የአገራዊ ምክክሩ አራት አጀንዳዎች ከስምምነት ሳይደረስባቸው ወደ ቀጣይ ዙር ተሻገሩ❗❗
በአገራዊ ምክክሩ የመንግሥት አደረጃጀትን ጨምሮ አራት አከራካሪ ጉዳዮች በ120 አባላት ያለው የሐሳብ አዘጋጅ ቡድን ስምምነት ሳይደረስባቸው ወደ ቀጣዩ የምክክር ሂደት መሻገራቸው ተገለጸ።
በአጀንዳው 500 ተሳታፊዎች ባሉበት የሥራ ቡድን 53 ጉዳዮች ቀርበው፣ 50 ላይ ስምምነት ሲደረስ ሦስቱ ግን ሳይስማሙ እንደቀሩ ቀደም ሲል ተገልጿል። የሐሳብ አዘጋጅ ቡድኑ እነዚህን ጉዳዮች በማጣጣም 62 ምክረ ሐሳቦች አድርጎ ሲያቀርብ፣ አራቱ ላይ የጋራ ስምምነት ሊደረስ እንዳልቻለ ተሳታፊዎች ገልጸዋል።
ከእነዚህ መካከል ዋነኛው የመንግሥት አወቃቀር ጉዳይ ሲሆን፣ አንደኛው አማራጭ ፓርላሜንታዊ ሥርዓት እንዲኖርና ፕሬዚዳንቱ ከፓርላማ እንዲመረጥ የሚደግፍ ሲሆን፣ ሌላኛው ፕሬዚዳንታዊ ሥርዓት እንዲኖርና ፕሬዚዳንቱ በሕዝብ ቀጥታ እንዲመረጥ የሚል ነው።
ሌሎቹ ሁለት ጉዳዮች የፌዴሬሽን ምክር ቤት አባላት አመራረጥና በምክር ቤቱ የብሔረሰቦች ውክልና አሠራርን የሚመለከቱ ናቸው። በአባላት አመራረጥ ላይ አንዱ ሐሳብ አባላት በክልሎች ምክር ቤቶች እንዲመረጡ ሲደግፍ፣ ሌላው ሕዝቡ በቀጥታ እንዲመርጣቸው የሚል ነው።
በብሔረሰቦች ውክልና ላይም አንድ ሐሳብ በሕዝብ ብዛት መሠረት ተጨማሪ ውክልና እንዲኖር ሲደግፍ፣ ሌላው ሁሉም ብሔረሰቦች በእኩል መልኩ እንዲወከሉ የሚል ሐሳብ ቀርቧል።
አራተኛው አከራካሪ ጉዳይ “ውህድ ማንነት” የሚለው ሐሳብ ሲሆን፣ የሥራ ቡድኑ ቀደም ሲል በስምምነት አልፎ የነበረው ሐሳብ በ120 አባላት ባለው የሐሳብ አዘጋጅ ቡድን ዳግም የአለመስማማት ጉዳይ ሆኗል። በጉዳዩ ላይ ከፍተኛ ተቃውሞ መቅረቡንና ከስምምነት ይልቅ አለመስማማት በሚል ወደ ቀጣዩ ዙር መተላለፉን ተሳታፊዎች ገልጸዋል።
በመሆኑም አራቱ ጉዳዮች በቀጣዩ የምክክር ዙር የበለጠ ውይይትና የመግባባት ሥራ የሚያስፈልጋቸው ጉዳዮች ሆነው መቀጠላቸው ታውቋል።
@darashMedia
@darashMedia
በአገራዊ ምክክሩ የመንግሥት አደረጃጀትን ጨምሮ አራት አከራካሪ ጉዳዮች በ120 አባላት ያለው የሐሳብ አዘጋጅ ቡድን ስምምነት ሳይደረስባቸው ወደ ቀጣዩ የምክክር ሂደት መሻገራቸው ተገለጸ።
በአጀንዳው 500 ተሳታፊዎች ባሉበት የሥራ ቡድን 53 ጉዳዮች ቀርበው፣ 50 ላይ ስምምነት ሲደረስ ሦስቱ ግን ሳይስማሙ እንደቀሩ ቀደም ሲል ተገልጿል። የሐሳብ አዘጋጅ ቡድኑ እነዚህን ጉዳዮች በማጣጣም 62 ምክረ ሐሳቦች አድርጎ ሲያቀርብ፣ አራቱ ላይ የጋራ ስምምነት ሊደረስ እንዳልቻለ ተሳታፊዎች ገልጸዋል።
ከእነዚህ መካከል ዋነኛው የመንግሥት አወቃቀር ጉዳይ ሲሆን፣ አንደኛው አማራጭ ፓርላሜንታዊ ሥርዓት እንዲኖርና ፕሬዚዳንቱ ከፓርላማ እንዲመረጥ የሚደግፍ ሲሆን፣ ሌላኛው ፕሬዚዳንታዊ ሥርዓት እንዲኖርና ፕሬዚዳንቱ በሕዝብ ቀጥታ እንዲመረጥ የሚል ነው።
ሌሎቹ ሁለት ጉዳዮች የፌዴሬሽን ምክር ቤት አባላት አመራረጥና በምክር ቤቱ የብሔረሰቦች ውክልና አሠራርን የሚመለከቱ ናቸው። በአባላት አመራረጥ ላይ አንዱ ሐሳብ አባላት በክልሎች ምክር ቤቶች እንዲመረጡ ሲደግፍ፣ ሌላው ሕዝቡ በቀጥታ እንዲመርጣቸው የሚል ነው።
በብሔረሰቦች ውክልና ላይም አንድ ሐሳብ በሕዝብ ብዛት መሠረት ተጨማሪ ውክልና እንዲኖር ሲደግፍ፣ ሌላው ሁሉም ብሔረሰቦች በእኩል መልኩ እንዲወከሉ የሚል ሐሳብ ቀርቧል።
አራተኛው አከራካሪ ጉዳይ “ውህድ ማንነት” የሚለው ሐሳብ ሲሆን፣ የሥራ ቡድኑ ቀደም ሲል በስምምነት አልፎ የነበረው ሐሳብ በ120 አባላት ባለው የሐሳብ አዘጋጅ ቡድን ዳግም የአለመስማማት ጉዳይ ሆኗል። በጉዳዩ ላይ ከፍተኛ ተቃውሞ መቅረቡንና ከስምምነት ይልቅ አለመስማማት በሚል ወደ ቀጣዩ ዙር መተላለፉን ተሳታፊዎች ገልጸዋል።
በመሆኑም አራቱ ጉዳዮች በቀጣዩ የምክክር ዙር የበለጠ ውይይትና የመግባባት ሥራ የሚያስፈልጋቸው ጉዳዮች ሆነው መቀጠላቸው ታውቋል።
@darashMedia
@darashMedia