#በአዋጅ ቁጥር 1234/2013 ዓ.ም አንቀጽ 38 ንዑስ አንቀይ 2 ላይ በግልጽ እንደተመለከተው የፌዴራል ፍርድ ቤቶች በየዓመቱ ከነሐሴ 1 ቀን እስከ መስከረም 30 ድረስ ዝግ ይሆናሉ።
#በርካቶቻችን ግን የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ዝግ ይሆናሉ ሲባል ክርችም ተደርጎ እንደሚዘጋ ተቋም አድርገን በስህተት እንረዳለን፤ ለዛም ነው ትላንት በችሎት ገጠመኝ በርካታ ባለጉዳዮች ፍርድ ቤት ሊዘጋ ነውና ኧረ በፍጥነት ዕግድ ስጡን! ፋይል ክፈቱልን! የውሳኔ ግልባጭ ካልተሰጠን... እያሉ ሲጋፉ የተስተዋለው።
በዚህ የዕረፍት ወቅት የሚሰሩ ሥራዎች፦
#የዋስትና
#የእጅ ከፍንጅ ወንጀሎች
#አካል ነፃ የማውጣት ክሶች
#በመንግሥትና በሕዝብ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ሊያደርሱ የሚችሉ ጉዳዮች
#የቀለብ ጉዳዮች እና ሌሎች በበቂ ምክንያት በአስቸኳይ ሊታዩ የሚገባቸው ጉዳዮች በተረኛ ችሎት በመደበኛነት ይስተናገዳሉ።
ሌሎች ጉዳዮችስ?
#ትልቁ አለመረዳት እዚህ ጋር ነው፤ የፌዴራል ፍርድ ቤቶች በከፊል ዝግ በሚሆኑባቸው ወቅቶች ፋይል መክፈትንና ዕግድ መጠየቅን ሚከለክል ድንጋጌ አልተቀመጠም።
#ያለዎት ጉዳይ ቀጣይ ዓመት ጥቅምት ወር ፋይል ቢከፈት ሚፈጠርብዎት የመብት ጥሰት ከሌለ ፋይል ሳይከፍቱ መቆየት ይችላሉ፤ ነገር ግን የለም ፋይል ከፍቼ ቀጠሮው ለቀጣይ ዓመት ይሻገርልኝ ካሉም መብትዎ ነውና የተሳሳተውን አረዳድ ያርሙ።
#በስተመጨረሻ በአዲስ አበባ ደረጃ የከተማው የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤቶች እና ማኅበራዊ ፍርድ ቤቶች መደበኛ ሥራቸውን እንደሚያከናውኑ አይርሱ።
⚖️ይግባኝ መብት ነው!!!
©️ጠበቃ ቴዎድሮስ አብዲሳ
☎️ 09 10 61 69 50
በማንኛውም ፌዴራል ፍርድ ቤት
ጠበቃና የሕግ አማካሪ
#በርካቶቻችን ግን የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ዝግ ይሆናሉ ሲባል ክርችም ተደርጎ እንደሚዘጋ ተቋም አድርገን በስህተት እንረዳለን፤ ለዛም ነው ትላንት በችሎት ገጠመኝ በርካታ ባለጉዳዮች ፍርድ ቤት ሊዘጋ ነውና ኧረ በፍጥነት ዕግድ ስጡን! ፋይል ክፈቱልን! የውሳኔ ግልባጭ ካልተሰጠን... እያሉ ሲጋፉ የተስተዋለው።
በዚህ የዕረፍት ወቅት የሚሰሩ ሥራዎች፦
#የዋስትና
#የእጅ ከፍንጅ ወንጀሎች
#አካል ነፃ የማውጣት ክሶች
#በመንግሥትና በሕዝብ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ሊያደርሱ የሚችሉ ጉዳዮች
#የቀለብ ጉዳዮች እና ሌሎች በበቂ ምክንያት በአስቸኳይ ሊታዩ የሚገባቸው ጉዳዮች በተረኛ ችሎት በመደበኛነት ይስተናገዳሉ።
ሌሎች ጉዳዮችስ?
#ትልቁ አለመረዳት እዚህ ጋር ነው፤ የፌዴራል ፍርድ ቤቶች በከፊል ዝግ በሚሆኑባቸው ወቅቶች ፋይል መክፈትንና ዕግድ መጠየቅን ሚከለክል ድንጋጌ አልተቀመጠም።
#ያለዎት ጉዳይ ቀጣይ ዓመት ጥቅምት ወር ፋይል ቢከፈት ሚፈጠርብዎት የመብት ጥሰት ከሌለ ፋይል ሳይከፍቱ መቆየት ይችላሉ፤ ነገር ግን የለም ፋይል ከፍቼ ቀጠሮው ለቀጣይ ዓመት ይሻገርልኝ ካሉም መብትዎ ነውና የተሳሳተውን አረዳድ ያርሙ።
#በስተመጨረሻ በአዲስ አበባ ደረጃ የከተማው የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤቶች እና ማኅበራዊ ፍርድ ቤቶች መደበኛ ሥራቸውን እንደሚያከናውኑ አይርሱ።
⚖️ይግባኝ መብት ነው!!!
©️ጠበቃ ቴዎድሮስ አብዲሳ
☎️ 09 10 61 69 50
በማንኛውም ፌዴራል ፍርድ ቤት
ጠበቃና የሕግ አማካሪ