#የእንቢታሽ ሱሰኛ!
(ሚካኤል አስጨናቂ)
አንቺን በማሰብ ውስጥ መደሰት ለምጄ
ፍቅርሽ ሱስ ሆኖብኝ ... ማንነቴን ክጄ
ባንቺ መወድስ ስም ክታብ አሰርቼ
ስምሽን አንግቼ …
እንደ አሞራ ዙሬሽ ፣ አንዣብቤ በላይ
አንቺን ሳይሽ ፣ ‘ዋይ ፣ ዋይ …’
አጃኢብ ነው መቼም!
ስትሄጅ ተራመድሁ... ስትቆሚ ቆሜ
ባንቺ ስፍር ልኬት.. .በጠርዝ ተመድሜ
ከዕድሜ ከዘመኔ ፣ ዓመታት ቆንጥሬ
ከእንቢታሽ ጋራ ፣ በእልህ ሰክሬ
ስንኞችን ጭሬ.. .
አንቺን በመጀንጀንጀን ፣ ልማድ ተጠፍሬ
በሚጣፍጥ ህመም ...
ብቻዬን በአርምሞ ፣ ስብሰለስል ኖሬ
ከሀሳቤ ማግስት ... በስንኜ ድርድር
ቃላት ድል ነስተውሽ ፣ በኃይላቸው በትር
እኔም በተራዬ ፣ መፈቀር ስጀምር
“ፍቅርህን ተቀበልሁ” ያልሽኝ ጊዜ ‘ለታ
ፍቅርሽ ጥሎኝ ጠፋ ፣ ትዝታሽ ተረታ።
(እንቢ በይኝ ዳግም
እልህን ላጣጥም ። )
@getem
@getem
@getem
(ሚካኤል አስጨናቂ)
አንቺን በማሰብ ውስጥ መደሰት ለምጄ
ፍቅርሽ ሱስ ሆኖብኝ ... ማንነቴን ክጄ
ባንቺ መወድስ ስም ክታብ አሰርቼ
ስምሽን አንግቼ …
እንደ አሞራ ዙሬሽ ፣ አንዣብቤ በላይ
አንቺን ሳይሽ ፣ ‘ዋይ ፣ ዋይ …’
አጃኢብ ነው መቼም!
ስትሄጅ ተራመድሁ... ስትቆሚ ቆሜ
ባንቺ ስፍር ልኬት.. .በጠርዝ ተመድሜ
ከዕድሜ ከዘመኔ ፣ ዓመታት ቆንጥሬ
ከእንቢታሽ ጋራ ፣ በእልህ ሰክሬ
ስንኞችን ጭሬ.. .
አንቺን በመጀንጀንጀን ፣ ልማድ ተጠፍሬ
በሚጣፍጥ ህመም ...
ብቻዬን በአርምሞ ፣ ስብሰለስል ኖሬ
ከሀሳቤ ማግስት ... በስንኜ ድርድር
ቃላት ድል ነስተውሽ ፣ በኃይላቸው በትር
እኔም በተራዬ ፣ መፈቀር ስጀምር
“ፍቅርህን ተቀበልሁ” ያልሽኝ ጊዜ ‘ለታ
ፍቅርሽ ጥሎኝ ጠፋ ፣ ትዝታሽ ተረታ።
(እንቢ በይኝ ዳግም
እልህን ላጣጥም ። )
@getem
@getem
@getem