TGStat
TGStat
Type to search
Advanced channel search
  • flag English
    Site language
    flag Russian flag English flag Uzbek
  • Sign In
  • Catalog
    Channels and groups catalog Search for channels
    Add a channel/group
  • Ratings
    Rating of channels Rating of groups Posts rating
    Ratings of brands and people
  • Analytics
  • Search by posts
  • Telegram monitoring
Brook News ብሩክ ኒዉስ

15 Mar, 11:25

Open in Telegram Share Report

Prev Next
የትግራይ ክልል ነዋሪዎች በፍርሀት ክልሉን ለቀው ለመሸሽ እያሰቡ መሆኑን ኤኤፍፒ ዘግቧል‼️
በአቶ ጌታቸው ረዳ ጊዜያዊ አስተዳደርና በህወሀት ሊቀመንበር ዶክተር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል መካከል የተፈጠረው የስልጣን ሽኩቻ ወደ ውጥረት መሻገሩን የጠቀሰው ዘገባው አንደኛው አንጃ በመቀሌ የሚገኘውን ማዘጋጃ ቤት መቆጣጠሩን አስታውቋል፡፡

አንድ ስሙ እንዳይጠቀስ የፈለገ የመቀሌ ዩኒቨርስቲ መምህር ለዜና አውታሩ ሲናገር ‹‹አሁን ህዝቡ ጦርነት ከተቀሰቀሰ ካለፈው የከፋ ሁኔታ ሊያጋጥም ይችላል በሚል ስጋት ላይ ነው›› ብሏል፡፡ ሌላ ነዋሪ ደግሞ ህዝቡ ክልሉን ጥሎ ለመሸሽ ጥረት በማድረግ ላይ መሆኑን ገልፃለች፡፡ ምህረት የተባለችው ይህች የ27 አመት ወጣት ስትናገር ‹‹ባለፈው ጦርነት ጊዜ በመቀሌ ውስጥ ታሽገን ነበር፡፡ አሁን ያ እንዲደገም አንፈልግም፡፡›› ብላለች፡፡

ጨምራም ‹‹አሁን ክልሉን ለቀን ለመውጣት ጥረት እያደረግን ነው፡፡ ነገር ግን የአውሮፕላን ትኬት ለመቁረጥ ስንፈልግ ሰሞኑን ያሉት በረራዎች የሞሉ መሆኑን ለማወቅ ችለናል፡፡ ስለዚህም ክልሉን ለመልቀቅ ሌሎች አማራጮችን እየፈለግን ነው›› በማለት አስረድታ ነዋሪው በፍርሀት ውስጥ እንደሚገኝ ገልፃለች፡፡

እንደኤኤፍፒ ዘገባ የደብረፅዮን አንጃ የመቀሌ ከተማን ማዘጋጃ ቤት ትላንት የተቆጣጠረ ሲሆን የራሱን ከንቲባም ሾሟል፡፡ እንዲሁም በመቀሌ የሚገኘውን የኤፍኤም ሬዲዮ ጣቢያ በቁጥጥሩ ስር አስገብቷል፡፡ የዶክተር ደብረፅዮን ቃል አቀባይ ለዜና አውታሩ ሲናገሩ ‹‹ቀደም ሲል ተመርጠው የነበሩት ከንቲባ በአቶ ጌታቸው ረዳ ተባረው ነበር፡፡ ያ ደግሞ ህጋዊ አልነበረም፡፡ ስለዚህም አሁን እኚያን ከንቲባ መልሰን ሾመናቸዋል›› ብለዋል፡፡
Via- አዩ ዘ ሀበሻ

25.7k 0 14 152
Catalog
Channels and groups catalog Channels compilations Search for channels Add a channel/group
Ratings
Rating of Telegram channels Rating of Telegram groups Posts rating Ratings of brands and people
API
API statistics Search API of posts API Callback
Our channels
@TGStat @TGStat_Chat @telepulse @TGStatAPI
Read
Blog Telegram Research 2019 Telegram Research 2021 Telegram Research 2023
Contacts
Support Email Jobs
Miscellaneous
Terms and conditions Privacy policy Public offer
Our bots
@TGStat_Bot @SearcheeBot @TGAlertsBot @tg_analytics_bot @TGStatChatBot