ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የተሰጠ መግለጫ
የኢትዮዽያ ንግድ ባንክ ለመንግስት አንድም ብር አበድሮ አያውቅም!
********************************
የኢትዮዽያ ንግድ ባንክ በዚህ በጀት ዓመትም ሆነ ከዚያ በፊት አንድም ብር ለመንግስት በቀጥታ አበድሮ አያውቅም። መንግስት ከሀገር ውስጥ የንግድ ባንኮች (በብሔራዊ ባንክ በኩል ለሽያጭ ከሚቀርበው የግምጃ ቤት ሰነድ ግዢ ውጪ) በቀጥታ የመበደር አሰራርም ሆነ ልምድ የለውም። ሀቁ ይህ ሆኖ ሳለ የኢትዮዽያ ንግድ ባንክ በዚህ በተገባደደው ሳምንት ለኢ.ፌ.ዲ.ሪ. የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት የልማት ድርጅቶች ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የስምንት ወራት የስራ አፈጻጸም ማቅረባችንን ተንተርሶ በሪፓርተር ጋዜጣ የዕሁድ ዕትም ቅጽ 30 ቁጥር 2602 መጋቢት 28 ቀን 2017 ዓ.ም. ታትሞ የተሰራጨው ዜና ከርዕሱ ጀምሮ ለቋሚ ኮሚቴው ከቀረበው ሪፖርትም ሆነ ከእውነታው የተለየና የተዛባ መረጃ ሆኖ አግኝተነዋል። ለምሳሌ በጋዜጣው ዕትም ርዕስ ላይ የተገለጸውና “̋መንግስት ከኢትዮዽያ ንግድ ባንክ የተበደረው አንድ ትሪሊየን ዕዳ እንዳለበት ተገለጸ” የተባለው ዜና ከእውነት የራቀ ከመሆኑም በላይ በሪፖርቱም ፈጽሞ እንደዚህ አይነት ኃሳብ አልቀረበም።
“ባለፉት 15 ዓመታት 92 በመቶ ብድር የተሰጠው ለመንግስት ተቋማት ነው ተብሏል” የሚለው ኃሳብም ስህተት ነው። የቀረበው ሪፖርት በግልጽ እንደሚያሳየው ከለውጡ በፊት የባንካችን የብድር ትኩረት ለመንግስት ተቋማት እንደነበርና ይህ ብድር አድጎ በመጨረሻም ከአምስት ዓመት በፊት እስከ 92% እንደደረሰ እና ከአምስት ዓመት ወዲህ ግን ያ አሰራር የተቀየረና ቅድሚያ ለግል ተበዳሪዎች እየተሰጠ በመሆኑ ፤ ለምሳሌ ያህል በዚህ ስምንት ወራት ከተሰጠው ጠቅላላ ብር 264.65 ቢሊዮን ብድር ውስጥ ከ88% በላይ ብድር የተሰጠው ለግሉ ዘርፍ በመሆኑ አሁን ያለው የመንግስት ተቋማት የብድር ክምችት ድርሻ ወደ 72% ዝቅ ማለቱን ተመላክቷል።
በመሰረቱ ይህ የመንግስት የልማት ድርጅቶች ዕዳ መንግስት በቀጥታ ራሱ የተበደረው የመንግስት ዕዳ ሳይሆን የተለያዩ እንደ ባንካችን ያሉ የመንግስት የልማት ድርጅቶች የተበደሩት ዕዳ ነው። መንግስት በእነኚህ የመንግስት የልማት ድርጅቶች ውስጥ የባለቤትነት ድርሻ ቢኖረውም እነዚህ ተቋማት ከአስፈፃሚው መንግስት የተለዩና የራሳቸው ካፒታል ያላቸው፣ እንደ ማንኛውም ድርጅት ንግድ ፍቃድ አውጥተው የሚነግዱ፣ በድርጅታቸው ስም ገንዘብ የሚበደሩ፣ ሊያተርፉም ሆነ ሊከስሩ የሚችሉ፣ ለትርፍ የተቋቋሙ የልማት ድርጅቶች ሲሆኑ ብድሮቹንም የወሰዱት ለራሳቸው ፕሮጀክቶች በመሆኑ ለእነዚህ ተቋማት የተሰጠውን ብድር የመንግስት ብድር ተደርጎ መወሰዱ ስህተት ነው። በሀገሪቱ የማክሮ ኢኮኖሚ አስተዳደር መሰረት መንግስት ማንኛውም ዓይነት የአጭርም ሆነ የረጅም ግዜ የገንዘብ ፍላጎቱን በሕግ በተቀመጠው አሰራርና ምንጭ ያሟላል እንጂ ከሀገር ውስጥ የንግድ ባንኮች በቀጥታ ብድር የሚወስድበት አግባብ የለም።
ትክክለኛው እውነታ ይህ ሆኖ እያለ አንዳንድ የመገናኛ ብዙኃን ዕዳውን መንግስት በቀጥታ የተበደረው ዕዳ እንደሆነ አድርገው በሪፖርተር ጋዜጣም ሆነ ጋዜጣውን ተከትለው በወጡ አንዳንድ የሚዲያ አካላትም መረጃውን በተዛባና በተሳሳተ መልኩ መዘገባቸው ከባንካችን መግለጫ አውድ ውጭ የቀረበ ከመሆኑም በላይ የጋዜጣው ርዕስ በውስጡ ከተጻፉት ኃሳቦች ጋርም ያልተጣጣመ መሆኑ አንባቢያንን ግራ ሊያጋባ እንደሚችል ስለሰጋን እውነታውን ለማሳወቅ ተገደናል።
በጋዜጣው በጉልህ ከተገለጸው በተቃራኒ መንግስት የልማት ድርጅቶች ከባንካችን የተበደሩትንና ለበርካታ ዓመታት ሳይከፍሉ የቆዩትን ከፍተኛ የብድር ገንዘብ በባንካችን ላይ የደቀነውን አደጋ በመገንዘብ የሚከተሉትን እርምጃዎች በመውስድ ባንካችንን ከውድቀት ታድጎታል።
1ኛ. የልማት ድርጅቶቹ ከባንካችን ብድሩን የሚወስዱበት አሰራር አመላለሱን የሚያረጋግጥ ስላልነበረ ይህ አሰራር ሙሉ በሙሉ እንዲቀርና ባንካችን የውሳኔ ነጻነት እንዲኖረው ለመንግስት ተቋማትም ቢሆን አዋጭ የንግድ ኃሳብ ለሚያቀርቡና ባንካችን ስለአመላለሱ እርግጠኛ ለሆነባቸው ብቻ ብድር እንዲሰጥ አቅጣጫ የተቀመጠው ከ5 ዓመት በፊት ነው። ይህ ብቻ ሳይሆን ቅድሚያ ለግል ተበዳሪዎች እንዲሰጥ እና የመንግስት የልማት ድርጅቶችም ቀድመው የጀመሩትን ፕሮጀክቶች ሳይጨርሱ ሌላ እንዳይጀምሩ ስለተደረገ ከ5 ዓመት በፊት 92% ደርሶ የነበረው የመንግስት ተቋማት አጠቃላይ የብድር ድርሻ ወደ 72% በአጭር ጊዜ ውስጥ ዝቅ ማለቱ እና የግሉ ተበዳሪዎች ድርሻ ደግሞ ከ8% ወደ 28% በፍጥነት ማደጉ ከፍተኛ ስኬት ሆኖ የቀረበና አንባቢያን ሊያውቁት የሚገባው ጥሬ ሀቅ ነው።
2ኛ. የልማት ድርጅቶቹ በወቅቱ መመለስ ያልቻሉትን ዕዳ በተመለከተ ደግሞ፡-
ሀ. መጀመሪያ የመንግስት ዕዳ እና ኃብት አስተዳዳሪ ድርጅት በማቋቋም እዳዎቹን እንዲከፍል ከፍተኛ ጥረት ተደርጓል። በዚህ ጥረትም ከብር 42.4 ቢሊዮን በላይ እንዲከፈል ተደርጓል።
ለ. ችግሩ በዕዳና ሀብት አስተዳደር ድርጅት ጥረትም ሊፈታ እንደማይችል በመረጋገጡ በዚህ የበጀት ዓመት መጀመሪያ ላይ አጠቃላይ የአከፋፈል ችግር የገጠመው የመንግስት የልማት ድርጅቶች የብር 845.3 ቢሊዮን ዕዳ ተሰባስቦ ወደ ገንዘብ ሚኒስቴር እንዲዞር እና በየዓመቱ በጀት ተይዞለት እና በአስተማማኝ ሁኔታ እንዲከፈል ለዚህም ተመጣጣኝ የመንግስት ቦንድ ለባንካችን እንዲሰጥ በፓርላማ ጭምር በማጸደቅ ኃላፊነት የሚሰማውና ቆራጥ መንግስት ብቻ የሚፈጽመው ታሪክ በመስራት ባንካችንን ከውድቀት ኢኮኖሚያችንንም ከትልቅ አደጋ ያዳነ እርምጃ በመውሰዱ መንግስታችንን እጅግ በጣም አመስግነናል፤ አሁንም እጅግ በጣም እናመሰግናለን። ከዚሁ ከተዛወረው ዕዳ ላይ ደግሞ በስምምነቱ መሰረት የመጀመሪያ የግማሽ ዓመት ወለድ በጥር ወር መጀመሪያ ላይ በገንዘብ ሚኒስቴር በኩል ብር 38 ቢሊዮን ለባንካችን ተከፍሏል። ስለዚህ መንግስት ባንካችንን ለማዳን ሲል ከልማት ድርጅቶች ተቀብሎ መክፈል ከጀመረው ዕዳ ውጪ የተበደረው ምንም ገንዘብ እንደሌለ ለሕዝባችን ማሳወቅ እንፈልጋለን።
3ኛ. መንግስት ከልማት ድርጅቶች ከተረከበው ከፍተኛ ዕዳ በተጨማሪ ባንካችንን ለማጠናከር የብር 54.7 ቢሊዮን የካፒታል ጭማሪ በማድረግ ከላይ ከተገለጸው የድርጅቶች ዕዳ ጋር ተደምሮ ብር 900 ቢሊዮን የመንግስት ቦንድ እንዲሰጠን በማድረጉም ባንካችንን ሊገጥሙት የሚችሉትን የፋይናንሻል ስጋቶችን መቋቋም ብቻ ሳይሆን ጠንካራ እና ተወዳዳሪ ባንክ እንዲሆን ረድቶታል።
4ኛ. መንግስት ባንካችንን የበለጠ ለማጠናከር ከዓለም ባንክ ጋር በመተባበር ላለፉት አምስት ዓመታት ጥልቅ ሪፎርም እንድናደርግ ከፍተኛ ድጋፍ እና አመራር የሰጠን ሲሆን የባንካችን ካፒታል የበለጠ እንዲጠናከርና የውጪ ምንዛሬ ፍላጎታችንን ለማሟላት ያለመ 650 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር የካፒታል ማሳደጊያ ድጋፍ እንድናገኝ በማድረጉ ባንካችንን የበለጠ የሚያገዝፈው እና የማይበገር ጠንካራ ተወዳዳሪ የሚያደርገው የመንግስታችን ልዩ ድጋፍ በመሆኑ ባንካችን አሁንም አብዝቶ ያመሰግናል።
እንግዲህ እውነታው ይህ ሆኖ ሳለ በስብሰባው ላይ የቀረቡትና ሕዝባችን ሊያውቃቸው የሚገቡ ብዙ መልካም ዜናዎች እያሉ ያለመታደል ሆኖ አሉታዊ ዜና የመናፈቅ ችግር ጎልቶ በታየበት አኳኋን ሪፖርተርም ሆነ ሌሎች ጥቂት ሚዲያዎች የባንካችንን እጅግ በጣም አንጸባራቂ የስምንት ወራት አፈጻጸም ላይ ጥላሸት ለመቀባት መሞከራቸው አሳዛኝ ተግባር ሆኖ አግኝተ
የኢትዮዽያ ንግድ ባንክ ለመንግስት አንድም ብር አበድሮ አያውቅም!
********************************
የኢትዮዽያ ንግድ ባንክ በዚህ በጀት ዓመትም ሆነ ከዚያ በፊት አንድም ብር ለመንግስት በቀጥታ አበድሮ አያውቅም። መንግስት ከሀገር ውስጥ የንግድ ባንኮች (በብሔራዊ ባንክ በኩል ለሽያጭ ከሚቀርበው የግምጃ ቤት ሰነድ ግዢ ውጪ) በቀጥታ የመበደር አሰራርም ሆነ ልምድ የለውም። ሀቁ ይህ ሆኖ ሳለ የኢትዮዽያ ንግድ ባንክ በዚህ በተገባደደው ሳምንት ለኢ.ፌ.ዲ.ሪ. የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት የልማት ድርጅቶች ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የስምንት ወራት የስራ አፈጻጸም ማቅረባችንን ተንተርሶ በሪፓርተር ጋዜጣ የዕሁድ ዕትም ቅጽ 30 ቁጥር 2602 መጋቢት 28 ቀን 2017 ዓ.ም. ታትሞ የተሰራጨው ዜና ከርዕሱ ጀምሮ ለቋሚ ኮሚቴው ከቀረበው ሪፖርትም ሆነ ከእውነታው የተለየና የተዛባ መረጃ ሆኖ አግኝተነዋል። ለምሳሌ በጋዜጣው ዕትም ርዕስ ላይ የተገለጸውና “̋መንግስት ከኢትዮዽያ ንግድ ባንክ የተበደረው አንድ ትሪሊየን ዕዳ እንዳለበት ተገለጸ” የተባለው ዜና ከእውነት የራቀ ከመሆኑም በላይ በሪፖርቱም ፈጽሞ እንደዚህ አይነት ኃሳብ አልቀረበም።
“ባለፉት 15 ዓመታት 92 በመቶ ብድር የተሰጠው ለመንግስት ተቋማት ነው ተብሏል” የሚለው ኃሳብም ስህተት ነው። የቀረበው ሪፖርት በግልጽ እንደሚያሳየው ከለውጡ በፊት የባንካችን የብድር ትኩረት ለመንግስት ተቋማት እንደነበርና ይህ ብድር አድጎ በመጨረሻም ከአምስት ዓመት በፊት እስከ 92% እንደደረሰ እና ከአምስት ዓመት ወዲህ ግን ያ አሰራር የተቀየረና ቅድሚያ ለግል ተበዳሪዎች እየተሰጠ በመሆኑ ፤ ለምሳሌ ያህል በዚህ ስምንት ወራት ከተሰጠው ጠቅላላ ብር 264.65 ቢሊዮን ብድር ውስጥ ከ88% በላይ ብድር የተሰጠው ለግሉ ዘርፍ በመሆኑ አሁን ያለው የመንግስት ተቋማት የብድር ክምችት ድርሻ ወደ 72% ዝቅ ማለቱን ተመላክቷል።
በመሰረቱ ይህ የመንግስት የልማት ድርጅቶች ዕዳ መንግስት በቀጥታ ራሱ የተበደረው የመንግስት ዕዳ ሳይሆን የተለያዩ እንደ ባንካችን ያሉ የመንግስት የልማት ድርጅቶች የተበደሩት ዕዳ ነው። መንግስት በእነኚህ የመንግስት የልማት ድርጅቶች ውስጥ የባለቤትነት ድርሻ ቢኖረውም እነዚህ ተቋማት ከአስፈፃሚው መንግስት የተለዩና የራሳቸው ካፒታል ያላቸው፣ እንደ ማንኛውም ድርጅት ንግድ ፍቃድ አውጥተው የሚነግዱ፣ በድርጅታቸው ስም ገንዘብ የሚበደሩ፣ ሊያተርፉም ሆነ ሊከስሩ የሚችሉ፣ ለትርፍ የተቋቋሙ የልማት ድርጅቶች ሲሆኑ ብድሮቹንም የወሰዱት ለራሳቸው ፕሮጀክቶች በመሆኑ ለእነዚህ ተቋማት የተሰጠውን ብድር የመንግስት ብድር ተደርጎ መወሰዱ ስህተት ነው። በሀገሪቱ የማክሮ ኢኮኖሚ አስተዳደር መሰረት መንግስት ማንኛውም ዓይነት የአጭርም ሆነ የረጅም ግዜ የገንዘብ ፍላጎቱን በሕግ በተቀመጠው አሰራርና ምንጭ ያሟላል እንጂ ከሀገር ውስጥ የንግድ ባንኮች በቀጥታ ብድር የሚወስድበት አግባብ የለም።
ትክክለኛው እውነታ ይህ ሆኖ እያለ አንዳንድ የመገናኛ ብዙኃን ዕዳውን መንግስት በቀጥታ የተበደረው ዕዳ እንደሆነ አድርገው በሪፖርተር ጋዜጣም ሆነ ጋዜጣውን ተከትለው በወጡ አንዳንድ የሚዲያ አካላትም መረጃውን በተዛባና በተሳሳተ መልኩ መዘገባቸው ከባንካችን መግለጫ አውድ ውጭ የቀረበ ከመሆኑም በላይ የጋዜጣው ርዕስ በውስጡ ከተጻፉት ኃሳቦች ጋርም ያልተጣጣመ መሆኑ አንባቢያንን ግራ ሊያጋባ እንደሚችል ስለሰጋን እውነታውን ለማሳወቅ ተገደናል።
በጋዜጣው በጉልህ ከተገለጸው በተቃራኒ መንግስት የልማት ድርጅቶች ከባንካችን የተበደሩትንና ለበርካታ ዓመታት ሳይከፍሉ የቆዩትን ከፍተኛ የብድር ገንዘብ በባንካችን ላይ የደቀነውን አደጋ በመገንዘብ የሚከተሉትን እርምጃዎች በመውስድ ባንካችንን ከውድቀት ታድጎታል።
1ኛ. የልማት ድርጅቶቹ ከባንካችን ብድሩን የሚወስዱበት አሰራር አመላለሱን የሚያረጋግጥ ስላልነበረ ይህ አሰራር ሙሉ በሙሉ እንዲቀርና ባንካችን የውሳኔ ነጻነት እንዲኖረው ለመንግስት ተቋማትም ቢሆን አዋጭ የንግድ ኃሳብ ለሚያቀርቡና ባንካችን ስለአመላለሱ እርግጠኛ ለሆነባቸው ብቻ ብድር እንዲሰጥ አቅጣጫ የተቀመጠው ከ5 ዓመት በፊት ነው። ይህ ብቻ ሳይሆን ቅድሚያ ለግል ተበዳሪዎች እንዲሰጥ እና የመንግስት የልማት ድርጅቶችም ቀድመው የጀመሩትን ፕሮጀክቶች ሳይጨርሱ ሌላ እንዳይጀምሩ ስለተደረገ ከ5 ዓመት በፊት 92% ደርሶ የነበረው የመንግስት ተቋማት አጠቃላይ የብድር ድርሻ ወደ 72% በአጭር ጊዜ ውስጥ ዝቅ ማለቱ እና የግሉ ተበዳሪዎች ድርሻ ደግሞ ከ8% ወደ 28% በፍጥነት ማደጉ ከፍተኛ ስኬት ሆኖ የቀረበና አንባቢያን ሊያውቁት የሚገባው ጥሬ ሀቅ ነው።
2ኛ. የልማት ድርጅቶቹ በወቅቱ መመለስ ያልቻሉትን ዕዳ በተመለከተ ደግሞ፡-
ሀ. መጀመሪያ የመንግስት ዕዳ እና ኃብት አስተዳዳሪ ድርጅት በማቋቋም እዳዎቹን እንዲከፍል ከፍተኛ ጥረት ተደርጓል። በዚህ ጥረትም ከብር 42.4 ቢሊዮን በላይ እንዲከፈል ተደርጓል።
ለ. ችግሩ በዕዳና ሀብት አስተዳደር ድርጅት ጥረትም ሊፈታ እንደማይችል በመረጋገጡ በዚህ የበጀት ዓመት መጀመሪያ ላይ አጠቃላይ የአከፋፈል ችግር የገጠመው የመንግስት የልማት ድርጅቶች የብር 845.3 ቢሊዮን ዕዳ ተሰባስቦ ወደ ገንዘብ ሚኒስቴር እንዲዞር እና በየዓመቱ በጀት ተይዞለት እና በአስተማማኝ ሁኔታ እንዲከፈል ለዚህም ተመጣጣኝ የመንግስት ቦንድ ለባንካችን እንዲሰጥ በፓርላማ ጭምር በማጸደቅ ኃላፊነት የሚሰማውና ቆራጥ መንግስት ብቻ የሚፈጽመው ታሪክ በመስራት ባንካችንን ከውድቀት ኢኮኖሚያችንንም ከትልቅ አደጋ ያዳነ እርምጃ በመውሰዱ መንግስታችንን እጅግ በጣም አመስግነናል፤ አሁንም እጅግ በጣም እናመሰግናለን። ከዚሁ ከተዛወረው ዕዳ ላይ ደግሞ በስምምነቱ መሰረት የመጀመሪያ የግማሽ ዓመት ወለድ በጥር ወር መጀመሪያ ላይ በገንዘብ ሚኒስቴር በኩል ብር 38 ቢሊዮን ለባንካችን ተከፍሏል። ስለዚህ መንግስት ባንካችንን ለማዳን ሲል ከልማት ድርጅቶች ተቀብሎ መክፈል ከጀመረው ዕዳ ውጪ የተበደረው ምንም ገንዘብ እንደሌለ ለሕዝባችን ማሳወቅ እንፈልጋለን።
3ኛ. መንግስት ከልማት ድርጅቶች ከተረከበው ከፍተኛ ዕዳ በተጨማሪ ባንካችንን ለማጠናከር የብር 54.7 ቢሊዮን የካፒታል ጭማሪ በማድረግ ከላይ ከተገለጸው የድርጅቶች ዕዳ ጋር ተደምሮ ብር 900 ቢሊዮን የመንግስት ቦንድ እንዲሰጠን በማድረጉም ባንካችንን ሊገጥሙት የሚችሉትን የፋይናንሻል ስጋቶችን መቋቋም ብቻ ሳይሆን ጠንካራ እና ተወዳዳሪ ባንክ እንዲሆን ረድቶታል።
4ኛ. መንግስት ባንካችንን የበለጠ ለማጠናከር ከዓለም ባንክ ጋር በመተባበር ላለፉት አምስት ዓመታት ጥልቅ ሪፎርም እንድናደርግ ከፍተኛ ድጋፍ እና አመራር የሰጠን ሲሆን የባንካችን ካፒታል የበለጠ እንዲጠናከርና የውጪ ምንዛሬ ፍላጎታችንን ለማሟላት ያለመ 650 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር የካፒታል ማሳደጊያ ድጋፍ እንድናገኝ በማድረጉ ባንካችንን የበለጠ የሚያገዝፈው እና የማይበገር ጠንካራ ተወዳዳሪ የሚያደርገው የመንግስታችን ልዩ ድጋፍ በመሆኑ ባንካችን አሁንም አብዝቶ ያመሰግናል።
እንግዲህ እውነታው ይህ ሆኖ ሳለ በስብሰባው ላይ የቀረቡትና ሕዝባችን ሊያውቃቸው የሚገቡ ብዙ መልካም ዜናዎች እያሉ ያለመታደል ሆኖ አሉታዊ ዜና የመናፈቅ ችግር ጎልቶ በታየበት አኳኋን ሪፖርተርም ሆነ ሌሎች ጥቂት ሚዲያዎች የባንካችንን እጅግ በጣም አንጸባራቂ የስምንት ወራት አፈጻጸም ላይ ጥላሸት ለመቀባት መሞከራቸው አሳዛኝ ተግባር ሆኖ አግኝተ