ፌስቡክ የ20 አመት ጉዞ፤ ከዶርም እስከ 3 ቢሊየን ተጠቃሚ
የሃርቫርድ ዩኒቨርሲቲ የኮምፒውተር ሳይንስ ተማሪው ማርክ ዙከርበርግ ከጓደኞቹ ጋር በመሆን የሰራው የማህበራዊ ትስስር ገጽ ፌስቡክ ትናንት 20 አመት ደፍኗል።
ዙከርበርግ ከፌስቡክ በፊት ከሃርቫርድ ዩኒቨርሲቲ ሴቶች ውቧ የትኛዋ ናት የሚልና ተማሪዎች አስተያየት የሚሰጡበት “ፌስማሽ” የተሰኘ ድረገጽ አስተዋውቆ ነበር።
የ19 አመቱ ዙከርበርግ የዩኒቨርሲቲውን የመረጃ ስርአት ሰብሮ የሴት ተማሪዎችን ፎቶ ከመታወቂያቸው ላይ በመውሰድ የሰራው ድረገጽ ወዲያውኑ በመዘጋቱም “ዘፌስቡክ”ተወለደ።
ዙከርበርግና ጓደኞቹ ለሃርቫርድ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የሰሩት ፌስቡክ አለም ሲያዳርስ ግን ጊዜ አልፈጀበትም።
በአሁኑ ወቅት በወር ከ3 ቢሊየን በላይ ተጠቃሚ ያለው ፌስቡክ፥ ተቀባይነቱ እያደገ እንዲሄድ በየጊዜው ማሻሻያዎችን ማድረጉ ይታወቃል።
በሁለት አስርት አመት ጉዞውም ከካምብሪጅ አናሊይቲካ ቅሌት እስከ ምርጫ ጣልቃገብነት በመረጃ አያያዙ በርካታ ክሶች ሲቀርቡበት ቆይተዋል።
የሃርቫርድ ዩኒቨርሲቲ የኮምፒውተር ሳይንስ ተማሪው ማርክ ዙከርበርግ ከጓደኞቹ ጋር በመሆን የሰራው የማህበራዊ ትስስር ገጽ ፌስቡክ ትናንት 20 አመት ደፍኗል።
ዙከርበርግ ከፌስቡክ በፊት ከሃርቫርድ ዩኒቨርሲቲ ሴቶች ውቧ የትኛዋ ናት የሚልና ተማሪዎች አስተያየት የሚሰጡበት “ፌስማሽ” የተሰኘ ድረገጽ አስተዋውቆ ነበር።
የ19 አመቱ ዙከርበርግ የዩኒቨርሲቲውን የመረጃ ስርአት ሰብሮ የሴት ተማሪዎችን ፎቶ ከመታወቂያቸው ላይ በመውሰድ የሰራው ድረገጽ ወዲያውኑ በመዘጋቱም “ዘፌስቡክ”ተወለደ።
ዙከርበርግና ጓደኞቹ ለሃርቫርድ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የሰሩት ፌስቡክ አለም ሲያዳርስ ግን ጊዜ አልፈጀበትም።
በአሁኑ ወቅት በወር ከ3 ቢሊየን በላይ ተጠቃሚ ያለው ፌስቡክ፥ ተቀባይነቱ እያደገ እንዲሄድ በየጊዜው ማሻሻያዎችን ማድረጉ ይታወቃል።
በሁለት አስርት አመት ጉዞውም ከካምብሪጅ አናሊይቲካ ቅሌት እስከ ምርጫ ጣልቃገብነት በመረጃ አያያዙ በርካታ ክሶች ሲቀርቡበት ቆይተዋል።