የውጭ ሀገር ስራ ስምሪት አዋጅ በአራት ዓመት ውስጥ ለሁለተኛ ጊዜ ተሻሻለበውጭ ሀገር ለስራ የሚሰማሩ ኢትዮጵያውያንን የሚመለከተው አዋጅ፤ ከአራት ዓመት በኋላ በድጋሚ ማሻሻያ ተደረገበት። የአዋጅ ማሻሻያው በውጭ ሀገር ለስራ የሚሰማሩ ዜጎች “መብታቸው፣ ደህንነታቸው እና ክብራቸው በዘላቂነት መጠበቁን ለማረጋገጥ” “እንዲያስችል ሆኖ የተዘጋጀ ነው” ተብሏል።
በ2008 ዓ.ም የወጣው “የኢትዮጵያ የውጭ ሀገር ስምሪት አዋጅ” ሰራተኛን በውጭ ሀገር ለስራ ማሰማራት የሚቻለው፤ “በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግስት እና በተቀባይ ሀገር መካከል የሁለትዮሽ ስምምነት ሲኖር ብቻ እንደሆነ” የሚገድብ ድንጋጌ ነበረው። በ2013 ዓ.ም. የጸደቀው የዚህ አዋጅ ማሻሻያ በበኩሉ፤ በውጭ ሀገራት “የሰለጠነ የሰው ኃይል” ለሚፈለግበት ስራ ተጨማሪ ሁለት የስምምነት አማራጮችን አካትቷል።
የመጀመሪያው አማራጭ፤ ጉዳዩ በሚመለከተው የኢትዮጵያ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት እና በተቀባይ ሀገር ከሚገኘው አቻ ስልጣን ካለው የመንግስት ተቋም ጋር “የሁለትዮሽ ስምምነት” ወይም “መግባቢያ ሰነድ” ሲኖር ሰራተኛን ማሰማራት እንደሚቻል ይፈቅዳል። ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ተመሳሳይ ስምምነት በውጭ ሀገር ከሚገኝ “እውቅና ካለው አሰሪ ኩባንያ” ጋር ከፈጸመም፤ ኢትዮጵያውያን ሰራተኞችን መላክ እንደሚቻል በአዋጁ ማሻሻያው ተደንግጓል።
“የሰለጠነ የሰው ኃይል የሚሰማራበት ስራ አፈላልጎ ያገኘ ኤጀንሲ፤ በተቀባይ ሀገር መንግስት እውቅና ካለው ቀጣሪ አሰሪ ኩባንያ ጋር የስራ ስምሪት ስምምነት እንዲፈጽም” ጉዳዩ የሚመለከተው ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ሊፈቅድ እንደሚችልም በ2013ቱ የአዋጅ ማሽሻያ ላይ ተቀምጧል።
🔴 ለዝርዝሩ ➡️
https://ethiopiainsider.com/2025/16038/@EthiopiaInsiderNews