የባሕር በር ጥያቄ የሀገርና የሕዝብ አጀንዳ እንጂ የመንግሥት ብቻ አይደለም
******
(ኢ ፕ ድ)
የባሕር በር ጥያቄ የሀገርና የሕዝብ አጀንዳ እንጂ የመንግሥት ብቻ ስላልሆነ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች በባሕር በር ጉዳይ ላይ ከመንግሥት ጎን መቆም እንዳለባቸው የኢትዮጵያ ዲሞክራቲክ ህብረት ፓርቲ ሊቀመንበር አቶ ገብሩ በርሄ ገለፁ፡፡
ሊቀመንበሩ ለኢፕድ እንደገለጹት፤ ፓርቲያቸው በኢትዮጵያ የባሕር በር ማግኘት ዙሪያ ከ1984ዓ.ም አንስቶ የተለያየ ጥረት ሲያደርግ ቆይቷል። መሰል አቋም ካላቸው ፓርቲዎች ጋርም በጋራ በመሆን ፊርማ የማሰባሰብ ሥራ ሲሠራ እንደነበር አስታውሰዋል።
አንዳንድ ሀገራት ኢትዮጵያ ከሶማሊላንድ ጋር የተደረገውን የባሕር በር ስምምነት እንዳይሳካ ለማድረግ ሲንቀሳቀሱ እንደነበር ገልፀው፤ እንዲህ ያለው የታሪካዊ ጠላቶቻችን እንቅስቃሴ ለእኛ አዲስ አይደለም ብለዋል። https://press.et/?p=146933
******
(ኢ ፕ ድ)
የባሕር በር ጥያቄ የሀገርና የሕዝብ አጀንዳ እንጂ የመንግሥት ብቻ ስላልሆነ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች በባሕር በር ጉዳይ ላይ ከመንግሥት ጎን መቆም እንዳለባቸው የኢትዮጵያ ዲሞክራቲክ ህብረት ፓርቲ ሊቀመንበር አቶ ገብሩ በርሄ ገለፁ፡፡
ሊቀመንበሩ ለኢፕድ እንደገለጹት፤ ፓርቲያቸው በኢትዮጵያ የባሕር በር ማግኘት ዙሪያ ከ1984ዓ.ም አንስቶ የተለያየ ጥረት ሲያደርግ ቆይቷል። መሰል አቋም ካላቸው ፓርቲዎች ጋርም በጋራ በመሆን ፊርማ የማሰባሰብ ሥራ ሲሠራ እንደነበር አስታውሰዋል።
አንዳንድ ሀገራት ኢትዮጵያ ከሶማሊላንድ ጋር የተደረገውን የባሕር በር ስምምነት እንዳይሳካ ለማድረግ ሲንቀሳቀሱ እንደነበር ገልፀው፤ እንዲህ ያለው የታሪካዊ ጠላቶቻችን እንቅስቃሴ ለእኛ አዲስ አይደለም ብለዋል። https://press.et/?p=146933