GhionMagazine ግዮን መጽሔት


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: not specified


https://t.me/+kQKnGzeZl1IyZmZk
በኢትዮ ሐበሻ ሕትመትና ማስታወቂያ ኃ/የ/ግ/ማ ሥር ታተመው ለንባብ የሚበቁት ግዮን መጽሔት እና ኢትዮ ሐበሻ ጋዜጣ የቴሌግራም ቻናል ነዉ።
ዕለታዊ ትኩስ ዜናዎች
ፖለቲካዊ፣ ዘገባዎች
ሃይማኖታዊና ባህላዊ
ማኅበራዊና፣ ኢኮኖሚያዊ
ኪናዊ ይዘት ያላቸው ጽሑፎች በስፋት ይስተናገዱበታል፡፡https://t.me/+kQKnGzeZl1IyZmZk
በተጨማሪም፡-

Related channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
not specified
Statistics
Posts filter


ምስራቅን ፍቷት!!!

እጅግ የማከብራትና ወዳጄ ገጣሚ እና የጦቢያ ግጥም በጃዝ ፕሮግራም አዘጋጅ ምስራቅ ተረፈ በትላንትናው እለት በፖሊስ መታሰሯንና ለተጨማሪ ምርመራም ፖሊስ የጊዜ ቀጠሮ ጠይቆ መፈቀዱን ሰማሁ።

ምስራቅ እጅግ አገሯን የምትወድ፣ ሕግ አክባሪ፣ በእርጋታዋ የምትታወቅ፣ ሃሳቧን በድፍረት ስነ ጽሑፋዊ በሆነ መንገድ የምትገልጽ ምርጥ ገጣሚ፣ ምርጥ ጸሐፊ፣ ምርጥ የመድረክ ሰው፣ ምርጥ ጋዜጠኛም ነች።

የጦቢያ ግጥም በጃዝ ፕሮግራም በመንግስት እንዲቆም ከተደረገ ወራቶች ተቆጥረዋል። ሃሳብን በነጻነት የሚገለጽበትን መድረክ ከመዝጋት አልፎ እሷን ማሰር ሃሳብን በመግለጽ ነጻነት እና የኪነ-ጥበብ ነጻነት ላይ የተፈጸመ ጥቃት ነው።

የአገዛዝ ሥርዓቶች ሁሌም የፍርሃት ቆፈን ውስጥ መውደቃቸው የሚታየው ሃሳብን መፍራት ሲጀምሩና ሃሳባዊያንን ኢላማ አድርገው ማዋከብ፣ ማሰርና ማሳደድ ሲጀምሩ ነው።

ምስራቅን ፍቷት!
ጦቢያ ላይ የተደረገውም ጫናና እገዳ ይነሳ!
ፍትህ ለምስራቅና ሃሳባቸውን በነጻነት በመግለጻቸው ለሚሳደዱ ሁሉ!
#Free Misrak Terefe
#Free ጦቢያ

ከያሬድ ሀይለማርያም


በአፋር ክልል በተፈጸመ የድሮን ጥቃት ከስምንት በላይ ሰዎች ተገደሉ፤ ነዋሪዎች የጅቡቲን መንግስት ተጠያቂ አድርገዋል

በአፋር ክልል በኢትዮ-ጂቡቲ ድንበር አቅራቢያ በምትገኘው ኤሊዳዓር ወረዳ ሲያሩ ቀበሌ ሀሙስ ጥር 22 ቀን 2017 ዓ.ም በተፈፀመ የድሮን ጥቃት ቢያንስ ስምንት ሰዎች ሲገደሉ ሌሎች በርካታ ሰዎች ደግሞ መቁሰላቸውን ነዋሪዎች ለአዲስ ስታንዳርድ ገለጹ።

ነዋሪዎች እንደገለጹት ከሟቾቹ መካከል አንዲት ነፍሰ ጡር ሴት እና ሁለት ወንድማማቾች የሚገኙበት ሲሆን ቢያንስ አራት ሰዎች ላይ ከባድ ጉዳት ደርሶባቸው፤ ሁለቱ በአሁኑ ወቅት በዱብቲ ሆስፒታል ህክምና እየተደረገላቸው ነው።

ነዋሪው ጥቃቱ የተፈፀመው "በ #ጅቡቲ መንግስት" እንደሆነ በመግለጽ "ድሮኖች አካባቢውን ዒላማ ሲያደርጉ በሁለት ወራት ውስጥ ለኹለተኛ ጊዜ ነው" ብለዋል።

ሌላኛው ነዋሪ በበኩላቸው "የጅቡቲ መንግስት ተቃዋሚ ታጣቂዎች በድንበር አካባቢ እንዳሉ በመግለጽ የጂቡቲ ባለሥልጣናት፤ ታጣቂ ቡድኑን ለማጥቃት በማስመሰል የአከባቢው ነዋሪዎችን ከክልሉ በኃይል ለማስወጣት ጥቃት መፈጸሙን" እና ጥቃቱ የአካባቢውን ህዝብ ዒላማ ያደረገ መሆኑን ተናግረዋል።


“ሺ ጊዜ እንዳፈቅር ” የግጥም መድበል ተመረቀ

የገጣሚት መሠረት አዛገ ” ሺ ጊዜ እንዳፈቅር” የግጥም መድበል፣ 4 ኪሎ በሚገኘው ዋልያ መጻሕፍት፣ አንጋፋ የኪነጥበብ ሰዎች፣ ጋዜጠኞች፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶችና የሥነ ጽሑፍ ቤተሰቦች በተገኙበት በደማቅ ስነ ስርዓት ተመርቋል።

በምረቃው ሥነ ስርዓት ላይ ጸሐፌ ተውኔትና ገጣሚ አያልነህ ሙላቱ፣ ጸሐፌ ተውኔትና ገጣሚ ሥዩም ተፈራ፣ ደራሲና ጋዜጠኛ ዘነበ ወላ፣ ደራሲና መምህር ኃ/መለኮት መዋዕል፣ መምህር፤ ዶ/ር የሻው ተሰማ (የኮተቤው) እና ወጣት ገጣሚያን ሥራቸውን አቅርበዋል ።

ገጣሚ መሠረት አዛገ፣ የ”መሠረት የበጎ አድራጎት ድርጅት” መሥራችና ሥራ አስኪያጅ ስትሆን፣ ላለፉት 14 ዓመታት በህጻናትና በእናቶች ድጋፍና እገዛ ላይ በሠራቻቸው ሥራዎች በርካታ ሽልማቶችን ከሀገር ውስጥና ከተለያዩ የውጪ ሀገራት እንዲሁም ዓለም አቀፍ ተቋማት ማግኘት የቻለች እንስት ናት፡፡

ከጌጡ ተመስገን


በትግራይ በ14 ወረዳዎች 266 ትምህርት ቤቶች እድሳት ሊደረግላቸው ነዉ

የዓለም ባንክ በትግራይ በተካሄደው ጦርነት ሳቢያ የወደሙ ትምህርት ቤቶችን፣ የጤና ተቋማትን እና የውሃ አቅርቦት ተቋማት የእድሳት ግንባታ ለማድረግ የሚያስችል 3 ነጥብ 52 ቢሊየን ብር ድጋፍ ማድረጉ ተገለጸ። ከዓለም ባንክ በተገኘው ድጋፍ በ14 ወረዳዎች 266 ትምህርት ቤቶች እድሳት በተጨማሪ 84 የጤና ተቋማት እና 844 የውሃ አቅርቦት የሚሰጡ ጉድጓዶች ላይ የእድሳት ግንባታ እንደሚካሄድ ተጠቁሟል።

ይህ የተገለጸው በውቅሮ ከተማ በዓለም ባንክ ድጋፍ የእድሳት ሥራ በሚደረግላቸው ፕሮጀክቶች ዙሪያ በተዘጋጀ የምክክር መድረክ ላይ ሲኾን በመድረኩ ላይ የክልል እንዲሁም የወረዳዎች አመራሮች እና ተወካዮች እየተሳተፉ ይገኛሉ። የትግራይ ተሐድሶና መልሶ ማቋቋም ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቴድሮስ ገ/እግዚአብሔር እንደተናገሩት በትግራይ ጦርነት ያስከተለው ውድመትና ጉዳት ከፍተኛ በመኾኑ በሁሉም የትግራይ አካባቢዎች የመልሶ ግንባታና የመልሶ ማቋቋም ሥራ እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል። የእድሳት ግንባታ የሚካሄድባቸው ወረዳዎችም ዋጅራት፣ ሰሓርቲ፣ ሓሓይለ፣ ዓዴት፣ ጉለመከዳ፣ ብዘት፣ እገላ፣ ፅምብላ፣ እምባስነይቲ፣ ዛና፣ ማእከል ኣድያቦ፣ ራያ ዓዘቦ፣ ነቅሰገና ኣላጀ መኾናቸው ተጠቁሟል።


Misrak Terefe ን አገኘኋት።
በቀድሞ አጠራሩ 3ኛ፤ አሁን አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የሚባለው ውስጥ፦ እስረኛ ሆና አገኘኋት።


ለመጨረሻ ጊዜ የተገናኘነው የመንበረ ፀባኦት ቅድስት ስላሴ ካቴድራል ምርቃት እለት ነበር። ያኔ፤ እሷ ያሳተመችውን "ምጥቀት በቅኔ አክናፍ" መፅሐፍ በስጦታ አበረከተችልኝ። እና ተጨዋውተን፣ ተሳስቀን፣ ተፎጋግረን ተለያየን።

ዛሬ መታሰሯን አላመንኩም። ከጠዋቱ 3፡ 30 ነው አዲስአበባ ፖሊስ የተገኘሁት።

አላመንኩም ነበር ታሰረች መባሏን። ማታ/ለሊት ያውቋታል ወደምላቸው ሰዎች ስልክ መታሁ። መታሰሯን ማረጋገጥ አልቻልኩም።

እዚያ 3ኛ ግቢ ውስጥ ሳገኛት ነው እርግጠኛ የሆንኩት።

ሳስጠራት እየሳቀች መጣች።
"ቦታ ተቀያየርን አይደል?!" አለችኝ።
"እቅጩን በሃያ ዓመት" አልኳት።

የዛሬ ሀያ ዓመት እኔ እስረኛ ነበርኩ፤ እሷ ደግሞ ጠያቂዬ። አሁን የተገላቢጦሽ እሷ እስረኛ ነበር።

"የእናንተ ጊዜ መጨባበጥ ይቻል ነበር" አለችኝ እየሳቀች።

በመሃላችን ከሁለት ሜትር ርቀት ቢኖርም፣ በ "ነፃነት" አወራን፤ ምክንያቱም እኔ እና እሷ ብቻ ነበርን ተጠያያቂዎች።

"ፖሊሶች የጠየቁኝ አርትስ ቲቪ ላይ ቀርበው በነበሩ፣ ነገር ግን ሰሞኑን በቲክቶክ ላይ ተቆራርጠው በብዛት ሲዘዋወሩ በነበሩ ቪዲዮዎች ነው" አለች።
ገረመኝ።

"ለማንኛውም ፖሊስ የማጣራው ነገር አለ፤ የጊዜ ቀጠሮ 14 ቀን ይሰጠኝ ብሎ ነበር። ፍርድ ቤት ጥያቄውን ውድቅ አድርጎ 7 ቀን ብቻ የሰጠው"
"ወከባ ምናምን አለ?"
"የለም፤ በጥሩ ሁኔታ ነው የያዙኝ፤ አድናቂዎቼ ሳይሆኑ አይቀሩም" አለችኝ እየሳቀች።

እንዲህ እንዲህ እያልን ለብዙ ደቂቃ አወራን።
ወሬ ሲያልቅብኝ "በቃ ቻው፤ ሰባት ቀን ምን አላት?፤ የዛሬ ሳምንት ስትወጪ ቀጨኔ አበቅየለሽ ቤት እጋብዝሻለሁ" አልኳት።
በዚሁ ተሰነባበትን።

በአጭሩ፤ ምስራቅ ተረፈ ብትታሰርም ከነ ሙሉ ፈገግታዋ ናት።

ከወሰንሰገድ ገ/ኪዳን




የአሜሪካ ተራድኦ ድርጅት በመንግስት ስር ሆኖ እንደገና ሊደራጅ ነው ተባለ

የዓለማችን ልዕለ ሀያል ሀገር የሆነችው አሜሪካ በመላው ዓለም የረድኤት ስራዎችን የሚያግዝ የአሜሪካ ተራድኦ ድርጅት ወይም ዩኤስኤይድ የተሰኘውን ዓለም አቀፍ ተቋም ካቋቋመች ከ60 ዓመት በላይ ሆኗታል፡፡

ይህ ድርጅት ኢትዮጵያን ጨምሮ በመላው ዓለም የሰብዓዊ ድጋፍ ለሚፈልጉ ዜጎች መሰረታዊ ድጋፎችን በማድረግም ይታወቃል፡፡

ከሁለት ሳምንት በፊት ወደ ስልጣን የመጡት ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ይህ የረድኤት ድርጅት የመንገስትን ወጪ ከሚያንሩ ተቋማት መካከል አንዱ ነው በሚል ከአስቸኳይ የሰብዓዊ እርዳታዎች ውጪ ሌሎች ወጪዎችን ለሶስት ወራት እንዳያወጣ አግደዋል፡፡

በአሜሪካ ትቅደም ፖሊሲያቸው የሚታወቁት ፕሬዝዳንት ዶናልድ ዩኤስኤይድ የግብር ከፋይ አሜሪካዊያንን ገንዘብ እያባከነ ነው የሚል አቋም አላቸው፡፡

በዩኤስኤይድ ላይ የተጣለው እገዳ ኢትዮጵያን ጨምሮ በበርካታ ሀገራት የተሰማሩ ድርጅቶችን ህልውና ከመፈታተኑ ባለፈ አገልግሎት ሲያገኙ የነበሩ ዜጎችንም እንደጎዳ ተገልጿል፡፡

ሮይተርስ እንደዘገበው ከሆነ የዶናልድ ትራምፕ አስተዳድር ዩኤስኤይድን አሁን ካለበት ነጻ ዓለም አቀፍ ተቋምነት ይልቅ በአሜሪካ መንግስት ስር ሆኖ እንዲቀጥል የሚያስችል ውሳኔ ለማስተላለፍ አቅደዋል፡፡

ድርጅቱ በአሜሪካ መንግስት ስር ሆኖ ከተደራጀ አሁን ያለበትን አቅም ለማስቀጠል የሚቸገር ሲሆን ከዚህ በፊት በተቋሙ ስር ሆነው አገልግሎት ሲያገኙ የነበሩ ዜጎችንም ለከፋ ጉዳት ሊዳርግ ይችላል ተብሏል፡፡

ዩኤስኤይድ በመላው ዓለም ለሚያካሂዳቸው የሰብዓዊ ድጋፍ አገልግሎት ለመስጠት በዓመት ከ70 ቢሊዮን ዶላር በላይ ወጪ በማድረግ ላይ ነበር፡፡

የዶናልድ ትራምፕ አዲስ የዩኤስ እቅድ ተፈጻሚ የሚሆነው በሀገሪቱ ህግ አውጪ ምክር ቤት ቀርቦ በአብላጫ ድምጽ ከጸደቀ ሲሆን ጉዳዩ ዋነኛ የመከራከሪያ አጀንዳ እንደሚሆንም ይጠብቃል፡፡




በራስ አል ካይማህ ግማሽ ማራቶን እጅጋየሁ ታዬ አሸነፈች

18ኛው የራስ አል ካይማህ ግማሽ ማራቶን ዛሬ ማለዳ እንደሚካሄድና እጅጋየሁ ታዬ ለማሸነፍ ግምት እንዳገኘች መዘገባችን ይታወሳል፡፡ በዚሁ መሰረት ዛሬ ማለዳ ውድድሩ ተካሂዷል፡፡

የትራክ ሯጯ አትሌት እጅጋየሁ ታዬ እንደተሰጣት ግምት አሸንፋለች፡፡

የዓለም ሻምፒዮና የነሐስ ሜዳሊያ አሸናፊዋ እጅጋየሁ ርቀቱን አንድ ሰዓት ከ05 ደቂቃ 52 ሰከንድ አጠናቃ የወርቅ ሜዳሊያውን ወስዳለች፡፡

ኬንያውያኑ ጁዲ ኬምቦይ እና ጄስካ ቼላንጋት ሁለተኛና ሶስተኛ ደረጃን አግኝተዋል፡፡ ኢትዮጵያውያኑ ፍታዊ ዘራይ፣ ጌጤ አለማየሁ እና አዳኔ አንማው ከአራተኛ እስከ ስድስተኛ ያለውን ደረጃ ይዘው ውድድራቸውን አጠናቀዋል፡፡

የቦታው ፈጣን ሰዓት ባለቤቷ ግርማዊት ገብረእግዚያብሄር ውድድሩን ማቋረጧ ታውቋል፡፡

የወንዶቹን ውድድሩን ገመቹ ዲዳ በሁለተኛነት አጠናቋል፡፡ ገመቹ ርቀቱን ለመጨረስ 59 ደቂቃ 25 ሰከንድ ወስዶበታል፡፡

ኬንያዊው አሌክስ ማታታ የውድድሩ ሻምፒዮን ሆኗል፡፡ ለማሸነፍ ግምት አግኝቶ የነበረው ኢሳያ ላሶይ ሶስተኛ ደረጃን ሲያገኝ፣ ጭምዴሳ ደበሌ፣ ገርባ ዲባባና ንብረት መላክ ከአራተኛ እና ስድስተኛ ያለውን ደረጃ ይዘው የራስ አል ካይማህ ግማሽ ማራቶንን ማጠናቀቃቸውን የአፍሪካ አትሌቲክስ ህብረት መረጃ ይጠቁማል፡፡


በትግራይ ክልል በሕገ-ወጥ መንገድ ሊሸጥ የነበረ ከ35 ሺሕ 900 ሊትር በላይ ነዳጅ መያዙ ተገለጸ

በትግራይ ክልል በተያዘው የ2017 ግማሽ ዓመት በሕገ-ወጥ መንገድ ሊሸጥ የነበረ ከ35 ሺሕ 900 ሊትር በላይ ነዳጅ በቁጥጥር ሥር መዋሉን የክልሉ ንግድ ቢሮ አስታውቋል፡፡

በክልሉ በተያዘው ግማሽ ዓመት ሕገ-ወጥ የነዳጅ ግብይትን ለማስቀረት ሲሰራ የነበረ ሲሆን፤ በዚህም በተደረገው ክትትልና ቁጥጥር መሰረት ነዳጁ ሊያዝ መቻሉን፤ በቢሮው የፕላን ልማትና እቅድ ዳይሬክተር አቶ ሐጎስ ግርማይ ተናግረዋል።

ዳይሬክተሩ አክለውም እንደ አጠቃላይ በክልሉ እየገባ ያለው ነዳጅ አነስተኛ መሆኑን የገለጹ ሲሆን፤ በ6 ወራት ውስጥ ከታቀደው 67 በመቶው ብቻ ወደ ክልሉ የገባ መሆኑን አንስተዋል፡፡

ይህም ካለው ፍላጎት ጋር ሲነጻጸር በጣም አነስተኛ መሆኑን ተናግረዋል።

በተጨማሪም ቤንዚል ከጥር 14 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ክልሉ እየደረሰ አለመሆኑን አንስተዋል፡፡

"ይህንን ችግር መፍትሄ ለመስጠት ከሚመለከተው አካል ጋር በመሆን እየተሰራ ቢሆንም፤ አሁንም በቂ የሆነ አቅርቦት የለም" ብለዋል፡፡

ባለው ነዳጅ ማህበረሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን፤ ከሚመለከተው አካል ጋር በመሆንም ነዳጅ በሕገ-ወጥ መንገድ እንዳይዘዋወር ወይንም እንዳይሸጥ ቁጥጥር እየተደረገ እንደሚገኝም ገልጸዋል፡፡

እንደ አጠቃላይ ያሉ ግብአቶችን በመጠቀም ሕገ-ወጥ ግብይትን ለመቀነስ በቀጣይ የተለያዩ ሥራዎች እንደሚሰሩም አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡ (አሐዱ ሬዲዮ)


ተመድ በሞት አፋፍ ላይ ያሉ 2 ሺህ 500 ህፃናት ለአስቸኳይ ሕክምና ከጋዛ እንዲወጡ ጠየቀ

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ከአሜሪካ ህክምና ባለሙያዎች ጋር ተገናኝተው ህፃናቱ ለሞት አደጋ መጋለጣቸውን ካረጋገጡ በኋላ፣ 2 ሺህ 500 ህፃናት ሕክምና እንዲያገኙ በአስቸኳይ ከጋዛ እንዲወጡ ጠይቀዋል።

ለተመድ ማረጋገጫ የሰጡት አራቱ ዶክተሮች በጋዛ ከ2 ሚሊየን በላይ ሰዎችን ባፈናቀለው እና የጤና ጥበቃ ሥርዓትን ባወደመው ለ15 ወራት በዘለቀው ጦርነት ወቅት በፈቃደኝነት የህክምና አገልግሎት ሲሰጡ የቆዩ ናቸው።

በፈረንጆቹ ጥር 19 ቀን 2025 የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ ከመደረሱ ከቀናት በፊት፣ ከ12 ሺህ የሚበልጡ ታካሚዎች ለሕክምና ሊመውጣት እየተጠባበቁ እንደሆነና በስምምነቱ ሊወጡ እንደሚችሉ ተስፋ አድርጎ እንደነበር የዓለም ጤና ድርጅት አመላክቷል።

ይሁንና ከካሊፎርኒያ የመጡት የድንገተኛ ቀዶ ጥገና ሐኪም ፌሮዜ ሲድዋ እንደተናገሩት፣ አስቸኳይ ሕክምና ከሚያስፈልጋቸው ታካሚዎች መካከል 2 ሺህ 500 ሕፃናት ይገኙበታል።

ከአንቶኒዮ ጉተሬዝ ጋር ስብሰባ ካደረጉ በኋላ ለጋዜጠኞች ማብራሪያ የሰጡት ሲድዋ፣ እነኚህ 2 ሺህ 500 ህፃናት በሚቀጥሉት ጥቂት ሳምንታት ውስጥ ሊሞቱ እንደሚችሉ አስረድተዋል፡፡

አንዳንዶቹም አሁን ህይወታቸውን እያጡ እንደሆነ፣ አንዳንዶቹም ነገ ሊሞቱ እንደሚችሉ እና አንዳንዶቹ ደግሞ በቀጣዩ ቀን ህይወታቸው ሊያልፍ እንደሚችል ማመላከታቸውንም ሬውተርስ ዘግቧል።


ቻይና በበሽታ ስጋት ከታንዛኒያ፣ ሶማሊያና ሌሎች በርካታ ሀገራት የሚገቡ የእንስሳት ምርቶችን አገደች

ቻይና በተለይም በጎች ወደ አገር ውስጥ እንዳይገቡ ከልክላለች። ከዚህ በተጨማሪ ቻይና ፍየል፣ዶሮና ሌሎች የእንስሳት ተዋፅኦም ከአፍሪካ፣እስያ እና አውሮፓ ወደ ሀገሯ እንዳይገቡ ከልክላለች።

ክልከላው ሊጣል የቻለዉ ከበግና ከፍየሎች የሚነሳ የእግርና የአፍ በሽታ መታየት መጀመሩን ተከትሎ ነው። እግዱ በህይወት ያሉ እንስሳት ብሎም የተቀነባበረ የስጋ ውጤት የሚያጠቃልል ሲሆን ቻይና እዚህ ውሳኔ ላይ ልትደርስ የቻለችውም የዓለም የእንስሳት ጤና ድርጅት በተለያዩ ሀገራት የእንስሳት በሽታ በወረርሺኝ መልኩ እየታየ ነው ማለቱን ተከትሎ ነው።

ከዓለማችን ግዙፍ የእንስሳት ስጋ ተቀባይ በሆነችዉ ቻይና የተወሰነው ውሳኔ እንደ ጋና፣ ሶማሊያ፣ ኳታር፣ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ፣ ናይጄርያ፣ ታንዛንያ፣ ቡልጋርያና ኤርትራ የመሳሰሉ ሀገራት ላይ ተፅእኖ ያሳድራል ተብሏል።

ከነዚህ ሀገራት በተጨማሪ ቻይና ከፍልስጤም፣ አፍጋኒስታን፣ ኔፓልና ባንግላዲሽ የሚመጡ የእንስሳት ተዋፅኦ ላይ እገዳ የጣለች ሲሆን ሙሉ በሙሉ ባይሆንም ከጀርመን ወደ ቻይና የሚላኩ የተወሰኑ የስጋ ምርቶች ላይም እገዳ ጥላለች።


አብን በቀጣዩ ምርጫ ላይሳተፍ ይችላል ተባለ

የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) 300 የሚደርሱ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቶቹ በሥራ ላይ ባለመኾናቸው በቀጣዩ ጠቅላላ ምርጫ የመሳተፍ አቅም አይኖረውም ሲሉ አባላቶቹ መናገራቸው ተሰማ።

ከፓርቲው አባላት የተወሰኑት መንግሥትን ለመግልበጥ ሙከራ አያደረጋችኋል ተብለው ለ6 ወራት ከታሠሩ በኋላ፣ ባለፈው ሳምንት እንደተፈቱ ተነግሯል። አብን መጋቢት 11 ቀን፣ 2014 ዓ፣ም በባሕርዳር ከተማ ያካሄደውን ጠቅላላ ጉባኤ በምርጫ ቦርድ ተቀባይነት ባለማግኘቱ ጉባኤው በድጋሚ እንዲካሄድ ቦርዱ ቢያዝም፣ እስካኹን ድረስ ፓርቲው ጉባኤውን ማካሄድ አልቻለም።

የፓርቲው አመራሮች ከምርጫ ቦርድ ጋር ያላቸው ንግግር በግልጽ የማይታወቅ መኾኑ፣ የፓርቲውን ሕልውና አሳሳቢ እንዳደረገው አባላቱ ገልጸዋል። የአብን አባላት በፓርቲው ወቅታዊ ቁመና ዙሪያ ላነሱት ቅሬታ፣ የፓርቲው አመራሮች ምላሽ እንዲሠጡ ቢጠየቅም አለመሳካቱን ዋዜማ ዘግባለች።


ገጣሚ እና የጦቢያ ግጥም በጃዝ ፕሮግራም አዘጋጅ ምስራቅ ተረፈ የ7 ቀን ቀጠሮ ተጠየቀባት

ገጣሚ እና የጦቢያ ግጥም በጃዝ ፕሮግራም አዘጋጅ ምስራቅ ተረፈ ትናንት ጥር 22 ቀን 2017 ዓ.ም በፖሊስ ለጥያቄ ትፈለጊያለሽ ተብላ ወደ አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን እንደተወሰደች ታውቋል።

የመሠረት ሚድያ ምንጮች እንደጠቆሙት ምስራቅ ዛሬ ጥር 23 ቀን 2017 ዓ.ም ከሰዓት በኋላ ፖሊስ ምርመራ ለማጣራት ጊዜ እንዲሰጠው ፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት አቅርቧት ፍርድ ቤቱ ፖሊስ ምርመራውን አጣርቶ እንዲያቀርብ 7 ቀን በመስጠት  ለጥር 30 ቀን 2017 ዓ.ም ቀጠሮ ሰቷል፣ ምስራቅ ተረፈ ወደ አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ተመልሳለች።

ምስራቅ የኪነጥበብ ምሽቶችን በሀገር ውስጥ እንዲሁም በውጭ ሀገራት በማዘጋጀት እንዲሁም የራሷን ግጥሞች በማቅረብ በብዛት ትታወቃለች።

እንደ ዶ/ር በድሉ ዋቅጅራ እና ገጣሚ ትእግስት ማሞ ያሉ የደመቁባቸውን ዝግጅቶች በማሰናዳት የምትታወቀው ግለሰቧ ግጥም፣ መነባንብ፣ ዲስኩር እንዲሁም ጥበብ እና ጥበብ ነክ ስራዎች ይበልጥ እንዲለመዱ እንደለፋች ብዙዎች ይናገራሉ።

ገጣሚ ምስራቅ አሁን ላይ የታሰረችበት ምክንያት ምን እንደሆነ ግልፅ እንዳልሆነ ታውቋል።

@MeseretMedia


የድምፃዊ ዮሐና አልበም ተለቀቀ

የድምፃዊ ዮሐና አዲስ አልበም ዛሬ ጥር 23 2017 ዓ.ም በቀኑ 8:00 ጀምሮ ለአድማጮች ቀርቧል።

ድምፃዊ ዮሐና 'ሃሎ' የሚል መጠሪያ ያለውን እና 10 ሙዚቃዎች ያካተተውን አዲስ አልበሙን እንደለቀቀ ኤቨንት አዲስ ሚዲያ ተመልክቷል።

በዚህ አዲስ አልበም ዮሐና ከሰራቸው ሙዚቃዎች መካከል 'ታማ' በሚል ርዕስ ያቀነቀነው ሙዚቃ ከዮሐና ጋር ጥብቅ ቁርኝት ላላት መቐለ ከተማ የተፃፈ የፍቅር ደብዳቤ እንደሆነ ተነግሯል።

ግጥም እና ዜማ ሙሉ በሚባል ደረጃ ራሱ ዮሐና እንደሰራው እና አርቲስት ሳምቮድ፣ ዮርዳኖስ (ጆጆ) በአልበሙ ውስጥ ተሳትፎ ካደረጉት መካከል መሆናቸው ተገልጿል ።

በሙዚቃ ቅንብሩ እና ሚክሲንግ ሃይፐር ዜማ እና ማሩ አለማየሁ (ማርቭል) ሲሳተፉበት በማስተሪንግ ላይ ደግሞ ኪሩቤል ተስፋዬ ተሳትፈዋል።


ኢትዮጵያን ጨምሮ ከ 300 ሚሊዮን በላይ አፍሪካዊያንን የኤሌትሪክ ተጠቃሚ ያደርጋል ለተባለዉ ፕሮጀከት 54 ቢሊዮን ዶላር ተመድቧል

የአፍሪካ የኃይል ጉባዔ ሚሽን 300 በሚል መሪ ሀሳብ በመጪዎቹ አምስት ዓመታት ኢትዮጵያን ጨምሮ 300 ሚሊዮን አፍሪካውያንን የኤሌትሪክ ኃይል ተጠቃሚ የሚያደርግ ፕሮጀክት መታቀዱ ተነግሯል።

ለዚህም ፕሮጀክት ማስፈፀሚያ ከተለያዩ አለምአቀፍ ለጋሽ ተቋማት 53 ነጥብ 95 ቢሊዮን ዶላር መገኘቱን የአፍሪካ ልማት ባንክ አስታውቋል።

ለሁለት ቀናት በታንዛኒያ ዳሬሠላም በተደረገው ጉባዔ ላይ 30 የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች ተመጣጣኝ እና አስተማማኝ የኤሌክትሪክ አገልግሎት በ2030 እንዲስፋፋ ያላቸውን ቁርጠኝነት ማሳየታቸው ተገልጿል።


ፑንትላንድ ሰነድ አልባ ኢትዮጵያውያንን ያዘች

በሶማሊያ የፑንትላንድ ባለሥልጣናት በቦሳሶ ከተማ የሚገኙና የመኖሪያ ፈቃድ ወይም ሰነድ የሌላቸውን በመቶ የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንን እንዲያዙ አድርገዋል።

ወደ ሀገራቸው እንደሚመልሱም አስታውቀዋል። እርምጃው ሰነድ አልባ የውጪ ዜጎችን ከሀገሪቱ የማስወጣት ዘመቻ አካል እንደሆነም ተመልክቷል።

የተያዙት ስደተኞች በመኪና ተጭነው ከከማዋ ውጪ ተወስደዋል። ይህም ወደ ኢትዮጵያ ለመመለስ በማሰብ ሳይሆን እንዳልቀረ ተነግሯል።

እርምጃው የተወሰደው ፑንትላንድ በአይሲስ ላይ ወታደራዊ ዘመቻ በማካሄድ ላይ ባልችበት ወቅት ሲሆን፣ ባለፈው ሳምንት አንድ በአይሲስ አባልነት የተጠረጠረን ግለሰብ የፀጥታ ኅይሎች ተኩሰው መግደላቸውን ተከትሎ ነው።

የተያዙት ስደተኞች ከሽብር እንቅስቃሴ ጋራ ግንኙነት ይኖራቸው ባለሥልጣናት ማስረጃ አላቀረቡም። voa


የግጭት ዳፋ ባገረሸበት ሰላሌ የነዋሪው ሰቆቃ

በኦሮሚያ ክልል ግጭት ከከፋባቸው አከባቢዎች አንዱ የሆነው ሰላሌ በግጭቱ ምክንያት የነዋሪዎች ሕይወት ለአደጋ መጋለጡን እየተናገሩ ነዉ።ነዋሪዎቹ እንደሚሉት እገታ፣ ማስፈራሪያና ቅሚያ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባበሰ ነዉ።

አንድ የሰሜን ሸዋ ዞን የደብረጽጌ ከተማ ነዋሪ እንደሚሉት የመንግሥት ፀጥታ አስከባሪዎችና አማፂያን ሠላም እንደሚያወርዱ የአካባቢዉ ህዝብ በተደጋጋሚ በአደባባይ ሠልፍ ጭምር ጠይቋል። ተደጋጋሚዉ ጥያቄና ተማጽዕኖ መና ቀርቶ ታጣቂዎች የሚያደርሱት አስገድዶ ስወራ፣ እገታና ዘረፋዉ ቀጥሏል። የአከባቢው ነዋሪዎች እንደሚሉት ገበያ ለመሔድና እና ለቅሶ ለመድረስ እንኳን እየሠጉ ነዉ። 

ከአንድ ሳምንት በፊት ከደብረሊባኖስ አከባቢ ለገበያ በመኪና ሲጓዙ የነበሩ 50 ያክል ነጋዴዎች ሳዲኒ ብዮ በሚባል የያያ ጉሉለ ወረዳ ታፍነው እንደተወሰዱ ሌላዉ ነዋሪ አስታዉቀዋል።

የያያ ጉሌሌ ፊታል ከተማ አስተያየት ሰጪ አክለዉ እንዳሉት የፀጥታ ችግሩ ፋታ አይሰጥም።መኪና ሙሉ ሰዎች መወሰዳቸዉ የችግሩን ክፋት እንደሚያሳይ ነዋሪዉ ገልፀዋል።

ይህ ቦታ ከአንድ ወር ግድም በፊት አምስት የዞን ባለስልጣናትን ጨምሮ የመንግስት ሰራተኞች የተገደሉበት አካባቢ ነው፡፡ነዋሪዉ እንደሚሉት ባለፈው ሳምንት ማክሰኞ የተወሰዱት ወደ 50 የሚሆኑ ገበያተኞች እስካሁን አልተመለሱም፤ «የመኪናዉ ሾፈርም አብሮ እንደተወሰደ ነው” ብለዋል፡፡

በቅርቡ ከዞን የመጣው የመንግስት ሠራዊትም ዘመቻ መክፈቱን ባስታወቀ በጥቂት ጊዜ ዉስጥ ከአካባቢዉ በመልቀቁ ምንም ለውጥ አልታየም፡፡ «ከዚህ ከተማ ውጪ ታጣቂዎች የማይገኙበት ሥፍራ የለም» ይላሉ ነዋሪዎቹ።

“ተቸግረናል፡፡ ከተማ ውስጥ እንኳ ቢሆን ተኝቶ የሚያድር ሰው አታገኝም፡፡ ሰው እየተደበቀ ከቦታ ቦታ እየተንቀሳቀሰ ነው ቀን የሚገፋው፡» ይላሉ። ነዋሪዉ እንደሚሉት ሁለቱ ተፋላሚዎች ብዙ ጊዜ ፊትለፊት ሲዋጉ አታይም፡፡

«የመንግስት ጦር ሲመጣ ጫካ ያለው በደፈጣ ነው የሚጠብቀው፡፡ ሁለቱ ተፋላሚዎች ተነጋግረው መግባባት ስላልቻሉ በመሃል የመጨረሻ ስቃይ እያየን ነዉ» አከሉ ነዋሪዉ።

የመንግስት የጸጥታ ሃይልም፣ አማጺዎችም የነዋሪዉን ሥልክ ሥለሚወስዱ መረጃ  መለዋወጥ እንኳን አዳጋች ሆኖ ህዝቡ ከዚህ በፊት ሲኖር ከነበረው ሃምሳ ኣመት ወደ ኋላ ተመልሶ እየኖረ ነው ብለዋል፡፡የአዲስ አበባዉ ወኪላችን ስዩም ጌቱ ሥለ ህዝቡ ሮሮ  የዞኑን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ከፋለ አደሬን በስልክ ለማነጋገር ቢደዉልም መልስ ግን አላገኘም።
Dw Amharic




85ኛው የአገው ፈረሰኞች ማኅበር በ እንጅባራ ከተማ በድምቀት እየተከበረ ነው

ከ62 ሺህ በላይ አባላት ያሉትና በ2014 ዓ.ም በኢትዮጵያ የቅርስ ጥበቃ ባለሥልጣን ሀገራዊ ቅርስ ኾኖ የተመዘገበው የአገው ፈረሰኞች ማኅበር 85ኛውን ክብረ በዓል "አርበኝነታችን ለአሁናዊ ሰላማችን" በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ ይገኛል።

በበዓሉ ላይ ፌዴራል እና የክልል ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎች እና ሌሎች ታዳሚያን የተገኙ ሲሆን፤ የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ሚኒስትር ዴዔታ ተስፋሁን ጎበዛይ ለሀገር መስዋዕትነት የከፈሉ ፈረሶችን እና ፈረሰኞችን ለመዘከር የአገው ፈረሰኞች በዓል በየዓመቱ እንደሚዘከር ገልጸዋል።

20 last posts shown.