ነፍስ ከሥጋ ጋር ተዋሕዳ ትነሣለች እንጂ ሥጋ ፈርሶና በስብሶ አይቀርም። ስለዚህ ገሃነም የገባ ሰው መከራ የሚደርስበት ከነሥጋው ስለሆነ ወይፌኑ እሳተ ወዕፄ ዲበ ሥጋሆሙ ተብሏል።
▶️፯. "ባግዋም እያለቀሰና እየቃሰተ በታላቅ ቃል ፈጽሞ ጮኽ ልብሱንም ቀደደ" ይላል። አሕዛብም ሲያዝኑ ልብስ መቅደድ ለአሕዛብ ልምዳቸው ነበር ማለት ነው?
✔️መልስ፦ አዎ። በብዙዎች ሀገሮች ልብስን መቅደድ ትእምርተ ኀዘን (የኀዘን ምልክት) ነው። ስለዚህ ከአሕዛብ ወገን የነበረው ባግዋ ልብሱን ቀድዷል።
© በትረ ማርያም አበባው
✝️የዩቲዩብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።
🌻የፌስቡክ ገጼ Betremariam Abebaw https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።
▶️፩. ቢትወደድ የሚለው ቃል ፍች ምንድን ነው?
✔️መልስ፦ ቢትወደድ ማለት በንጉሡ ከሁሉ በላይ የሚወደድ ባለሥልጣን ማለት ነው።
▶️፪. ዮዲ.፲፪፥፰ ላይ "ሌሊትም ወጥታ በምንጩ ውሃ ትጠመቅ ነበር" ይላል የምን ጥምቀት ነው?
✔️መልስ፦ ለምን ትጠመቅ እንደነበረ ምክንያቱን መጽሐፍ ቅዱሱ አይገልጽም። የልጅነት ጥምቀት እንዳልሆነ ግን ይታወቃል። የልጅነት ጥምቀት የተሰጠው ከጌታ ልደት በኋላ ነውና።
▶️፫. የብሉይ ኪዳን ሰዎች ግድያን እንደጽድቅ መውሰዳችን ራሳችን በመረዳት ወይስ እግዚአብሔር ጽድቅ ነው ብሎ ነው?
✔️መልስ፦ በብሉይ ኪዳን በግፍ መግደል ኃጢአት ነበር። ነገር ግን በግፍ የገደለ ሰውን መግደል ፍትሓዊ ስለነበረ እንደጽድቅ ይቆጠር ነበር።
▶️፬. ዮዲ.፲፩፥፲፱ ላይ "በመካከሏም ዙፋንህን ትዘረጋለህ እረኛቸውም እንደበተናቸው በጎች ፈጽመህ ትከብባቸዋለህ ውሻም አይጮህብህም" የሚለው ሽንገላ አይሆንም?
✔️መልስ፦ ጠላትን ለማጥፋት እና ከጠላት ለመዳን መስሎ መቅረብ ሽንገላ አይሆንም። ዮዲት የእስራኤልን ጠላት ሆሎፎርኒስን ለማጥፋት ሰላማዊ መስላ ቀርባ ገድለዋለች። ዳዊት ከንጉሥ አንኩስ ለመዳን እብድ መስሎ ታይቷል። ንጹሓንን ለማጥፋት ንጹሕ መስሎ መቅረብ ነው ሽንገላ።
▶️፭. ጾመ ድኅነት እና ጾመ ዮዲት የዕለት ግንኙነት አለው?
✔️መልስ፦ ጾመ ድኅነት በሐዲስ ኪዳን የመጣ ጾም ነው። ይኸውም ረቡዕ እና ዓርብን መጾም ነው። ጾመ ዮዲት በብሉይ ኪዳን የነበረና ዮዲት የጾመችው ጾም ነው። ስለዚህ በዘመን አይገናኙም።
▶️፮. ዮዲ.16፥20-21 ከፍርድ ቀን በኋላ የሥጋ ቅጣት አለ እንዴ?
✔️መልስ፦ በትንሣኤ ጊዜ ነፍስ ከሥጋ ጋር ተዋሕዳ ትነሣለች እንጂ ሥጋ ፈርሶና በስብሶ አይቀርም። ስለዚህ ገሃነም የገባ ሰው መከራ የሚደርስበት ከነሥጋው ስለሆነ ወይፌኑ እሳተ ወዕፄ ዲበ ሥጋሆሙ ተብሏል።
▶️፯. "ባግዋም እያለቀሰና እየቃሰተ በታላቅ ቃል ፈጽሞ ጮኽ ልብሱንም ቀደደ" ይላል። አሕዛብም ሲያዝኑ ልብስ መቅደድ ለአሕዛብ ልምዳቸው ነበር ማለት ነው?
✔️መልስ፦ አዎ። በብዙዎች ሀገሮች ልብስን መቅደድ ትእምርተ ኀዘን (የኀዘን ምልክት) ነው። ስለዚህ ከአሕዛብ ወገን የነበረው ባግዋ ልብሱን ቀድዷል።
© በትረ ማርያም አበባው
✝️የዩቲዩብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።
🌻የፌስቡክ ገጼ Betremariam Abebaw https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።