ጤናማና ትክክለኛ የቤተክርስቲያን መሪ ስትኾን እንዲህ ታስባለህ፤ ትጨነቃለህም።
በCordova ግዛት የTrinity Baptist Church ቄስ ወይም መጋቢ የኾነው Matt Crawford እንዲህ ይላል፦
" ... ቤተክርስቲያን ለሰዎች የእምነት ቦታ ከአምላካቸው ጋር በጋራ በአምልኮ የሚያሳልፉባት ቦታ መኾንዋ ቀርቶ፣ በአዲሱ የአሜሪካ መንግሥት አስተዳደር ወረራ እየተደረገባትና የመኖሪያ ፈቃድ የሌላቸውና የአገሪቱን የኢሚግሬሽን መሥሪያ ቤት ውሳኔ እየተጠባበቁ ያሉትን ሰዎች ማፈሻ ቦታ ኾናለች። እኔም የቤተክርስቲያን መሪ እንደ መኾኔ፣ ልቤን ክፉኛ አስጨንቆታል። የወሰድኩትን ትንሽ የእረፍት ጊዜ በአግባቡ እንዳልጠቀም አእምሮዬን እረፍት ነስቶታል። ለእነዚህ በአገራቸው በሰላምና በመልካም ኹኔታ መኖር አቅቷቸው ወይም የተሻለ ኑሮ ለልጆቻቸው ፍለጋ ለተሰደዱትና በፍርሃት ላሉት አምላኬን እለምናለሁ። ብርቱ ጸሎት ያሻናል።
እኔም ስደተኛ ነኝ። ..."
“በስደተኛው ግፍ አታድርጉ፤ እናንተ በግብፅ ምድር ስደተኞች ስለ ነበራችሁ የስደተኛ ነፍስ እንዴት እንደ ሆነች አውቃችኋልና።”(ዘጸ. 23፥9)
“እኔ እግዚአብሔር አምላካችሁ ነኝና ለመጻተኛና ለአገር ልጅ አንድ ዓይነት ሕግ ይሁንላችሁ።”(ዘሌዋ. 24፥22)
ይህን የተገለጠ ቅዱስ ቃል፣ ኹል ጊዜ ዓለማውያንና አረማውያን ከሚሠሩት የግፍ ሥራ ጋራ "ሰባኪና አገልጋይ ነን" የሚሉ ሰዎች ሲተባበሩ ሳይ፤ ጨውነትና ብርሃንነትን ሲሸሽጉ ስመለከት እተክዛለኹ፤ እጨነቃለኹ።
ይህ ወንድማችን ግን እጅግ የተወደደ ነው። ከግፉአን ጎን በመቆም ብርሃንነቱን ገልጦአል። ጌታ አብዜቶ ይባርከው።
ጌታ ሆይ የክፋት ቀናትን አሳጥርልን፤ አሜን። (የቄሱን ሙሉ መልእክት - https://churchleaders.com/news/)
የቴሌግራም አድራሻ - https://t.me/ebenezertek
በCordova ግዛት የTrinity Baptist Church ቄስ ወይም መጋቢ የኾነው Matt Crawford እንዲህ ይላል፦
" ... ቤተክርስቲያን ለሰዎች የእምነት ቦታ ከአምላካቸው ጋር በጋራ በአምልኮ የሚያሳልፉባት ቦታ መኾንዋ ቀርቶ፣ በአዲሱ የአሜሪካ መንግሥት አስተዳደር ወረራ እየተደረገባትና የመኖሪያ ፈቃድ የሌላቸውና የአገሪቱን የኢሚግሬሽን መሥሪያ ቤት ውሳኔ እየተጠባበቁ ያሉትን ሰዎች ማፈሻ ቦታ ኾናለች። እኔም የቤተክርስቲያን መሪ እንደ መኾኔ፣ ልቤን ክፉኛ አስጨንቆታል። የወሰድኩትን ትንሽ የእረፍት ጊዜ በአግባቡ እንዳልጠቀም አእምሮዬን እረፍት ነስቶታል። ለእነዚህ በአገራቸው በሰላምና በመልካም ኹኔታ መኖር አቅቷቸው ወይም የተሻለ ኑሮ ለልጆቻቸው ፍለጋ ለተሰደዱትና በፍርሃት ላሉት አምላኬን እለምናለሁ። ብርቱ ጸሎት ያሻናል።
እኔም ስደተኛ ነኝ። ..."
“በስደተኛው ግፍ አታድርጉ፤ እናንተ በግብፅ ምድር ስደተኞች ስለ ነበራችሁ የስደተኛ ነፍስ እንዴት እንደ ሆነች አውቃችኋልና።”(ዘጸ. 23፥9)
“እኔ እግዚአብሔር አምላካችሁ ነኝና ለመጻተኛና ለአገር ልጅ አንድ ዓይነት ሕግ ይሁንላችሁ።”(ዘሌዋ. 24፥22)
ይህን የተገለጠ ቅዱስ ቃል፣ ኹል ጊዜ ዓለማውያንና አረማውያን ከሚሠሩት የግፍ ሥራ ጋራ "ሰባኪና አገልጋይ ነን" የሚሉ ሰዎች ሲተባበሩ ሳይ፤ ጨውነትና ብርሃንነትን ሲሸሽጉ ስመለከት እተክዛለኹ፤ እጨነቃለኹ።
ይህ ወንድማችን ግን እጅግ የተወደደ ነው። ከግፉአን ጎን በመቆም ብርሃንነቱን ገልጦአል። ጌታ አብዜቶ ይባርከው።
ጌታ ሆይ የክፋት ቀናትን አሳጥርልን፤ አሜን። (የቄሱን ሙሉ መልእክት - https://churchleaders.com/news/)
የቴሌግራም አድራሻ - https://t.me/ebenezertek