✍የሴት ልጅ መብት በእስልምና
➊ "ሴትን ልጅ የሚያልቅ ሰው የለም እርሱ የላቀና የተከበረ ሰው ቢሆን እንጂ ሴትን የሚያዋርድ ሰው የለም እርሱ የተዋረደ ሰው ቢሆን እንጂ።" ረሱል ﷺ
➋ ‹‹ስለ ሚስቱ የተገደለ ሰው ሰማዕት (ሸሂድ) ነው፡፡›› (አል ቲርሚዚ 1421/ አቡ ዳውድ 4772)
➌ በአንድ ወቅት አንድ ሰው ወደ ነቢዩ ﷺ ዘንድ መጣና "ልወዳጀው ዘንድ ለመልካም ወዳጅነት እጅግ ተገቢው ሰው ማነው ?" አላቸው ። እሳቸውም በመጀመሪያ እናትህ አሉት ። ሰውዬውም "ቀጥሎስ?" አላቸው ።
ነብዩም ﷺ በ2ኛም "እናትህ" አሉት።
ሰውዬው አሁንም "ቀጥሎስ?" አላቸው
"በ3ኛ ደረጃም እናትህ" ሲሉ መለሱለት ረሱልﷺ። ሰውዬው አሁንም "ቀጥሎስ?" አላቸው ። እሳቸውም በመጨረሻ(በ4ኛው) "አባትህን" አሉት።
➍ ነብዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ግን “ከአማኞች ኢማኑ (እምነቱ) የተሟላው
ስነ ምግባሩ ያማረው ነው፡፡ ከናንተ በላጫቻችሁ #ለሴቶቻቸው በላጭ የሆኑት
ናቸው” ብለው ነበር፡፡
[አስሶሒህ፡ 284]
➎ መልእክተኛው ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም “#በሴቶች ጉዳይ አደራችሁን” ብለው ነበር፡፡ [ቡኻሪና ሙስሊም]
➏ ነብዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ይላሉ፡- “አንድ ሙእሚን ወንድ
አንዷን ሙእሚናህ #ሴት (ሚስቱን) አይጥላ ፡፡ ከሷ የሆነን ባህሪ ቢጠላ ሌላ
የሚወደው አለውና፡፡” [ሙስሊም]
➐ “አዋጅ! ለናንተ #በሴቶቻችሁ ላይ ሐቅ አላችሁ፡፡ #ለሴቶቻችሁም
በናንተ ላይ ሐቅ አላቸው፡፡” [ሶሒሑልጃሚዕ፡ 7880]
➑ እንደዚሁ #ሴት ልጅ ከደረሰች ቦሃላ
ስታገባ ባልዋ ግማሽ ኢማኑ(እምነቱ) እንዲሞላ ምክንያት ናት።
➒ የሴቶች የማስተማር መብት በኢስላም
ﻭَﺍﻟْﻤُﺆْﻣِﻨُﻮﻥَ ﻭَﺍﻟْﻤُﺆْﻣِﻨَﺎﺕُ ﺑَﻌْﻀُﻬُﻢْ ﺃَﻭْﻟِﻴَﺎﺀُ
ﺑَﻌْﺾٍ ۚ ﻳَﺄْﻣُﺮُﻭﻥَ ﺑِﺎﻟْﻤَﻌْﺮُﻭﻑِ ﻭَﻳَﻨْﻬَﻮْﻥَ ﻋَﻦِ
ﺍﻟْﻤُﻨْﻜَﺮِ
”ኣማኝ ወንዶችና ኣማኝ #ሴቶች
ከፊሎቻቸው ለ ከፊሉ ረዳቶች ናቸው
በመልካም ያዛሉ ከመጥፎ የከለክላሉ።”
(ሱራ 9:71)
منقول
T.me/dawudyassin