በዐድዋ ድል የቤተክርስቲያን ሚና
በመ/ር ጌታቸው በቀለ
✍️ ዐፄ ምኒልክ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን
ስዕለት ተሥለዋል፡፡
✍️ ብፁዕ አቡነ ማቴዎስና ዕጨጌ ወልደ ጊዮርጊስ በመላ ሀገሪቱ ጸሎት፣
ኀዘንና ምህላ ዐውጀው ነበር።
✍️ ከዘመቻው በፊት ዘማች አብያተክርስቲያናትም ተለይተዋል፣
✍️ በዘመቻውም ታቦት፣መስቀል፣ ንዋያተ ቅድሳት ጥላዎች እና
ድባቦች ይዘው ሊቃውንቱ እና ካህናት ዘምተዋል።
የዐድዋ ጦርነት የካቲት 23 ቀን በዕለተ ሰንበት በ6 ሰዓት ውስጥ በሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ተራዳኢነት፣ በጀግኖች አባቶቻችን አርበኝነት ተጋድሎ በኢትዮጵያ የበላይነትና ድል አድራጊነት ተጠናቀቀ፡፡
ይህንንም ድል በየዓመቱ ሀገራችን ኢትዮጵያ ታከብረዋለች፡፡ ዘንድሮም ለ129ኛ ዓመት ይከበራል፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንም በመናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን በታላቅ ድምቀት ታከብራለች፡፡ በዐድዋው ድል የቤተክርስቲያንን አስተዋጽኦ፣ የቅዱስ ጊዮርጊስን ተራዳኢነት በስፋት ታስተምራለች፡፡ ታሪኩን እንደሚከተለው እንመለከታለን፡-
የዐድዋን ድል
የዐድዋ ድል ለዘመናት ተከብሮ የኖረውን የኢትዮጵያን ሉዓላዊ ሀገርነትና ነፃነትን ከማረጋገጡም በላይ ለሀገራችን ዓለም አቀፍ ዝናን አጐናጽፏታል፡፡ የዐድዋ ድል ለኢትዮጵያውያን የትብብር፣ የአንድነት፣ የኩራትና የክብር ምንጭ ከመሆኑ ባሻገር፤ የድሉ ባለቤት የሆነችው ኢትዮጵያ ለጥቁሮች ነፃነትና የክብር ፋና ለመሆን በቅታለች፡፡ የዐድዋ ድል ምሳሌነት አፍሪካውያን በቅኝ ገዥዎቻቸው ላይ አንዲነሡ ምክንያት ሆኗል፣ ለፓን አፍሪካን እንቅስቃሴ መፋፋምም ጉልህ አስተዋጽኦ አበርከቷል፡፡ ከዚህ አልፎ የዐድዋ ድል ከነጮች ተጽዕኖ ነፃ የሆነ የጥቁሮች የሃይማኖት እንቅስቃሴ እንዲጀመር ምክንያት እስከ መሆን ደርሷል፡፡ ለአብነትም ኢትዮጵያኒዝም እየተባለ ይጠራ የነበረውና በተለይ በአሜሪካና በደቡብ አፍሪካ የነበረውን እንቅስቃሴ መጥቀስ ይቻላል፡፡
በዐድዋ ድል የቤተክርስቲያን ሚና
ለዐድዋ ድል መገኘት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሚና እጅግ የላቀ መሆኑ አጠያያቂ አይደለም፡፡ ይህች ጥንታዊ ቤተክርስቲያን በዐድዋ ጦርነት ወቅት ከመነሻው እስከ መጨረሻው፣ ከዘመቻው እስከ ድሉ፣ ከዋዜማው እስከ ጦርነቱ በመሪነትና በተሳታፊነት ነበረች፡፡ ቤተክርስቲያኗ ሕዝቡን በመቀስቀስ፣ አመራር በመስጠት፣ አብራ በመዝመት፣ የሥነ ልቦና ዝግጅት እንዲኖር በማድረግ፣ በጦርነቱ በመሳተፍ፣ መረጃ በመስጠትና በማስቀመጥ ባደረገችው አስተዋጽዖ ተወዳዳሪ አልነበራትም፡፡ በዐድዋ ጦርነት ወቅት ቤተክርስቲያኗ የነበራትን የላቀ ሚና ለመረዳት የዐፄ ምኒልክን የክተት ዐዋጅ መመልከት በቂ ነው፡፡ ዐዋጁ ጦርነቱ ከቤተክርስቲያን፣ ከእግዚአብሔር እና ከወላዲት አምላክ ጠላት ጋር እንደሆነና የመጣው ጠላት አገር የሚያፈርስ ብቻ ሳይሆን፤ ሃይማኖት የሚለውጥ ጭምር መሆኑን የሚያስገነዝብ ነው፡፡ ዐዋጁ እንደሚከተለው ነበር፡-
ስማ፣ ስማ፣ተሰማ የማይሰማ የእግዚአብሔር እና የወላዲት አምላክ ጠላት ነው፡፡ ስማ፣ ስማ ተሰማማ፣ የማይሰማ የእግዚአብሔርና የቤተክርስቲያን ጠላት ነው፡፡ ስማ፣ ስማ ተሰማማ፣ የማይሰማ የእግዚአብሔርን የንጉሡ ጠላት ነው፡፡ እግዚአብሔር ወሰን እንዲሆን የሰጠንን ባሕር አልፎ ሃይማኖት የሚለውጥና ሀገር የሚያጠፋ ጠላት መጥቶአል፡፡ እኔ ምኒልክ በእግዚአብሔር ርዳታ ሀገሬን ለጠላት አሳልፌ አልሰጥም፡፡ ያገሬ ሰው! ከአሁን ቀደመ የበደልኩህ አይመስለኝም፡፡ አንተም እስካሁን አላስቀየምኸኝም፡፡ ጉልበት ያለህ በጉልበትህ ርዳኝ፣ ጉልበት የሌለህ ለልጅህ፣ ለሚስትህ፣ ለሃይማኖትህ ስትል በኅዘን ርዳኝ፡፡ወስልተህ የቀረህ ግን ኋላ ትጣላኛለህ፣ አልተውልህም፡፡ ማርያምን ለዚህ አማላጅ የለኝም፡፡ ዘመቻዬም በጥቅምት ነው፡፡
ዐፄ ምኒልክ ዐዋጅን ካስነገሩ በኋላ በአዲስ አበባ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ተገኝተው ጸሎት ማድረሳቸውና ስእለት መሳላቸው የጦርነቱ መንፈሳዊ ዝግጅት አካልና ለቤተክርስቲያኗ ልዩ መልእክት የነበረው ነው፡፡ ስእለታቸውም “አምላከ ቅዱስ ጊዮርጊስ ድሉን ቢሰጠኝ ይህን የቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ሣር ክዳኑን ለውጬ ባማረ ሕንፃ አሠራዋለሁ ” የሚል ነበር፡፡ ይህንም ስእለታቸውን ከድል በኋላ ፈጽመውታል፡፡
የክተት ዐዋጁን ተከትሎም በሊቀ ጳጳሱ ብፁዕ አቡነ ማቴዎስና በዕጨጌ ወልደ ጊዮርጊስ በመላ ሀገሪቱ ጸሎት፣ ኀዘንና ምህላ ታወጀ፡፡ ከዚሁ ጋር በተያያዘ የቤተክርስቲያን አስተምህሮው ተጠናከሮ ቀጠለ፡፡ አገር ከሌለ ሃይማኖት የለም፣ ሃይማኖትና ነፃነትን ማጣት ሽንፈት ነው፣ ወደ ፈጣሪ ለአገርና ለሃይማኖት ታግሎ መሔድ ሰማዕትነት ነው፣ ኢትዮጵያን ያህል አገር ማጣት እግዚአብሔርን ከሚያህል ጌታ መለየት ሞት ነው፣ ስለ አገር፣ ሃይማኖትና ነጻነት መሞት ክብር ነው ወዘተ… የሚሉት ርእሰ ጉዳዮች አንኳር ጉዳዮች ነበሩ፡፡ ከዚያም
በመ/ር ጌታቸው በቀለ
✍️ ዐፄ ምኒልክ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን
ስዕለት ተሥለዋል፡፡
✍️ ብፁዕ አቡነ ማቴዎስና ዕጨጌ ወልደ ጊዮርጊስ በመላ ሀገሪቱ ጸሎት፣
ኀዘንና ምህላ ዐውጀው ነበር።
✍️ ከዘመቻው በፊት ዘማች አብያተክርስቲያናትም ተለይተዋል፣
✍️ በዘመቻውም ታቦት፣መስቀል፣ ንዋያተ ቅድሳት ጥላዎች እና
ድባቦች ይዘው ሊቃውንቱ እና ካህናት ዘምተዋል።
የዐድዋ ጦርነት የካቲት 23 ቀን በዕለተ ሰንበት በ6 ሰዓት ውስጥ በሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ተራዳኢነት፣ በጀግኖች አባቶቻችን አርበኝነት ተጋድሎ በኢትዮጵያ የበላይነትና ድል አድራጊነት ተጠናቀቀ፡፡
ይህንንም ድል በየዓመቱ ሀገራችን ኢትዮጵያ ታከብረዋለች፡፡ ዘንድሮም ለ129ኛ ዓመት ይከበራል፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንም በመናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን በታላቅ ድምቀት ታከብራለች፡፡ በዐድዋው ድል የቤተክርስቲያንን አስተዋጽኦ፣ የቅዱስ ጊዮርጊስን ተራዳኢነት በስፋት ታስተምራለች፡፡ ታሪኩን እንደሚከተለው እንመለከታለን፡-
የዐድዋን ድል
የዐድዋ ድል ለዘመናት ተከብሮ የኖረውን የኢትዮጵያን ሉዓላዊ ሀገርነትና ነፃነትን ከማረጋገጡም በላይ ለሀገራችን ዓለም አቀፍ ዝናን አጐናጽፏታል፡፡ የዐድዋ ድል ለኢትዮጵያውያን የትብብር፣ የአንድነት፣ የኩራትና የክብር ምንጭ ከመሆኑ ባሻገር፤ የድሉ ባለቤት የሆነችው ኢትዮጵያ ለጥቁሮች ነፃነትና የክብር ፋና ለመሆን በቅታለች፡፡ የዐድዋ ድል ምሳሌነት አፍሪካውያን በቅኝ ገዥዎቻቸው ላይ አንዲነሡ ምክንያት ሆኗል፣ ለፓን አፍሪካን እንቅስቃሴ መፋፋምም ጉልህ አስተዋጽኦ አበርከቷል፡፡ ከዚህ አልፎ የዐድዋ ድል ከነጮች ተጽዕኖ ነፃ የሆነ የጥቁሮች የሃይማኖት እንቅስቃሴ እንዲጀመር ምክንያት እስከ መሆን ደርሷል፡፡ ለአብነትም ኢትዮጵያኒዝም እየተባለ ይጠራ የነበረውና በተለይ በአሜሪካና በደቡብ አፍሪካ የነበረውን እንቅስቃሴ መጥቀስ ይቻላል፡፡
በዐድዋ ድል የቤተክርስቲያን ሚና
ለዐድዋ ድል መገኘት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሚና እጅግ የላቀ መሆኑ አጠያያቂ አይደለም፡፡ ይህች ጥንታዊ ቤተክርስቲያን በዐድዋ ጦርነት ወቅት ከመነሻው እስከ መጨረሻው፣ ከዘመቻው እስከ ድሉ፣ ከዋዜማው እስከ ጦርነቱ በመሪነትና በተሳታፊነት ነበረች፡፡ ቤተክርስቲያኗ ሕዝቡን በመቀስቀስ፣ አመራር በመስጠት፣ አብራ በመዝመት፣ የሥነ ልቦና ዝግጅት እንዲኖር በማድረግ፣ በጦርነቱ በመሳተፍ፣ መረጃ በመስጠትና በማስቀመጥ ባደረገችው አስተዋጽዖ ተወዳዳሪ አልነበራትም፡፡ በዐድዋ ጦርነት ወቅት ቤተክርስቲያኗ የነበራትን የላቀ ሚና ለመረዳት የዐፄ ምኒልክን የክተት ዐዋጅ መመልከት በቂ ነው፡፡ ዐዋጁ ጦርነቱ ከቤተክርስቲያን፣ ከእግዚአብሔር እና ከወላዲት አምላክ ጠላት ጋር እንደሆነና የመጣው ጠላት አገር የሚያፈርስ ብቻ ሳይሆን፤ ሃይማኖት የሚለውጥ ጭምር መሆኑን የሚያስገነዝብ ነው፡፡ ዐዋጁ እንደሚከተለው ነበር፡-
ስማ፣ ስማ፣ተሰማ የማይሰማ የእግዚአብሔር እና የወላዲት አምላክ ጠላት ነው፡፡ ስማ፣ ስማ ተሰማማ፣ የማይሰማ የእግዚአብሔርና የቤተክርስቲያን ጠላት ነው፡፡ ስማ፣ ስማ ተሰማማ፣ የማይሰማ የእግዚአብሔርን የንጉሡ ጠላት ነው፡፡ እግዚአብሔር ወሰን እንዲሆን የሰጠንን ባሕር አልፎ ሃይማኖት የሚለውጥና ሀገር የሚያጠፋ ጠላት መጥቶአል፡፡ እኔ ምኒልክ በእግዚአብሔር ርዳታ ሀገሬን ለጠላት አሳልፌ አልሰጥም፡፡ ያገሬ ሰው! ከአሁን ቀደመ የበደልኩህ አይመስለኝም፡፡ አንተም እስካሁን አላስቀየምኸኝም፡፡ ጉልበት ያለህ በጉልበትህ ርዳኝ፣ ጉልበት የሌለህ ለልጅህ፣ ለሚስትህ፣ ለሃይማኖትህ ስትል በኅዘን ርዳኝ፡፡ወስልተህ የቀረህ ግን ኋላ ትጣላኛለህ፣ አልተውልህም፡፡ ማርያምን ለዚህ አማላጅ የለኝም፡፡ ዘመቻዬም በጥቅምት ነው፡፡
ዐፄ ምኒልክ ዐዋጅን ካስነገሩ በኋላ በአዲስ አበባ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ተገኝተው ጸሎት ማድረሳቸውና ስእለት መሳላቸው የጦርነቱ መንፈሳዊ ዝግጅት አካልና ለቤተክርስቲያኗ ልዩ መልእክት የነበረው ነው፡፡ ስእለታቸውም “አምላከ ቅዱስ ጊዮርጊስ ድሉን ቢሰጠኝ ይህን የቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ሣር ክዳኑን ለውጬ ባማረ ሕንፃ አሠራዋለሁ ” የሚል ነበር፡፡ ይህንም ስእለታቸውን ከድል በኋላ ፈጽመውታል፡፡
የክተት ዐዋጁን ተከትሎም በሊቀ ጳጳሱ ብፁዕ አቡነ ማቴዎስና በዕጨጌ ወልደ ጊዮርጊስ በመላ ሀገሪቱ ጸሎት፣ ኀዘንና ምህላ ታወጀ፡፡ ከዚሁ ጋር በተያያዘ የቤተክርስቲያን አስተምህሮው ተጠናከሮ ቀጠለ፡፡ አገር ከሌለ ሃይማኖት የለም፣ ሃይማኖትና ነፃነትን ማጣት ሽንፈት ነው፣ ወደ ፈጣሪ ለአገርና ለሃይማኖት ታግሎ መሔድ ሰማዕትነት ነው፣ ኢትዮጵያን ያህል አገር ማጣት እግዚአብሔርን ከሚያህል ጌታ መለየት ሞት ነው፣ ስለ አገር፣ ሃይማኖትና ነጻነት መሞት ክብር ነው ወዘተ… የሚሉት ርእሰ ጉዳዮች አንኳር ጉዳዮች ነበሩ፡፡ ከዚያም