የድምፃዊ ዮሐና አልበም ተለቀቀ
የድምፃዊ ዮሐና አዲስ አልበም ዛሬ ጥር 23 2017 ዓ.ም በቀኑ 8:00 ጀምሮ ለአድማጮች ቀርቧል።
ድምፃዊ ዮሐና 'ሃሎ' የሚል መጠሪያ ያለውን እና 10 ሙዚቃዎች ያካተተውን አዲስ አልበሙን እንደለቀቀ ኤቨንት አዲስ ሚዲያ ተመልክቷል።
በዚህ አዲስ አልበም ዮሐና ከሰራቸው ሙዚቃዎች መካከል 'ታማ' በሚል ርዕስ ያቀነቀነው ሙዚቃ ከዮሐና ጋር ጥብቅ ቁርኝት ላላት መቐለ ከተማ የተፃፈ የፍቅር ደብዳቤ እንደሆነ ተነግሯል።
ግጥም እና ዜማ ሙሉ በሚባል ደረጃ ራሱ ዮሐና እንደሰራው እና አርቲስት ሳምቮድ፣ ዮርዳኖስ (ጆጆ) በአልበሙ ውስጥ ተሳትፎ ካደረጉት መካከል መሆናቸው ተገልጿል ።
በሙዚቃ ቅንብሩ እና ሚክሲንግ ሃይፐር ዜማ እና ማሩ አለማየሁ (ማርቭል) ሲሳተፉበት በማስተሪንግ ላይ ደግሞ ኪሩቤል ተስፋዬ ተሳትፈዋል።
የድምፃዊ ዮሐና አዲስ አልበም ዛሬ ጥር 23 2017 ዓ.ም በቀኑ 8:00 ጀምሮ ለአድማጮች ቀርቧል።
ድምፃዊ ዮሐና 'ሃሎ' የሚል መጠሪያ ያለውን እና 10 ሙዚቃዎች ያካተተውን አዲስ አልበሙን እንደለቀቀ ኤቨንት አዲስ ሚዲያ ተመልክቷል።
በዚህ አዲስ አልበም ዮሐና ከሰራቸው ሙዚቃዎች መካከል 'ታማ' በሚል ርዕስ ያቀነቀነው ሙዚቃ ከዮሐና ጋር ጥብቅ ቁርኝት ላላት መቐለ ከተማ የተፃፈ የፍቅር ደብዳቤ እንደሆነ ተነግሯል።
ግጥም እና ዜማ ሙሉ በሚባል ደረጃ ራሱ ዮሐና እንደሰራው እና አርቲስት ሳምቮድ፣ ዮርዳኖስ (ጆጆ) በአልበሙ ውስጥ ተሳትፎ ካደረጉት መካከል መሆናቸው ተገልጿል ።
በሙዚቃ ቅንብሩ እና ሚክሲንግ ሃይፐር ዜማ እና ማሩ አለማየሁ (ማርቭል) ሲሳተፉበት በማስተሪንግ ላይ ደግሞ ኪሩቤል ተስፋዬ ተሳትፈዋል።