TGStat
TGStat
Type to search
Advanced channel search
  • flag English
    Site language
    flag Russian flag English flag Uzbek
  • Sign In
  • Catalog
    Channels and groups catalog Search for channels
    Add a channel/group
  • Ratings
    Rating of channels Rating of groups Posts rating
    Ratings of brands and people
  • Analytics
  • Search by posts
  • Telegram monitoring
Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/

22 Aug, 13:20

Open in Telegram Share Report

Prev Next
ሀገራዊ ምክክሩ ለቀጣናው ሰላምና ዘላቂ ዕድገት ወሳኝ ሚና እንዳለው ኡሁሩ ኬንያታ ገለጹ

+++++++++++++++++

#ጋዜጣ_ፕላስ- ሀገራዊ ምክክሩ ለቀጣናው ሰላምና ዘላቂ ዕድገት ወሳኝ ሚና እንዳለው የቀድሞው የኬንያ ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ገለጹ። ምክክሩ ብዝሃ ድምጾች የተሰሙበትና የሀገር ፍቅር ስሜት የተንጸባረቀበት እንደሆነም ጠቅሰዋል።

የቀድሞው የኬንያ ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ በሀገራዊ ምክክር የመዝጊያ ሥነ-ሥርዓት ላይ ባደረጉት ንግግር፤ ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ነፃነት ምልክት ከመሆኗም በላይ "ኢትዮጵያ በአፍሪካ ውስጥ የምትገኝ አገር ብቻ ሳትሆን የጥንታዊ የአፍሪካ ሥልጣኔ መገለጫም ናት" ብለዋል።

ኢትዮጵያ ለሉዓላዊነቷና ለአንድነቷ በየጊዜው ያሳየችው ጥረት ለመላው አፍሪካውያን አብነት መሆኑን የጠቆሙት ፕሬዚዳንቱ፤ የዓድዋ ድል የኢትዮጵያ ታሪክ ቢሆንም የሁሉም አፍሪካውያን የጋራ ድል መሆኑን አብራርተዋል።

ኢትዮጵያ በባህል፣ በቋንቋ፣ በታሪክ፣ በሥልጣኔ እንዲሁም በተፈጥሮ ሀብት የበለጸገች አገር መሆኗን ገልጸው፤ ለአብነትም የአክሱም ሥልጣኔን፣ የታላቁን አባይ ወንዝ፣ የዓድዋን ድልና የልዩ ልዩ ብሔር ብሔረሰቦችን ባህላዊ የዳኝነትና የአስተዳደር ሥርዓቶች ጠቅሰዋል።

«አዲስ አበባ የኢትዮጵያ ብቻ ሳትሆን የመላው አህጉሪቱ መዲና ናት» ያሉት የቀድሞው የኬንያ ፕሬዚዳንት፤ የተካሄደው ሀገራዊ ምክክር በአገሪቱም ሆነ በቀጣናው ዘላቂ ሰላምና ዕድገት ለማረጋገጥ ወሳኝ ሚና እንደሚኖረው አስረድተዋል።

1.4k 0 1 15
Catalog
Channels and groups catalog Channels compilations Search for channels Add a channel/group
Ratings
Rating of Telegram channels Rating of Telegram groups Posts rating Ratings of brands and people
API
API statistics Search API of posts API Callback
Our channels
@TGStat @TGStat_Chat @telepulse @TGStatAPI
Read
Академия TGStat Telegram Research 2019 Telegram Research 2021 Telegram Research 2023
Contacts
Справочный центр Support Email Jobs
Miscellaneous
Terms and conditions Privacy policy Public offer
Our bots
@TGStat_Bot @SearcheeBot @TGAlertsBot @tg_analytics_bot @TGStatChatBot