👉 ከዛሬ ጀምሮ ከአያት 49 ወደ ፊጋ የሚወስደው መንገድ በከፊል ይዘጋል ተባለ።
የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለሥልጣን ከአያት 49 ወደ ፊጋ በሚወስደው መንገድ 72 ድልድይ አካባቢ የመንገድ ጥገና ሥራ ሊካሄድ በመሆኑ መንገዱ ከዛሬ ሰኞ ነሐሴ 18 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በከፊል ለትራፊክ ዝግ እንደሚደረግ አስታውቋል ።
ከአያት 49 ወደ ፊጋ በሚወስደው መንገድ ላይ 72 ድልድይ አካባቢ የሚካሄደው የመንገድ ጥገና ሥራ በፍጥነት እንዲጠናቀቅ መንገዱን በከፊል ለትራፊክ መዝጋት እንዳስፈለገ ገልጸዋል።
የጥገና ሥራው በሚካሄድበት ወቅት በአካባቢው የትራፊክ መጨናነቅ ሊፈጠር እንደሚችል የተጠበቀ ሲሆን ለመንገድ ተጠቃሚዎች እንቅስቃሴ ችግር እንዳይፈጠር አሽከርካሪዎች ቀድመው የጉዞ እቅዳቸውን እንዲያስተካክሉ ባለሥልጣኑ አሳስቧል።
በመሆኑም አሽከርካሪዎች በ72 ድልድይ አካባቢ ሲያልፉ ተጨማሪ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ የትራፊክ መመሪያዎችን እንዲከተሉና በተቻለ መጠን አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ ባለሥልጣን መስሪያ ቤቱ ጥሪ አቅርቧል።
የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለሥልጣን ከአያት 49 ወደ ፊጋ በሚወስደው መንገድ 72 ድልድይ አካባቢ የመንገድ ጥገና ሥራ ሊካሄድ በመሆኑ መንገዱ ከዛሬ ሰኞ ነሐሴ 18 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በከፊል ለትራፊክ ዝግ እንደሚደረግ አስታውቋል ።
ከአያት 49 ወደ ፊጋ በሚወስደው መንገድ ላይ 72 ድልድይ አካባቢ የሚካሄደው የመንገድ ጥገና ሥራ በፍጥነት እንዲጠናቀቅ መንገዱን በከፊል ለትራፊክ መዝጋት እንዳስፈለገ ገልጸዋል።
የጥገና ሥራው በሚካሄድበት ወቅት በአካባቢው የትራፊክ መጨናነቅ ሊፈጠር እንደሚችል የተጠበቀ ሲሆን ለመንገድ ተጠቃሚዎች እንቅስቃሴ ችግር እንዳይፈጠር አሽከርካሪዎች ቀድመው የጉዞ እቅዳቸውን እንዲያስተካክሉ ባለሥልጣኑ አሳስቧል።
በመሆኑም አሽከርካሪዎች በ72 ድልድይ አካባቢ ሲያልፉ ተጨማሪ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ የትራፊክ መመሪያዎችን እንዲከተሉና በተቻለ መጠን አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ ባለሥልጣን መስሪያ ቤቱ ጥሪ አቅርቧል።