🍃بالقرآن نحي {በቁርአን እንኖራለን


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: not specified


የተለያዩ ቁርኣናዊ አስተምህሮ’ዎች፣ ጣፋጭ ቲላዋዎች፣ ቁርኣንን የሚመለከቱና በቁርኣን ዙሪያ የሚሽከረከሩ መልዕክቶች የሚተላለፍበት ቻናል join ይበሉ !
ቁርኣን የወረደው ለሰው ልጅ መመሪያ፣ እንድናስተነትነውና እንድንገሰፅበት ነው።
አላህ እንዲህ ይላል፦ (ይህ) ወዳንተ ያወረድነው ብሩክ መጽሐፍ ነው፡፡ አንቀጾቹን እንዲያስተነትኑና የአእምሮዎች ባለቤቶችም እንዲገሰጹ (አወረድነው)፡፡ {Q 38:29}

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
not specified
Statistics
Posts filter


Forward from: Venue
« በእንያ አይጠገብ ምግባረ ንፁህ፣ በወቅት፣ በዘመን የማይገደብ ፍቅርና አክብሮትን ልቦች ሸሽገው በሚያስቀምጡላቸው፣ ፈገግታቸው የትፍስህት ደጃፍ የሚያደርስ፣ ጥዑም ቃላቸው ምሬትን ሁሉ በሚያስወግደው፣ ቃላት ሊገልፇቸው ተስገብግበው አልሆንልህ ሲላቸው አደብን በሚማሩባቸው፣ በእንያ ጠቢብ ወግ አዋቂ፣ ተጠይቀው በማይከለክሉት፣ ጠይቀው በማይከለከሉት፣ አላህ አብልጦ በወደዳቸው፣ መወሳታቸውንም ከፍ ባደረገው፣ በረሱሉል አሚን፣ በንፁሁ አፋቃሪው፣ በተከበሩት በአላህ ነብይ በነብዩል ሁዳ፣ በአንቢያዎቹ ኢማም፣ በፋጢመቱ የአይን ማረፍያ፣ በአዒሸቱ ደስታ፣ በኡመቱ ጠበቃ፣ በጭንቁ ቀን አማላጁ፣ በሰውነት ልኬቱ፣ በሁሉም ተናፋቂው፣ በንፁሁ ነብይ ላይ የአላህ ሰላምና እዝነት ይስፈን!
እናንተ አማኞች ሆይ ውበታችሁ በሆኑት በአላህ ነብይ ላይ ትዋቡ ዘንድ ሰለዋትን አወርዱ!»
[ አብዱልሀኪም ሰፋ ]
:
@Venuee13
@Venuee13


إِنَّ رَبِّي لَطِيفٞ لِّمَا يَشَآءُۚ إِنَّهُۥ هُوَ ٱلۡعَلِيمُ ٱلۡحَكِيمُ }

ጌታዬ ለሚሻው ነገር እዝነቱ ረቂቅ ነው፡፡ እነሆ እሱ ዐዋቂው ጥበበኛው ነው» አለ፡፡

[Surah Yūsuf: 100]




Forward from: ABX
ሰውን ስንፈራ ከሰው እንሸሻለን፡፡ አላህን ስንፈራ ግን ወደ አላህ እንሸሻለን፡፡

የፈጠረን ጌታ አላህ ሁሌም መሸሻችን መጠጊያችን ነው፡፡
አጥፍተን ማንኳኳት የማንፈራው ቤት የሱ ብቻ ነው፡፡

አላህን ያዙ፣
አላህን ተማመኑ፣
ወደ አላህ ሽሹ፡፡

ከሚያሳምማችሁ ነገር ሁሉ ወደ አላህ ሽሹ፡፡
ከሚያስፈራችሁ ነገር ሁሉ ወደ አላህ ሸሹ፡፡
ሸክም ሲከብዳችሁ፣
ሀሳብ ሲጫናችሁ፣
ሲጨንቃችሁ፣
ሲሰለቻችሁ፣
ብቸኝነት ሲሰማችሁ፣
ሁሉ ነገር ሲያስጠላችሁ፣
ተስፋ መቁረጥ ሲያገኛችሁ፡፡
ወደ አላህ ሽሹ።

ከዱንያ ፈተና፣
ከሕይወት ሞት መከራ፣
ከመጥፎ ውሎና አዳር፣
ወደ አላህ ሽሹ፡፡

ከብቸኝነት፣
ከድካም፣
ከስንፍና፣
ከመጥፎ ሀሳብ፣
ከፍርሃት
ወደ አላህ ሽሹ፡፡

በተለይ ደግሞ
ከፈተና በኋላ፣
ከውድቀት በኋላ፣
ከውርደት በኋላ፣
ከኃጢኣት በኋላ፣
ከሰው ጠብቃችሁ ካጣችሁ በኋላ… ሁሉ ወደ አላህ ሽሹ፡፡

ጌታዬ፣
ጥላዬ፣
ከለላዬ፣
መከታዬ፣
ሰታሪዬ፣

ጥፋት አበዛህ ብለህ የማትመልስ፣
ለመምጣት ዘገየህ ብለህ የማታባርር ፣
ሁሌም የማታሳፍር አንተ ብቻ ነህ፡፡

መሳአል ኸይር
መልካም ጁምዓ።


https://t.me/MuhammedSeidAbx


https://vt.tiktok.com/ZS66qfcft/
Visit TikTok to discover videos!
Watch, follow, and discover more trending content.


ኃይል የለንም፣ ጉልበት የለንም፣ ብልሃት የለንም፣ ብልጠት የለንም፣ መላ የለንም፣ ዕውቀት የለንም፣ የበላይነት የለንም …
ብቻ አንተን ይዘን፣ አንተን አስበን፣ ባንተ ተመክተን … ቢስሚላህ ተወከልቱ ዐለሏህ ብለን እንወጣለን፡፡ ትመራናለህ፣ ታመላክተናለህ፣ ታሳካልናለህ … ብለን እናስባለን፡፡

ጌታዬ ሆይ !

እኛ የምንወደውን ሳይሆን አንተ የምትወደውን መልካም ውሎ አውሎን፡፡
ያንተ ምርጫ ከኛ ምኞት ይበልጣልና፡፡

ሶባሐል ኸይር ወዳጆቼ

https://t.me/MuhammedSeidAbx


አላህ ብዙ ፀጋዎችን ሠጠን።  ከተሠጠነ ፀጋ ዘካ ማውጣት ይጠበቅብናል። ትንሽ ትልቅ ብለን አንናቅ። ዘካ በረከትን ያመጣል። ዕውቀትን፣ ገንዘብን፣ ዕድሜን ያፋፋል።
አላህ በሰጣችሁ ነገር ሁሉ ሰዎችን እርዱ። ማገዝ በምትችሉትም እገዙ። ከችሮታዉም ለወንድም እህቶቻችሁ ቆንጥሩ። እኔ ምንም የለኝም አትበሉ። ሀሳብና ምክር፣ ገንዘብና ጉልበት፣ ጊዜና ዕውቀት፣ ተስፋና ፈገግታ ...እነኝህ ሁሉ ልናጋራቸው የሚገቡ የአላህ ፀጋዎች ናቸው። እናካፍላቸው ወዳጆቼ። ስናካፍላቸው ይበዙልናልና።
ከተሠጣችሁ አካፍላችሁ የምምውሉ ሁኑ።
ሶባሐል ኸይር❤

https://t.me/MuhammedSeidAbx


ادعُ ربَّك ولا تستعظم مطلوبك، ولا تستكثر سؤالك، بل ادعُه وكلُّك ثقة بجوده وكرمه، وغناه وقدرته، فإنه لا يعسُر على الغني القادر أن يعطي مَن شاء ما شاء .


Forward from: ABX
ወዳጄ!
ሁላችንም ወደ አላህ እየሄድን ነው፡፡ ቀጥ ብሎ በሙሉ ኢማን እና ዒባዳ ወደ አላህ የሚሄድሰው ግን የለም፡፡ ሁሉም እያነከሠ ነው የሚሄደው፡፡ ሁሉም የጎደለው ነው፡፡ ሁሉም ደካማ ነው፡፡ ግማሽ ሶላት፣ ግማሽ ፆም፣ ግማሽ ዚክር፣ ግማሽ ቁርኣን… ይዘን ነው የምንሄደው፡፡ የደከመ፣ የሰነፈ፣ የሰባበረ የቂን ነው ያለን።

ባይደርስ እንኳን ወደርሱ የሚሄድን አላህ ባርያ አይመልስም፡፡ እንሄዳለን፡፡አላህ ይርዳን ።…


https://t.me/MuhammedSeidAbx


Forward from: ABX
ጌትዬዋ
አታድክመን አበርታን
አታስንፈን አጀግነን።

ጁምዓ ከዐስር በኋላ ፀሐይ እስክትጠልቅ ደረስ ። ውድ ከሆኑ፣ ዱዓና ኢስቲግፋር ከሚወደድባቸው ጊዜያቶች አንዱ።
አንዳንድ ጊዜ እስቲ ቁጭ እያልን፣ ራሣችንን እየፈተሽን፣ ወደ ጌትዬዋ መለስ ቀለስ እያልን ...

መሳአል ኸይር

https://t.me/MuhammedSeidAbx


Video is unavailable for watching
Show in Telegram


أكرمتني فلك الحمد، وسترتني فلك الحمد، ورزقتني فلك الحمد، وعافيتني فلك الحمد.. لك الحمد حبًا وشكرًا، ولك الحمد يومًا وعمرًا، ولك الحمد دائمًا وأبدًا.. لك الحمد حتى ترضى، ولك الحمد إذا رضيت، ولك الحمد بعد الرضا، ولك الحمد على كلِّ حال يا الله"


اللهم إني ظلمت نفسي ظلماً كثيراً ولا يغفر الذنوب إلا انت فاغفرلي مغفرة من عندك وارحمني إنك أنت الغفور الرحيم


“አሃምየቱል ወቅቲ ፊሃያቲል ሙስሊም”
በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ወቅታውይ ምክር።


https://t.me/bilQURANnehyaa


Forward from: ABX
ማታ ላይ ከመተኛቷ በፊት ስትኳካል አይተዋት
"ምንድነው በእንቅልፍ ሰዓት እንዲህ የምትቀባቢው?" አሏት።
"አስከሬን እያበጃጀሁ፤ ለገናዦቼ ሥራ እያቃለልኩ ነው " አለች አሉ አንዷ እብድ።

ሰው ማለት ምድር ላይ የሚንቀሳቀስ፣ ቀኑን የሚጠብቅ ሙት ነው። የጊዜ ጉዳይ እንጂ አስከሬን ነው።

የድንገተኛ ሞት መብዛት ነገር ብዙ በእጅጉ ሊያሳስበን የሚገባበት ዘመን ላይ ነን ።

ማታ አልጋ ላይ ተኝተን ጠዋት መቃብር ውስጥ ራሣችንን ልናገኝ እንችላለን።

አስከሬን ነንና ዉዱእ አድርገን፣ በልቦናም ንፁህ ሆነን፣
አዝካሮችን አድርገን፣
የምድር ላይ የመጨረሻ ንግግራችንን አሳምረን እንተኛ።

ቲስበሑ

https://t.me/MuhammedSeidAbx


አምላካችን ሆይ ሶላትን ግዴታነቷን አስበን ሳይሆን አንተን ወደንና አፍቅረን የምንፈጽማት አድርገን።

የአላህ መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ.) እንዲህ ማለታቸው ተዘግቧል -

‹አንድ ባሪያ ለሶላት የቆመ እንደሆነ ወንጀሉ ሁሉ እንዲመጣ ተደርጎ በትከሻው ላይ ይደረጋል፡፡ ሩኩዕ እና ሱጁድ ባደረገ ቁጥር ደግሞ (ወንጀሎቹ) ከርሱ ይረግፋሉ፡፡›

ሶባሐል ኸይር

https://t.me/MuhammedSeidAbx


للهم صل وسلم وبارك عليه، عدد خلقك.. ورضا نفسك، وزنة عرشك، ومداد كلماتك، اللهم صل وسلم وبارك عليه عدد ما خلقت، وعدد ما رزقت، وعدد ما أحييت، وعدد ما أمت.
اللهم صل وسلم وبارك عليه في كل وقت وحين، وفي كل ملة ودين، وفي العالمين إلى يوم الدين .
اللهم صل وسلم وبارك عليه كلما ذكرك الذاكرون، وكلما غفل عن ذكرك الغافلون، و عدد من صلى عليه ، وعدد من لم يصل عليه، وعدد أوراق الأشجار، وعدد مياه البحار، وعدد ما أظلم عليه الليل وما أضاء عليه النهار.


Forward from: ABX
ሁሌም ቢሆን ለራሣችሁ ሥምና ክብር ቅድሚያ ስጡ፡፡
ከማይመጥናችሁ ቦታ በክብር የመልቀቅ ልምድ ይኑራችሁ።
ዉስጣችሁን በልቶ በሚጨርስ ግንኙነት ላይ ሙጭጭ አትበሉ።
ለማይሻሻልና ለማይግገባው ሰው ተደጋጋሚ ዕድል አትስጡ፡፡
ወዳጄ!
ነፍስህን ታከብራት ዘንድ ባንተ ላይ ሐቅ አላት።
ልትንከባከባት፣ ዕረፍት ልትሠጣት፣ ከክፉ ሰው ልታርቃት፣ ከሚያዋርዳት ሰው እና ቦታ ሁሉ ልታገልላት ግድ ይላል፡፡

https://t.me/MuhammedSeidAbx




Forward from: Venue
« ብዙ ሰዎች የተውበት(ንሰሀ) ትልቅነት ገና በደንብ በጥልቀት አልተረዱም። የተውበትን ትልቅነት ለወሬ ማድመቅያ፣ ለስብከቶች አፍ መሟሻ ከማዋል በዘለለ እውነተኛ ተውበት ያደረጉትን ለማክበር እና ለመቀበል ብዙ ሰው ያመነታል።
እረፉ ተውበት አይናቅም። ብታውቁ ተውበትን አለማክብር የአላህን ቀደር መሟገት ነው።
እናንተ ወደ አላህ ተመላሾች ሆይ ሁሉም ሰዎች ተውበታችሁን ባይቀበሉ አትዘኑ። የተውበትን ትልቅነት፣ ልቅና የሚያውቁት እነዝያ የአላህን እዝነት የተረዱት እንጂ እውነቱን የማይነሩት አይደሉም።
የአላህ ባሮችን ተውበት የምትንቅ ልብ ወየውላት! ወደ አላህ የተመለሱ ሰዎችን ተውበት የምታጣጥል ነፍስ የአላህን ቀደር እያስተባበለች እንደሆነ ትወቅ! »
[ አብዱልሀኪም ሰፋ ]
:
@Venuee13
@Venuee13

20 last posts shown.