የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በጨረታ ለመሸጥ ያወጣውን 50 ሚሊዮን ዶላር 12 ባንኮች ለአንዱ ዶላር በአማካይ 31.7095 ዋጋ በማቅረብ አሸንፈው መግዛታቸውን በድረ-ገጹ ላይ አሳውቋል። ባንኮች አንዱን ዶላር ለመግዛት ያቀረቡት አማካይ የመጫረቻ ዋጋ በቅርቡ ከወጣው የአማካይ የጨረታ ዋጋ ጋር ሲነጻጸር የ4 ብር ገደማ ቅናሽ አሳይቷል።
ብሔራዊ ባንኩ ቀጣዩን ጨረታ በሚቀጥለው ሁለት ሳምንት ውስጥ እንደሚያደርግና የጨረታውን ማስታወቂያ ከጨረታው ቀን አንድ ቀን አስቀድሞ እንደሚያሳውቅ ገልጿል።
ብሔራዊ ባንኩ ቀጣዩን ጨረታ በሚቀጥለው ሁለት ሳምንት ውስጥ እንደሚያደርግና የጨረታውን ማስታወቂያ ከጨረታው ቀን አንድ ቀን አስቀድሞ እንደሚያሳውቅ ገልጿል።