በትግራይ ክልል የአክሱም ወረዳ ፍርድ ቤት ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ሂጃብ እንዳይለብሱ የሚከለክለውን መመሪያ ትናንት ማገዱን የሙስሊም ዜና ምንጮች ዘግበዋል። ከትምህርት የታገዱ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታቸው እንዲመለሱ ያዘዘው ፍርድ ቤቱ፣ በሂጃብ ምክንያት ተማሪዎችን ከትምህርት ገበታ ያገዱ ትምህርት ቤቶችም ጥር 16 ፍርድ ቤት ቀርበው ቃላቸውን እንዲሠጡ ማዘዙን ዘገባዎቹ ጠቅሰዋል። የክልሉ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት እገዳው እንዲነሳ ክስ መመስረቱን ባለፈው ሳምንት ገልጦ ነበር።
Via Brook News
Source Wazema
Via Brook News
Source Wazema