" ከነፍሳችን በላይ አብልጠን በምንወዳቸው ውዱ ነብያችን ክብር የማንደራደር መሆኑን ሁሉም ሊያውቅ ይገባል።" ኡስታዝ አቡበከር አህመድ
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት የፕሬዝዳንት ፅ/ቤት ሀላፊ ኡስታዝ አቡበከር አህመድ ከሰሞኑ በተለያዩ ሶሻል ሚዲያዎች ድምበር የሚያልፉ ግለሰቦችን አስመልክቶ መልዕክት አስተላልፈዋል።
የፉሪ ክፍለ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ም/ቤት ከኢትዮጵያ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል ጋር በመተባበር የተዘጋጀ የዳዕዋ መድረክ በርካታ ሙስሊሞች በተገኙበት መልዕክት ያስተላለፉት ኡስታዝ አቡበከር አህመድ "ከነፍሳችን በላይ አብልጠን በምንወዳቸው ውዱ ነብያችን ክብር የማንደራደር መሆኑን ሁሉም ሊያውቅ ይገባል" ሲሉ ተናግረዋል።
"እኛ እምነታችን በምናስተምርበት ወቅት ፈፅሞ የሰዎች እምነት ላይ ድንበር አናልፍም እስልምናም ያንን አያዘንም ያሉ ሲሆን ሌሎች የእምነት ተቋማትም ድንበር የሚያልፍ ግለሰቦችን ተው ሊሉ ይገባል" ብለዋል።
"እንደ ተቋም በህግ መሄድ እስካለብን ጥግ ድረስ እንሄዳለን ያሉ ሲሆን ሙስሊሙ ማህበረሰብ በተለይ ወጣቱ በሰላማዊ መንገድ እምነቱን ማስከበር አለበት" ሲሉ ገልፀዋል።
ዘገባው የሀሩን ሚዲያ ነው
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት የፕሬዝዳንት ፅ/ቤት ሀላፊ ኡስታዝ አቡበከር አህመድ ከሰሞኑ በተለያዩ ሶሻል ሚዲያዎች ድምበር የሚያልፉ ግለሰቦችን አስመልክቶ መልዕክት አስተላልፈዋል።
የፉሪ ክፍለ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ም/ቤት ከኢትዮጵያ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል ጋር በመተባበር የተዘጋጀ የዳዕዋ መድረክ በርካታ ሙስሊሞች በተገኙበት መልዕክት ያስተላለፉት ኡስታዝ አቡበከር አህመድ "ከነፍሳችን በላይ አብልጠን በምንወዳቸው ውዱ ነብያችን ክብር የማንደራደር መሆኑን ሁሉም ሊያውቅ ይገባል" ሲሉ ተናግረዋል።
"እኛ እምነታችን በምናስተምርበት ወቅት ፈፅሞ የሰዎች እምነት ላይ ድንበር አናልፍም እስልምናም ያንን አያዘንም ያሉ ሲሆን ሌሎች የእምነት ተቋማትም ድንበር የሚያልፍ ግለሰቦችን ተው ሊሉ ይገባል" ብለዋል።
"እንደ ተቋም በህግ መሄድ እስካለብን ጥግ ድረስ እንሄዳለን ያሉ ሲሆን ሙስሊሙ ማህበረሰብ በተለይ ወጣቱ በሰላማዊ መንገድ እምነቱን ማስከበር አለበት" ሲሉ ገልፀዋል።
ዘገባው የሀሩን ሚዲያ ነው