በአሜሪካ አላስካ ግዛት10 ሰዎችን የጫነ አውሮፕላን መጥፋቱ ተገለፀ።
የቤሪንግ አየር መንገድ ንብረት የሆነው ሴስና ካራቫን አውሮፕላን አናላክሌት ከተባለ አካባቢ ወደ ኖም እያቀና ሳለ መጥፋቱ ነው የተገለፀው።
አውሮፕላኑ 9 ሰዎችን ያሳፈረ ሲሆን፤ በ1 ፓይለት አብራሪነት እየተጓዘ እንደነበረም ተጠቁሟል።
የአየር መንገዱ ባለሙያዎች ከአብራሪው ጋር ለመጨረሻ ጊዜ ያደረጉት የመረጃ ልውውጥ አብራሪው የማረፊያ ቦታ እስኪስተካከል አየር ላይ ለመቆየት መወሰኑን ሲያሳውቅ ነው ተብሏል። ይህም ትናንት ከቀኑ 10 ሰዓት ላይ ነበር። እስከ አሁን የጠፋውን አውሮፕላን ለማግኘት በአየር እና በምድር አሰሳ እየተደረገ ይገኛል።
የአላስካ ግዛት ባላት ከባድ የአየር ንብረት ሳቢያ በርካታ አውሮፕላኖች የተሰወሩባት አካባቢ መሆኗ ይነገራል።
የቤሪንግ አየር መንገድ ንብረት የሆነው ሴስና ካራቫን አውሮፕላን አናላክሌት ከተባለ አካባቢ ወደ ኖም እያቀና ሳለ መጥፋቱ ነው የተገለፀው።
አውሮፕላኑ 9 ሰዎችን ያሳፈረ ሲሆን፤ በ1 ፓይለት አብራሪነት እየተጓዘ እንደነበረም ተጠቁሟል።
የአየር መንገዱ ባለሙያዎች ከአብራሪው ጋር ለመጨረሻ ጊዜ ያደረጉት የመረጃ ልውውጥ አብራሪው የማረፊያ ቦታ እስኪስተካከል አየር ላይ ለመቆየት መወሰኑን ሲያሳውቅ ነው ተብሏል። ይህም ትናንት ከቀኑ 10 ሰዓት ላይ ነበር። እስከ አሁን የጠፋውን አውሮፕላን ለማግኘት በአየር እና በምድር አሰሳ እየተደረገ ይገኛል።
የአላስካ ግዛት ባላት ከባድ የአየር ንብረት ሳቢያ በርካታ አውሮፕላኖች የተሰወሩባት አካባቢ መሆኗ ይነገራል።