የአቡ ሱለይማን ዳውድ ያሲን የመማማሪያ መድረክ


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: not specified


نفهم الكتاب والسنة بفهم سلفنا الصالح
ቁርአንና ሐዲስን በሰለፎች ግንዛቤ እንገንዘብ

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
not specified
Statistics
Posts filter


🔹አል ኢርሻድ ኪታብ

በፉሪ አቡበክር አሲዲቅ መስጅድ

ሀሙስና ጁመአ ከመግሪብ እስከ ኢሻ

ክፍል 112

በአቡ ሱለይማን ዳውድ ያሲን

T.me/dawudyassin


ኢብኑ ዐብዲል በር እንድህ ይላሉ
«አንድ ሰዉ በራሱ መደነቁ የአእምሮዉን ደካማነት ማሳያ ነዉ»

📚ጃሚዑ በያኒል ዒልሚ ወፈድሊህ

👉 T.me/dawudyassin


👉 የቸኳዮች ማንነት በእውቀት ባልተቤቶች ሲቃኝ
〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰
دأب هؤلاء المتسرّعون على التحذير من بعض المشايخ وطلاب العِلْم السَّلفيين الأفاضل بِقَضْد إسقاطهم وتشويه سُمعتهم عندما تدعوهم جهة أو جمعية أو مؤسسةإلى القيام بالدّروس والدّورات العلمية لا سييا في بلاد الغَرب والأقلّيات الإسلاميةفي بلاد أوروبا وأمريكا » وهؤلاء الناس يحتاجونَ إلى مَن يُيّن لهم العقيدة الصّحيحة وأحكام العبادات
የእነዚህ የቸኳዮች አካሄድ
አንዳንድ መሻኢኾችንና ሰለፊ የሆኑ ተማሪዎችን ማስጠንቀቃቸው እነሱን አንድ ማህበር ወይም ተቋም ትምህርቶችንና የተለያየ ኮርሶችን ለመስጠት ጥሪ በሚያደርጉላቸው ግዜ እነሱን ለመጣልና ተሰሚነት እንዳያገኙ ስማቸውን ለማጥፋት ነው ። በተለይ በምእራቡ ሀገር ላይና በአውሮፓ ፣ በአሜሪካ እነዚህ ሰዎች ትክክለኛ እምነትንና የአምልኮትን ህግጋት የሚያብራራላቸው ያስፈልጋቸዋል ።
وبعضهم لا يعرف التوحيد من الشركَ ؛ وبعضهم حديث عهد بالإسلام ؛ فشغلوهم بهذا التّصنيف المتعسّف ؛ وهذا التحذير  اسمعوا لفلان ولا تسمعوا لفلان
አንዳንዶች ተውሂድን ከሽርክ ለይተው አያውቁም ፣ አንዳንዶች ለእስልምና ገና እንግዳ ናቸው ከመሆኑም ጋር በዚህ ድንበር ያለፈ የመፈረጅ ተግባር ላይ ጠመዷቸው እከሌን ስሙ እከሌን እንዳትሰሙ በሚል ማስጠንቀቅ ላይ ቢዚ አደረጓቸው ።
والمحذر منه لايُشكُ في سلفينه  أو يقول إن الَتزكية - حَصريًا -يُوتَى بها من قبل أشياخ معدودين ؛ فمّن جاءكم بتزكية منهم : فاقبلوه ؛ واسمعوا له وهيئوا له الجو المناسب لإلقاء الدّروس وإقامة الدّورات العلميّة ومَنْ أتى بتزكية مِنْ غيرهم : فاطرحوه وحذِّروا منه وأسقطوه ...

የሚያስጠነቅቁት ግለሰብም በሰለፍይነቱ ምንም ጥርጥር የለውም ። እንዲህም ይላል ተዝኪያ የሚመጣው ውስን ከሆኑ አሊሞች ነው ከእነሱ ተዝኪያ ይዞ የመጣ ተቀበሉት ፣ አድምጡት ፣ የተለያዮ ዱሩሶችንና ኮርሶችን እንዲሰጥ ሁኔታን አመቻቹለት ከእነሱ ውጪ ተዝኪያን ይዞ የመጣን ወርውሩት ፣ ከእነሱ አስጠንቅቁ ፣ ተሰሚነትም እንዳይኖረውም ውድቅ አድርጉት።
والحقيقةٌ أنَّ هذا منهج حزبي ضيِق  نتج عنه : تفرق وتحزّبٌ واختلاف بين أصحاب المنهج الواحد ؛ بل ونتج عنه تصدير بعض الأصاغر ؛ حتى تمن هو حديثٌ عهد بالإسلام ؛ ليُصبحَ حَكَمًا على المشايخ وطلاب العلم السّلفيينَ  بل ونتج عنه صدٌّ عن سبيل الله سُبْحَانه وَتعَالى . وبقاء أولئك الأقليّات على جهلهم ؛ وانتشار الفوضى والشّقاق بينهم
በእውነቱ ይህ አይነት አካሄድ ጠባብ የሆነ የቡድንተኝነት አካሄድ ነው ፣ ያስከተለውም ውጤት መለያየት ፣ ቡድንተኝነት ፣ በአንድ አካሄድ ላይ ያሉ ግለሰቦች እንዲለያዮ ፣ እንደዉም ያስከተለው ውጤት አንዳንድ ትናንሾች ፊት ለፊት እንዲሰለፉ ሌላው ይቅርና አዲስ ሰለምቴ የሆኑ ሳይቀሩ በአሊሞችና በሰለፊው ተማሪዎች መሀከል ፍርድ ሰጪ ሆነዋል ፣ እንደውም የዚህ ውጤት ሰዎችን ከአላህ መንገድ መዝጋት ነው ፣ እነዚያ በእውቀት አነስተኛ የሆኑትን በመሀይምነት ላይ እንዲቆዮ ፣ ስርአት አልበኝነት እንዲስፋፋ ፣ በመሀከላቸው እንዲለያዩ አድርጓል ፣
بل إنَّ منهم من حملوا السلاح على بعضهم وهم يعيشون في دول كافرة  كما نتج عن هذا المسلك أن توقفت كثير من الدروس والدورات العلميةالمؤصلّة ؛ لأنَّ الشَّبابٍ في تلك البلاد شغلوا ببعضهم  يبدع بعضهم بعضًا  ويُفسّق
بعضهم بعضًا  وربما كَفَّر بعضهم بعضًا
እንደውም በካፊር ሀገር ላይ እየኖሩ አንዳቸው በአንዳቸው ላይ መሳሪያ አንስቷል ፣ ይህ አካሄድ በርካታ ዱሩሶችና መሰረታዊ የሆኑ የእውቀት ማእድ የሚገኝበት ኮርሶች እንዲቆሙ ምክንያት ሆኗል ። ምክንያቱም ወጣቶች በዚያ ሀገር ላይ እርስ በእርሳቸው ላይ ተጠምደዋል ፣ከፊላቸው ከፊሉን ይበድአል ፣ ከፊሉ ከፊላቸውን ይፈስቃል ፣ ምናልባትም ከፊሉ ከፊላቸውን ያከፍራል ።
تنبيه ذوي الأفهام ገፅ 17

T.me/dawudyassin


📚بلوغ المرام
📚ቡሉጉል መራም

√ዘውትር ሰኞና ማክሰኞ

√ከመግሪብ እስከ ኢሻ

√በአቡ ሱለይማን ዳውድ ያሲን

√ክፍል 65

√በቢላል ኮካ መስጅድ ከአብነት ዝቅ ብሎ ከአሚን አጠቃላይ ሆስፒታል ጀርባ

T.me/dawudyassin


📚بلوغ المرام
📚ቡሉጉል መራም

√ዘውትር ሰኞና ማክሰኞ

√ከመግሪብ እስከ ኢሻ

√በአቡ ሱለይማን ዳውድ ያሲን

√ክፍል 64

√በቢላል ኮካ መስጅድ ከአብነት ዝቅ ብሎ ከአሚን አጠቃላይ ሆስፒታል ጀርባ

T.me/dawudyassin


🔹አጥፊዎችን በስም ጠቅሶ ማስጠንቀቅ፣ ከሰለፎች ፈለግ!
(መረጃ ለሚያከብሩ ብቻ!)
~
ዛሬ ዛሬ ስለ ቢድዐ ማውራት፣ የቢድዐ አራማጆች ሰዎችን እንዳያሳስቱ ማስጠንቀቅ እንደ አፍራሽ ተግባር እየተቆጠረ ነው፣ ከጠላት ጋር እንደማሴር። ይሄ አካሄድ ስሜታዊ ሽፋን ስለተሰጠው እንጂ ውድቅነቱ ለማንም አይሰወርም። እነዚህ "የሰው ስም አታንሱ" የሚሉ አካላት ራሳቸው የሚጠሉትን ሰው ትልቅ ዓሊም እንኳ ቢሆን ስሙን ጠርተው ከማብጠልጠል የማይመለሱ ናቸው። እነዚህ አካሄዳቸው እርስ በርሱ የሚጣረስ የሆኑ ሰዎችን ወደ ጎን እንተውና ጥንት በጉዳዩ ላይ የሰለፎች ፈልግ ምን ይመስል እንደነበር እንመልከት። ቀጥሎ የተዘረዘሩት በሙሉ ከሞቱ ከአንድ ሺህ አመት በላይ ያለፋቸው ቀደምት የኢስላም ሊቃውንት ናቸው።

1. ዐብዱላህ ብኑ ሙባረክ

በአንድ ወቅት “ሙዐላ ብኑ ሂላል ጥሩ ሰው ነበር በሐዲሥ ላይ ይዋሻል እንጂ” ይላሉ። በዚህን ጊዜ የሆነ ሱፊይ ሰማቸውና “የዐብዱረሕማን አባት ሆይ! እንዴት ሰው ታማለህ?” አላቸው። ኢብኑ ሙባረክ ታዲያ፡ “ዝም በል! ግልፅ ካላደረግን ሐቅና ባጢል እንዴት ይልለያል?!” አሉት። [አልኪፋያህ፡ 9]

2. ኢብራሂም አነኸዒይ

“ለቢድዐ ሰው ሃሜት የለውም!” ብለዋል። [አልኢባናህ፡ 2/449]

3. ሰዒድ ብኑ ጁበይር

“ጦልቅ ጋር አትቀመጡ” ብለዋል። የኢርጃእ ቢድዐ አራማጅ ስለሆነ ነው ይህን ያሉት። [አልኢባናህ፡ 2/450]

4. ሐሰን አልበስሪይ

“ለቢድዐ ሰው ሃሜት የለውም! አመፁን ባደባባይ ለሚያወጣ አመፀኛም ሃሜት የለም” ብለዋል። [ሸርሑ ኡሱሊ ሱናህ፣ ላለካኢ፡ 1/158]

5. አቡ ኢድሪስ አልኸውላኒይ

“አዋጅ! አቡ ጀሚላ በቀደር አያምንም። እንዳትቀማመጡት!” ብለዋል። [አልኢባናህ፡ 2/449]

6. ቀታዳህ

ዓሲም አልአሕወል እንዲህ ይላሉ፡- “ቀታዳ ዘንድ ተቀምጬ ነበር። ዐምር ብኑ ዑበይድ ስሙ ሲወሳ በክፉ አነሳው። 'ዑለማዎች ከፊሉ በከፊሉ ላይ እንደሚናገር አላውቅም ነበር' ስለው 'አሕወል ሆይ! አንድ ሰው ቢድዐ ሲያንፀባርቅ ሰዎች ይጠነቀቁት ዘንድ ስሙ ሊጠቀስ እንደሚገባ አታውቅም'ንዴ?' አለኝ።” [አልሚዛን፡ 5/330]

7. የሕያ ብኑ ሰዒድ አልቀጧን

እንዲህ ይላሉ፡- “ሱፍያኑ ሠውሪይን፣ ሹዕባን፣ ማሊክ ብኑ አነስን፣ ሱፍያን ብኑ ዑየይናን 'የሆነ (ተሻጋሪ) ጥፋት ወይም የዘገባ ድክመት ስላለበት ሰው ሁኔታ ዝም ልበል ወይስ ግልፅ ላድርግ?' ብየ ስጠይቃቸው 'ግልፅ አድርግ' አሉኝ።” [ሸርሑ ዒለሊ ቲርሚዚይ፡ 1/49]

8 - 9. አርጣህ ብኑ ሙንዚር እና አውዛዒይ

ዑቅባህ ብኑ ዐልቀማህ እንዲህ ይላሉ፡-
“በአንድ ወቅት ከአርጣህ ብኑ ሙንዚር ጋር ነበርኩኝ። በቦታው ከነበሩ ሰዎች አንዱ ‘ከአህሉ ሱና ጋር እየተቀመጠ፣ እየተቀላቀላቸው ስለ ቢድዐ ሰዎች ሲወራ ግን ‘ተውን እንግዲህ ስማቸውን አታንሱ’ ስለሚል ሰው ምን ትላላችሁ’ ሲል ጠየቀ። የዚህን ጊዜ አርጣህ ‘እሱ እራሱ ከነሱ ነው። እንዳያታልላችሁ!’ አለ። ይሄ የአርጣህ ንግግር አልተመቸኝምና ወደ አውዛዒይ ሄድኩኝ። አውዛዒይ እንዲህ አይነት ነገሮች ሲደርሱት ገላጭ ነበር። ጠየቅኩት። ‘አርጣህ እውነት ተናግሯል። ሐቁ እሱ ያለው ነው። ይሄ ሰውየ ስማቸው እንዳይነሳ ይከለክላል። ስማቸው ካልተገለፀ እንዴት ሰዎች ይጠነቀቋቸዋል?!’ አለ።” [ታሪኹ ዲመሽቅ፡ 8/15]

10 - 12. ሐማድ፣ ማሊክ እና ሸሪክ

አቡ ሰለማ አልኹዛኢይ እንዲህ ይላሉ፡- “ሐማድ ብኑ ሰለማን፣ ማሊክ ብኑ አነስን፣ ሸሪክ ብኑ ዐብዲላህን ቢድዐ ስለሚፈጥር ሰው 'ነገሩ ግልፅ ይደረጋል' ሲሉ ሰምቻለሁ።” [ሸርሑ ዒለሊ ቲርሚዚ፡ 1/49]

13. ኢማሙ አሕመድ

“ለቢድዐ ሰው ሃሜት የለውም!” ብለዋል። [ጦበቃቱል ሐናቢላ፡ 2/274]

ሙሐመድ ብኑ በንዳር፡ “በውኑ እኔ እከሌ እንዲህ ነው፣ እከሌ እንዲህ ነው ማለት ይከብደኛል” ቢሉ አሕመድ እንዲህ ሲሉ መለሱ፡- “አንተም ዝም ካልክ እኔም ዝም ካልኩ መሀይም የሆነ ሰው ጤነኛውን ከበሽተኛው እንዴት ይለየው?!” [አልፈታዋ፡ 28/231]

አሁንም ኢማሙ አሕመድ “ትርፍ ፆም ከሚፆም፣ ትርፍ ሶላት ከሚሰግድ፣ ኢዕቲካፍ ከሚያደርግ ሰውና ስለ ሙብተዲዖች ከሚያወራ ሰው የትኛው ነው አንተ ዘንድ ይበልጥ የተወደደው?” ተብለው ቢጠየቁ “ቢሰግድ፣ ቢፆም እንዲሁም ኢዕቲካፍ ቢያደርግ ለራሱ ነው። ስለ ሙብተዲዖች ሲያወራ ግን ጥቅሙ ለሙስሊሞች ነውና ይሄኛው ይበልጣል” ብለዋል። [አልፈታዋ፡ 28/231]

እስካሁን የተዘረዘሩት ሰዒድ ኢብኑ ጁበይር፣ አቡ ኢድሪስ አልኸውላኒይ፣ ሐሰን አልበስሪይ፣ ኢብራሂም አነኸዒይ፣ ኢብኑል ሙባረክ፣ ኢማሙ ማሊክ፣ ሸሪክ ብኑ ዐብዲላህ፣ አውዛዒይ፣ ዐርጧህ ብኑ ሙንዚር፣ ሐማድ ብኑ ሰለማ፣ ሸሪክ ብኑ ዐብዲላህ፣ ሱፍያኑ ሠውሪይ፣ ሹዕባ፣ ሱፍያን ብኑ ዑየይና፣ ቀታዳ እና ኢማሙ አሕመድ ናቸው። በእርግጠኝነት ከዚህ በላይ ብዙ መዘርዘር ይቻላል። ይህንን የምጠቅሰው ዲን ከሚንዱ አጥፊዎች ማስጠንቀቅ ከጥንት ዑለማዎች ጀምሮ ሲወርድ ሲዋረድ የመጣ ሐቅ እንጂ በቅርብ ጊዜ የተጀመረ ጉዳይ እንዳልሆነ ለመጠቆም ነው።

እንዲያውም ከነዚህ ሁሉ ፈለጎች በላይ ከነብዩ ﷺ ሱናዎች በቂ መረጃ አለ። ለምሳሌ ያክል ፋጢማህ ቢንት ቀይስ - ረዲየላሁ ዐንሃ - ሙዓዊያህ ብኑ አቢ ሱፍያንና አቡ ጀህም ለትዳር እንደጠየቋት ለነብዩ ﷺ ብታማክራቸው፡
“አቡ ጀህም ዱላውን ከትከሻው አያወርድም። ሙዓዊያም ድሃ ነው፣ ገንዘብ የለውም። ይልቅ ኡሳማህ ብኑ ዘይድን አግቢ” ብለው ነው የመለሱላት። ዘገባው ላይ ጣትህን እንዳትቀስር ሙስሊም ናቸው የዘገቡት። [ሙስሊም: 3770]
ልብ በሉ! ሰዎቹን በሌሉበት ነው ስማቸውን ያወሱት። በአንዲት ሴት የትዳር ጉዳይ አስፈላጊ ሲሆን የሰዎችን ስም ማንሳት ከተቻለ፣ ዲንን የሚያጠለሹ፣ ወደ ቢድዐ የሚጣሩ ሰዎችን ስም ጠቅሶ ማስጠንቀቅ ደግሞ የበለጠ ተገቢ ነው።

ከግለሰቦች በላይ ለእምነታችን ቅድሚያ ልንሰጥ ይገባል። እርግጥ ነው፡
* ፍትህ በጎደለው መልኩ በግል ጥላቻ ተነሳስተን በደለኛ ንግግር ልንናገር አይገባም።
* በትንሽ በትልቁ አደብ የቀለለው ትችት ውስጥ ከመግባትም ልንቆጠብ ይገባል።
* የሚታለፉና የማይታለፉ ርእሶችንም መለየት አለብን።
* ከዲን በመከላከል ሽፋን ተሻጋሪ ያልሆኑ የግለሰቦችን ነውሮች መዘክዘክም ነውረኝነት ነው።
እነዚህን ነገሮች ከጠበቁ በኋላ ዲን የሚበክሉ፣ ደካሞችን የሚያሳስቱ ሰባኪዎችን አትንኩ ማለት ግን የእውነት ዲናችንንም፣ ወገኖቻችንንም የሚጎዳ ነው። ሙብ ^ ተዲዖች ላይ እንደ አስፈላጊነቱ ስማቸውን እያነሱ ጭምር መልስና ማስጠንቀቂያ ባይሰጥባቸው ኖሮ ዲኑ የማንም መጫወቻ በሆነ፣ ህዝብም ገደል በገባ ነበር።
ደግሞም አስተውሉ! ከነዚህ የሰው ስም አታንሱ ከሚሉ ሰዎች ውስጥ የሰው ስም የማያነሳ አለ?! በጭራሽ! “ስም አታንሱ” የሚሉት ራሳቸው በቢድዐ ቁንጮዎች ላይ የሚሰጠውን ሂስ ዝም ለማሰኘት እንጂ አነሰም በዛ ራሳቸውም የሰው ስም ከማንሳት የሚቆጠቡ አይደሉም።

ማሳሰቢያ፦
ያወራሁት ስለ አጠቃላይ መርሁ ነው። እንጂ “ጉዳዩ ጤነኛ ባልሆነ መልኩ የሚያዝበት ሁኔታ አልበዛም ወይ?” ከተባለ “እንዴታ!” ነው መልሱ። በርግጠኝነት ውጥንቅጡ የወጣ፣ ከልክ ያለፈ፣ መረን የለቀቀ፣ ባላሰበው አቅጣጫ በሱና ስም ሱናን የሚዋጋ ብዙ ሰው አለ። እንዲህ አይነቱን አካል ሚዛን እንዲጠብቅ መታገል እንጂ የትኛውም አጥፊ ስሙ እንዳይነሳ ብሎ በር ለመከርቸም መሞከር አይሳካም እንጂ ቢሳካ ጉዳቱ ከባድ ነው የሚሆነው።

(ኢብኑ ሙነወር፣ የካቲት ዐ4/2009)
https://t.me/dawudyassin


በጉራጌ ዞን እነሞር ወረዳ እገበኝ ቀበሌ የሚገኘዉ ቢላል መስጅድ ኡስታዝ ይፈልጋል (አስቸኳይ
1 የማስቀራት ልምድ ያለው
2. ኢስላማዊ አደብ የተላበሰ
3.ኪታብ የማስቀራት አቅም ያለዉ
4 ከሰዎች ጋር ተግባቢነት ያለዉ
ብዛት:- 1 ወንድ
ደሞዝ:-  በስምምነት
ቅጥር በቋሚነት
በዚህ ያናግሩን
በቴሌግራም  @Jilaluebest
ለመደወል 0925417548
ጉራጊኛ ቋንቋ ለሚችል ቅድሚያ ይሰጣል


በኧገበኘ ቢላል መስጅድ የተደረገ የጁመዓ ኹጣባ

የሻዕባን ወር

በአቡ ሱለይማን ዳውድ ያሲን

T.me/dawudyassin


በጉሬ ነሲሓ መስጅድ የተደረገ ሙሀደራ

ረመዷንን እንዴት እንቀበለው

በአቡ ሱለይማን ዳውድ ያሲን

T.me/dawudyassin


በኧገበኘ ቢላል መስጅድ የተደረገ ሙሀደራ

ሽርክ ምንድን ነው?

በአቡ ሱለይማን ዳውድ ያሲን

T.me/dawudyassin


በኧወረሠባቴ መንደር የተደረገ ሙሀደራ

ረመዷንን እንዴት እንቀበለው?

በኡስታዝ አብዱል ካፊ ሙሐመድ

T.me/dawudyassin


አሠላሙ አለይኩም ወራህመቱላ ወበረካትሁ

ወንድም እህቶች እንዴት ናችሁ? የትናንቱ የቃፊላ ፕሮግራም ምን ይመስል ነበር?

አልሀምዱሊላህ ለትናንት የታቀደው የቃፊላ ዳዕዋ ፕሮግራም በታቀደለት መሠረት ተሳክተዋል::ምናልባት ከታቀዱት 16 ቦታዎች አንዱ ብቻ በተፈጠረ የትራንስፖት ችግር ወደ ጎፍረር የተላኩት ኡስታዞች በሠዓቱ ሊደርሡ አልቻሉም::በዚህም ምክንያት የጎፍረሩ አልተሳካም::አልሀምዱሊላህ ከዚህ ውጭ የገጠመ ምንም ችግር አልነበረም::ፕሮግራሙም በአግባቡ ተፈፅመዋል::የዚህ ፕሮግራም እስካሁን ከተደረጉት ትንሽ ሎዱ ቢበዛም ፕሮግራሙ ግን እጅግ አመርቂ ነበር ማለት ይቻላል::
በትናንቱ ፕሮግራም ብዙ አዳዲስ መስጅዶችን ተዳሠዋል::እንደዚሁም ከነባር ኡስታዞች ጉን ለጎን ብዙ ወጣት ዳኢዎች ተሳትፈውበታል::ከዚህ ሁሉ በጣም የሚገርመው ከዚህ ከአ.አ የተሳተፉ የእነሞር ተወላጆች ቁጥር ግን በጣም አነስተኛ ነው::በቀጣይም ዳዕዋውን በደንብ ተደራሽ ለማድረግ ግን የሁላችም ተሳትፎ እጅግ ወሳኝ በመሆኑ ከጎናችን በመሆን እንታግዙ ጥርያችን እናስተላልፋለን::

      እነዚህን መስጅዶች በዳዕዋው ተደራሽ ሆነዋል
🌹🌹ኧገበኘ ቢላል መስጅድ
🌹🌹ተርሆኘ
🌹🌹ዳእምር
🌹🌹ጠረደ ኑር መስጅድ
🌹🌹ጉስባጃ ጋፋራ መስጅድ
🌹🌹ኧገዚ ሠላም መስጅድ
🌹🌹ኧዘዊድ
🌹🌹ኧወረሠባቴ ነስር መስጅድ
🌹🌹ኧሠጠኜ
🌹🌹አስጠር ቢላል መስጅድ
🌹🌹ዚቁወ ትልቁመስጅድ
🌹🌹ኧሚኢዲ
🌹🌹ሚቄ ቶሬ መስጅድ
🌹🌹ማፌድ ጠይብ መስጅድ
   እነኝህን ነበሩ
T.me/dawudyassin


አልከሶ ላይ የሚደረጉ የሽርክ አይነቶች  በጥቂቱ በስልጥኛ ቋንቋ !!



❶ አልከስዬን ካሌ ዩለ አቦተ = ዮክቤ ረክቤን ወዬ በጫረተ

❷ ዮልዬይ ወልዬ አልከስዬ = የረህመተይ በረ ክፈቱዬ

❸ ያልከሶ አባባዬ ትልብል ትልብል = ለማኒ ጣልኩሙኝ ውርውር ልልብል

❹ ያልከሶ አባብዬ ኑዲኒሞ = ኤወዲ እለፈዲ ብለኒሞ

❺ ብንጥረታም ውስጥ ኡፍታሙ ሙለ = አቤት አቤት ይላን የሙሪዲ በላ

❻ አልከስዬን ካሌ ባዬት አለ = የትቆጬ ህንጣብተ ያበቀለ

❼ ያልከሶይ ጎተረ ባባተረ = ለኘ ልዮቡነ ምን ሀተረ

➑ ምንን በባሉሞ ትመጦሞ = አቤት አቤት ህላን በላይ ሰቦ

➒ ያልከሶ አባባዬ ላአሏህ በሎ = ይንጭነናይ ደዊ እትደሎ

❿ ህንጥረት ህንጥሮ ለዙረነ = ተላላፊ ነቶ ለይነቺነ 

=============

ይህነው ሽርክ ማለት !! ቀላል ነገር  አድርገን ማያት የለብንም !! ከቤተሰቦቻችን ጀምረን አከባቢያችነን ጭምር ልናስጠንቅቅ ይገባል ባይነኝ !!
منقول


🔹የራስን ስህተት እያቃለሉ የሌሎችን ስህተት መለቃቀምና ማግዘፍ መንሐጅ ሰለፍ አይደለም
〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰
👉 የዘመኑ ዘመናዊ ሙሪዶች የራሳቸው ስህተት አይታያቸውም የሚወዷቸው ሰዎችም ችግር እንዲወራ አይፈልጉም ፣ ስህተታቸውን ቁልጭ አድርገህ ብታሳያቸው ከስህተታቸው ከመመለስ ይልቅ ለምን እነ እከሌስ የእነሱ ስህተት ለምን አይነገርም ይሉሀል አልያም ትልልቅ ስህተቶች እያሉ ትንንሹን ለምን ትለቃቅማለህ ይላሉ ሱብሃ ረቢ ‼
👉 ጥቃቅን ስህተት የሚሉት እውነት ስህተቱ አነስተኛ ሆኖ ሳይሆን ስህተቱ እነሱ ላይ ስለተገኘ ነው ፣ ሌላው ላይ ከተገኘ ከባድ አደገኛ አጥፊ ወንጀል ሲሆን እነሱጋ ሲሆን ግን ተራ ስህተት ይሆናል
👉 ሰለፎች ከምንም በላይ የራሳቸው ሁኔታ ያሳስባቸው ነበር ፣ ስለሆነም ሁልግዜ ነፍስያቸውን ይተሳሰቡ ነበር። የነርሱን ነውር የነገራቸውን ሰው ዱአ ያደርጉለት ነበር
وكان عمر بن الخطاب رضي الله عنه يقول: "رحم الله امرأً أهدى إلي عيوبي"

ኡመር ቢን አል ኸጣብ  እንዲህ ይሉ ነበር
[ነውሬን ለነገረኝ ሰው አላሁ ተአላ ይዘንለት ]
👉 ሰለፎች ወንጀልን አግዝፈው ነበር የሚመለከቱት
عنْ أَنَس  قالَ: "إِنَّكُمْ لَتَعْملُونَ أَعْمَالًا هِيَ أَدقُّ في أَعْيُنِكُمْ مِنَ الشَّعَرِ، كُنَّا نَعْدُّهَا عَلَى عَهْدِ رسولِ اللَّهِ ﷺ مِنَ الْمُوِبقاتِ" رواه البخاري

[አነስ ኢብኑ ማሊክ እንዲህ ይላሉ
እናንተ የምትሰሩትን ስራ ከፀጉረችሁ አሳንሳችሁ የምትመለከቱትን እኛ በነብያችን ዘመን ከባድ አጥፊ ወንጀል አድርገን እንቆጥረው ነበር ] የቡኻሪ ዘገባ

👉 ሰለፎች አቋማቸው እንዲህ ሆኖ ሳለ ዛሬ ላይ ግን ለራሳችን ሲሆን በራሳችን ላይ ሲመጣብን ሀቅን ከመያዝ ይልቅ የተለያዩ ማስተባበያዎች ስንደረድር እንስተዋላለን
👉 🟣 የለተሞ ሸይኽና ሙሪዶቻቸው ከወደቁባቸው የመንሐጅና የስነምግባር ችግሮች መሀከል በጥቂቱ
① ቢድአ የሰራን  ሙብተዲእ እንለዋለን የሚል አደገኛ የሀዳዲያ ቃኢዳን መናገራቸውና ተግባራዊም ማድረጋቸው ነው
②  ከሀዳዲያ መንሐጅ መገለጫ አንዱ በሆነው ሰዎችን በተሰልሱል ከመንሐጅ አሰለፍ ማስወጣታቸው
③ የተለያዩ የቢድአ ንግግሮችን መናገራቸው
~ የሰዎችን የአቂዳ ደረጃ በፐርሰንት መመደባቸው
~ በኢስላም ታላቅ ደረጃ ባለው ምፅዋት ሰደቃ ላይ መቀለዳቸው
~ ሙስሊምን ከካፊር ጋር ማመሳሰላቸው
~ ወደ አላህ መቃረቢያ ከሆነው አንዱ
በተውበት ላይ ማሾፋቸው
④ መስአላ ፊቅሂያ በሆነ ነጥብ ላይ ሰዎችን በተብዲእ መፈረጃቸው
⑤ ተሳዳቢ ፣ ተራጋሚ ፣ ተዛላፊ መሆናቸው
⑥ መስፈርቱ ባልተሟላ ሁኔታ በተብዲእ ላይ መሰማራታቸው
⑦ ከሂዝብያ መሰረትና መገለጫ በሆነው ውሸት ላይ መዘፈቃቸው
~ ተውሂድ አያስተምሩም
~ ሽርክና ቢድአን አያስጠነቅቁም
~ አዲስ ዲን ይዘው መተዋል
~ ከቢድአ ሰዎች ጋር አንድ ሆነዋል
~ ስለ ጠመሙ አንጃዎች ላለማውራት ስምምነት ፈፅመዋል ።
👉 🟣 በእውነቱ የሚቀጥፏቸው ቅጥፈቶች ብዙ ናቸው ብልህ ለሆነ አንድ ጥቆማ ብቻ በቂው ነው ።
⑧ እርማት የሚያስፈልገውን ፈትዋቸውን እያወቁ እስከነ ስህተቱ ማሰራጨታቸው
⑨ ውስን በሆኑ የኢጅቲሐድ መስአላ ላይ የተቃረኗቸውን ሱኒ ወንድሞች ከየሁዳና ነሳራ የባሱ ናቸው ብለው መፈረጃቸው
👉 ይህንና ይህን የመሰሉ ከባባድ ስህተቶች ቀላልና ተራ ስህተቶች ተደርገው ይቆጠራሉ ፣ ተራ ትችት ብለው ያጣጥላሉ ፣ ደግሞ ራስ ምታታቸው ሲጨምር ሰው የመንሐጅ ርዕስ እያወራ ስለ አረብኛ አፃፃፍ ስህተት ያወራሉ እያሉ ርዕስ ያስቀይሳሉ የዚህ ሁሉ ምክንያቱ እነዚህ አደገኛ የሆኑ ስህተቶች የተገኙት በእነሱ ጉያ ስር  ስለሆነ ብቻ ነው ።
👉 እነዚህንና ሌሎችንም የመንሐጅና የስነምግር ችግራቸውን ከነድምፁ አያይዤ ከዚህ በፊት በተለያየ ርእስ ላይ ለቅቄዋለው ማረጋገጥ የፈለገ ድምፆቹን ማግኘት ይችላል
👉 ሰለፍያን የሞገተ ሁሉ ሰለፊ አይደለም፣ ለሰለፍያ የተቆረቆረ ሁሉ ትክክል ነው ማለት አይደለም
ኢንተቢሁ‼
T.me/dawudyassin


🔹አል ኢርሻድ ኪታብ

በፉሪ አቡበክር አሲዲቅ መስጅድ

ሀሙስና ጁመአ ከመግሪብ እስከ ኢሻ

ክፍል 111

በአቡ ሱለይማን ዳውድ ያሲን

T.me/dawudyassin


🔹አል ኢርሻድ ኪታብ

በፉሪ አቡበክር አሲዲቅ መስጅድ

ሀሙስና ጁመአ ከመግሪብ እስከ ኢሻ

ክፍል 110

በአቡ ሱለይማን ዳውድ ያሲን

T.me/dawudyassin


‏مِن فِقْهِ نَشْرِ الْعِلْم:
قال الذهبي رحمه الله: "يَنْبَغِي لِلْمُحَدِّثِ أَنْ لاَ يُشْهِرَ الأَحَادِيْثَ الَّتِي يَتَشَبَّثُ بِظَاهِرِهَا أَعدَاءُ السُّنَنِ مِنَ الجَهْمِيَّةِ، ... ، وَأَهْلِ الأَهْوَاءِ، وَالأَحَادِيْثَ الَّتِي فِيْهَا صِفَاتٌ لَمْ تَثْبُتْ، فَإِنَّكَ لَنْ تُحَدِّثَ قَوْماً بِحَدِيْثٍ لاَ تَبْلُغُهُ عُقُوْلُهُم، إِلاَّ كَانَ فِتْنَةً لِبَعْضِهِم فَلاَ تَكْتُمِ العِلْمَ الَّذِي هُوَ عِلْمٌ, وَلاَ تَبْذُلْهُ لِلْجَهَلَةِ الَّذِيْنَ يَشْغَبُوْنَ عَلَيْكَ, أَوِ الذين يفهمون مِنْهُ مَا يَضُرُّهُم"
سير أعلام النبلاء (578/10)


Video is unavailable for watching
Show in Telegram
•••
طلب العلم وإن قل أفضل من الجهل.


▫️إن لم تستطع العلم كلّه،  فنَلْ من العلم بعضه...

▫️لا تكن قانعا بجهلٍ،  فاطلب من العلم ولو أقلّه......

🎙فضيلة الشيخ عبد السلام الشويعر حفظه الله تبارك وتعالى.
•••📚


Forward from: ኢብኑ መስኡድ ኢስላሚክ ሴንተር – አዲስ አበባ ibnu Mas'oud islamic center
📣 ኢብኑ መስኡድ ኢስላሚክ ሴንተር በሚከተሉት የስራ ቦታዎች አአመልካቾችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል

የስራ መደብ 1:- የገቢ ማሰባሰቢያ አስተባባሪ

※ የትምህርት ደረጃ፡ ዲፕሎማ
※ የስራ ቦታ፡ አዲስ አበባ
※ የስራ ሁኔታ፡ የ3 ወር ኮንትራት
※ጾታ፡- ወ

🔅መስፈርት

✅ ዕርዳታ የማሰባሰብ ልምድ ያለው
✅ የኢብኑ መስዑድ / ነሲሃ ዳዕዋ እንቅስቃሴ ግንዛቤ ያለው
✅ በተለያዩ የዳዕዋ ተግባራት ላይ ተሳታፊ የሆነ
✅ ጥሩ የመግባባት ችሎታ ያለው
✅ ሱና ነጸብራቅ የሚታይበት

※ ተፈላጊ ብዛት፡ 2

※ ደሞዝ፡ በአፈፃፀሙ መሰረት ቦነስ ያለው

የስራ መደብ 2:- የእርዳታ ማስተባበሪያ ሰራተኛ

※ የትምህርት ደረጃ፡ ዲፕሎማ እና ከዚያ በላይ
※ የስራ ቦታ፡ አዲስ አበባ
※የስራ ሁኔታ፡ የ3 ወር ኮንትራት
※ ተፈላጊ ብዛት፡ 10
※ ደሞዝ፡ በአፈፃፀሙ መሰረት ቦነስ ያለው
※ጾታ፡- ወ

🔅 መስፈርት

✅ የኢብኑ መስዑድ / ነሲሃ ዳዕዋ እንቅስቃሴ ግንዛቤ ያለው
✅  በተለያዩ የዳዕዋ ተግባራት ላይ ተሳታፊ የሆነ
✅ ጥሩ የመግባባት ችሎታ ያለው
✅ የሱና ነጸብራቅ የሚታይበት

ለማመልከት:- CV በቴሌግራም @Ibnumesoud01 ላይ ይላኩ

___
🕌 ibnu Masoud islamic Center
@merkezuna


Noor_Book_com_وجوب_طاعة_السلطان_في_غير_معصية_الرحمن_بدليل_السنة.pdf
4.0Mb
ይህን ኪታብ አንብቡት‼

መንሐጅ አሰለፊና መንሐጅ አሱሩሪያ ከሚለዮበት ዋንኛና አንዱ የሆነው ነጥብ ይህ ነው
وجوب طاعه السلطان في غير معصية الرحمن بدليل السنة والقرآنPdf


مؤلف: محمد بن ناصر العريني

قدم له: الشيخ صالح الفوزان حفظه الله ورعاه

20 last posts shown.