ሀገራዊ ምክክሩ ለቀጣናው ሰላምና ዘላቂ ዕድገት ወሳኝ ሚና እንዳለው ኡሁሩ ኬንያታ ገለጹ
+++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ- ሀገራዊ ምክክሩ ለቀጣናው ሰላምና ዘላቂ ዕድገት ወሳኝ ሚና እንዳለው የቀድሞው የኬንያ ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ገለጹ። ምክክሩ ብዝሃ ድምጾች የተሰሙበትና የሀገር ፍቅር ስሜት የተንጸባረቀበት እንደሆነም ጠቅሰዋል።
የቀድሞው የኬንያ ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ በሀገራዊ ምክክር የመዝጊያ ሥነ-ሥርዓት ላይ ባደረጉት ንግግር፤ ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ነፃነት ምልክት ከመሆኗም በላይ "ኢትዮጵያ በአፍሪካ ውስጥ የምትገኝ አገር ብቻ ሳትሆን የጥንታዊ የአፍሪካ ሥልጣኔ መገለጫም ናት" ብለዋል።
ኢትዮጵያ ለሉዓላዊነቷና ለአንድነቷ በየጊዜው ያሳየችው ጥረት ለመላው አፍሪካውያን አብነት መሆኑን የጠቆሙት ፕሬዚዳንቱ፤ የዓድዋ ድል የኢትዮጵያ ታሪክ ቢሆንም የሁሉም አፍሪካውያን የጋራ ድል መሆኑን አብራርተዋል።
ኢትዮጵያ በባህል፣ በቋንቋ፣ በታሪክ፣ በሥልጣኔ እንዲሁም በተፈጥሮ ሀብት የበለጸገች አገር መሆኗን ገልጸው፤ ለአብነትም የአክሱም ሥልጣኔን፣ የታላቁን አባይ ወንዝ፣ የዓድዋን ድልና የልዩ ልዩ ብሔር ብሔረሰቦችን ባህላዊ የዳኝነትና የአስተዳደር ሥርዓቶች ጠቅሰዋል።
«አዲስ አበባ የኢትዮጵያ ብቻ ሳትሆን የመላው አህጉሪቱ መዲና ናት» ያሉት የቀድሞው የኬንያ ፕሬዚዳንት፤ የተካሄደው ሀገራዊ ምክክር በአገሪቱም ሆነ በቀጣናው ዘላቂ ሰላምና ዕድገት ለማረጋገጥ ወሳኝ ሚና እንደሚኖረው አስረድተዋል።
+++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ- ሀገራዊ ምክክሩ ለቀጣናው ሰላምና ዘላቂ ዕድገት ወሳኝ ሚና እንዳለው የቀድሞው የኬንያ ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ገለጹ። ምክክሩ ብዝሃ ድምጾች የተሰሙበትና የሀገር ፍቅር ስሜት የተንጸባረቀበት እንደሆነም ጠቅሰዋል።
የቀድሞው የኬንያ ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ በሀገራዊ ምክክር የመዝጊያ ሥነ-ሥርዓት ላይ ባደረጉት ንግግር፤ ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ነፃነት ምልክት ከመሆኗም በላይ "ኢትዮጵያ በአፍሪካ ውስጥ የምትገኝ አገር ብቻ ሳትሆን የጥንታዊ የአፍሪካ ሥልጣኔ መገለጫም ናት" ብለዋል።
ኢትዮጵያ ለሉዓላዊነቷና ለአንድነቷ በየጊዜው ያሳየችው ጥረት ለመላው አፍሪካውያን አብነት መሆኑን የጠቆሙት ፕሬዚዳንቱ፤ የዓድዋ ድል የኢትዮጵያ ታሪክ ቢሆንም የሁሉም አፍሪካውያን የጋራ ድል መሆኑን አብራርተዋል።
ኢትዮጵያ በባህል፣ በቋንቋ፣ በታሪክ፣ በሥልጣኔ እንዲሁም በተፈጥሮ ሀብት የበለጸገች አገር መሆኗን ገልጸው፤ ለአብነትም የአክሱም ሥልጣኔን፣ የታላቁን አባይ ወንዝ፣ የዓድዋን ድልና የልዩ ልዩ ብሔር ብሔረሰቦችን ባህላዊ የዳኝነትና የአስተዳደር ሥርዓቶች ጠቅሰዋል።
«አዲስ አበባ የኢትዮጵያ ብቻ ሳትሆን የመላው አህጉሪቱ መዲና ናት» ያሉት የቀድሞው የኬንያ ፕሬዚዳንት፤ የተካሄደው ሀገራዊ ምክክር በአገሪቱም ሆነ በቀጣናው ዘላቂ ሰላምና ዕድገት ለማረጋገጥ ወሳኝ ሚና እንደሚኖረው አስረድተዋል።