GhionMagazine ግዮን መጽሔት


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: not specified


https://t.me/+kQKnGzeZl1IyZmZk
በኢትዮ ሐበሻ ሕትመትና ማስታወቂያ ኃ/የ/ግ/ማ ሥር ታተመው ለንባብ የሚበቁት ግዮን መጽሔት እና ኢትዮ ሐበሻ ጋዜጣ የቴሌግራም ቻናል ነዉ።
ዕለታዊ ትኩስ ዜናዎች
ፖለቲካዊ፣ ዘገባዎች
ሃይማኖታዊና ባህላዊ
ማኅበራዊና፣ ኢኮኖሚያዊ
ኪናዊ ይዘት ያላቸው ጽሑፎች በስፋት ይስተናገዱበታል፡፡https://t.me/+kQKnGzeZl1IyZmZk
በተጨማሪም፡-

Related channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
not specified
Statistics
Posts filter


“ በአጠቃላይ አቃቢ ህግ በእኔ ላይ መስርቶ ባቀረበው ክስ ላይ የተገለጸውን ወንጀል አልፈጸምኩም” - አቶ ክርስቲያን ታደለ

እነአቶ ክርስቲያን ታደለ ዛሬ ችሎት ቀርበው የእምነት ክህደት ቃል መስጠታቸውን ጉዳዩን ከሚከታተሉ ሰዎችና ቃላቸውን ካቀረበበት ሰነድ መረዳት ትችሏል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የተመለከተው አቶ ክርስቲያን የእምነት ክህደት ቃል የሰጡበት ሰነድ፣ “በአጠቃላይ አቃቢ ህግ በእኔ ላይ መስርቶ ባቀረበው ክስ ላይ የተገለጸውን ወንጀል አልፈጸምኩም። ጥፋተኛም አይደለሁም” ይላል።

አቶ ክርስቲያን በሰጡት የእምነት ክህደት ቃል ምን አሉ?

“ለ550 ቀናትም በግፍና ጭካኔ እገታ ውስጥ የምገኘው ለአንዲት ደቂቃ እንኳን በጥፋተኝነት የሚያስቀጣ አንዳችም የወንጀል ድርጊት የሚያቋቁም የህግ መተላለፍ ስለፈጸምኩ አይደለም። የአማራ ሕዝብ የሚያነሳቸውን የህልውና ጥያቄዎች በይፋ በማቅረቤ፣ በሕዝቤ የሚደርሰውን ግፍ፣ በደል በማስረጃ በመሞገቴ፣ የገዢውን ፓርቲ አፈናና የመንግስት አሰራሮችንና አመራሮችን ብልሹነትና ዘረፋ በመታገሌ ነው ” ብለዋል።

“ ተደጋጋሚ የአመራር ብልሹነት ባሳዩ አካላትም የወንጀልና የፍትሃብሔር ተጠያቂነት እንዲረጋገጥ ክስ እንዲመሰረት ፍትህ ሚኒስቴር አዝዥለው ” የሚሉና ሌሎች ድርጊቶችን በአደባባይ እንደታገሉ ገልጸዋል።

“ ጠቅላይ ሚኒስትሩን ጨምሮ ሌሎች የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች በአሰራራቸው የፋይናንስ ገልጸኝነትና ህጋዊነት እንዲከተሉና እንዲረጋገጡ እንዲሁም ኦዲት ለመደረግ ፈቃደኝነታቸውን እንዲያረጋግጡ ጠይቄከለሁ ” ነው ያሉት።

እነዚህን ጥያቄዎች እንዳልጠይቅ አንዳንድ አመራሮች ለማግባባት እንደሞከሩ ገልጸው፣ “ አንዳንዶቹም ሊገድሉኝ፣ ሊያስሩኝና አንዳች ነገር ሊያደርሱብኝ እንደሚችሉ ጭምር ነግረውኛል፤ መልዕክትም አድርሰውኛል ” ብለዋል።

“ አንዳች ወንጀል አልፈጸምኩም ” ያሉት ክርስቲያን፣ “ ይህን በተመለከተ ከክሱ ይዘት ብቻ ሳይሆን በራሴ መንገድ ይህን ክስ ተዘጋጅቶ እንዲቀርብብኝ ካደረገው አካል ዘንድም አረጋግጫለሁ ” ሲሉ አስረድተዋል።

“ እኔ አማራ የሆንኩት አማራ ሆኘ ስለተወለድኩ ነው። የከማራ ብሔርተኝነት አቀንቃኝ የሆንኩትም ፈቅጄ፣ መርጨና ወድጄ ነው። በየትኛውም ቦታና ሁኔታ ለአማራነቴ ጥብቅና መቆምም ተፈጥሯዊ ግዴታዬ ነው ” ብለዋል።

“ አማራዊ እሴቶታችን ለኛ ቅዱስ ነው ” ብለው፣ “ ይሁንና አቃቢ ህግ ባቀረበው የፓለቲካ ውንጀላ ሰነድ ላይ፣ ‘አማራ ርስቱን ተቀምቷል፤ አገሪቱ በአማራ እሴት መመራት አለባት’ የሚል የርዕዮተዓለማዊ አቋም መያዛችን ክስ ሆኖ ቀርቧል” ብለዋል።

“ ይህ የአቃቢ ህግ ክስ ግን መንግስት ከአማራና ከአማራነት የጸዳች ኢትዮጵያ ነው ወይ የሚፈልገው ? የሚል ሙግት ያስነሳል። ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት ከአማራና ከአማራነት በስተቀር እንዲሆኑ የሚደነግግ ህግስ አለ ወይ? ” ሲሉ ጠይቀዋል።

በሌላ በኩል “ በአቃቢ ህግ ክስ ላይ ‘ቋሪትና ደጋ ዳሞት ላሉ የሽብር ቡድን አስተባባዎች በስልክ ሐምሌ 25/2015 ዓ/ም በመደወል መከላከያን ማጥቃት ህገ መንግስታዊ መብት መሆኑን በማሳወቅ እንዲመቱ ትዕዛዝ ሰጥቷል’ ” ማለቱን ጠቅሰል።

“ አቃቢ ህግ ለዚህ ክስ አስረጅ የሆነ አንዳችም ማስረጃ አላቀረበም ” ብለዋል።

(ሙሉ የእምነት ቃላቸውን የሰጡበት ሰነድ ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia




" ፍትህ የለም እንጂ ፍትህ ካለ እኔ ነጻ ሰው ነኝ። ፍርድ ቤት በነጻ ለቆ ለደረሰብኝ በደል ሁሉ ካሳ ሊያሰጠኝ በቻለ ነበር " - አቶ ዮሐንስ ቧያለው

እነ አቶ ዮሐንስ ቧያለው እና አቶ ክርስቲያን ታደለ ዛሬ ለፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ህገ መንግስትና የሽብር ወንጀል ችሎት በረበባቸው ክስ የእምነት ክህደት ቃል መስጠታቸውን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከደረሰው የሰነድ ማስረጃ ለማወቅ ችሏል።

አቶ ዮሐንስ ቧያለው በሰጡት የእምነት ክህደት ቃል፣ " የቀረበብኝን ውንጀላና አሉባልታ አልቀበልም። ወንጀልም አልፈጸምኩም " ማለታቸውን ሰነዱ ያወሳል። 

አክለው፣ " ፍትህ የለም እንጂ ፍትህ ካለ እኔ ነጻ ሰው ነኝ። ፍርድ ቤት በነጻ ለቆ ለደረሰብኝ በደል ሁሉ ካሳ ሊያሰጠኝ በቻለ ነበር። ግን እንዴት ሆኖ/ ራሱ ነጻ ያልሆነ ማንን ሊያደርግ ይችላል " ነው ያሉት።

የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ በ18/07/2016 ዓ/ም በስማቸው በሚጠራው መዝገብ ላይ ያቀረበውን ክስ " ሙሉ በሙሉ ተቀባይነት የለውም " ሲሉ ውድቅ አድርገውታል።

የተቃውሟቸውን ምክንያት የገለጹበት ሰነድ፣ " ሁሉም የክስ ጭብጦች በፈጠራ ተሞሉ ናቸው " ይላል።

የክስ ጭብጡ፣ " ‘የሽብር ቡድን አመራር በመሆን፣ አባል በመሆን፣ ራሱን በመሰየም፣ በማደረጃት፣ የሰራተኛ ሰነድ በማዘጋጀትና ጽንፈኛ ፋኖን በመምራት የሽብር ወንጀል ፈፅሟል’ ይላል " ሲሉ አስረድተዋል በሰነዳቸው። 

ዮሐንስ በሰጡት የእምነት ክህደት ቃል፣ " የተጠቀሰው ሀሳብ በአንድ በኩል መረጃ አልባና ከእውነት የራቀ ሲሆን፣ በሌላ መልኩ ደግሞ የአንድን የህዝብ ባህላዊ ተቋም ለመክሰስ የሞከረ ሆኖ አግኝቼዋለሁ " ሲሉ ወንጅለዋል።

" መረጃ አልባነቱን " ጭምር በገለጹበት ሰነድ አቶ ዮሐንስ ምን አሉ ?

“ በኢፌድሪ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተሰየመ አሸባሪ ቡድን ማን እንደሆነ፣ በዚህ ቡድን ላይ የእኔ ኃላፊነትና የፈጸምኩት ወንጀል ምን እንደሆነ ከመግለጽ ይልቅ ጠቅላይ አቃቤ ህግ ራሱ በጭንቅላቱ የፈጠረው ‘አሸባሪና ጽንፈኛ ቡድን አመራርና አባል ነው’ የሚል የፈጠራ ድርሰት መቅረቡ ነው።

በአንጻሩ አንድን የህዝብ ባህላዊ ተቋም ፍትህ ሚኒስቴር (ጠቅላይ አቃቢ ህግ) በአዋጅ ከተሰጠው ስልጣን በመተላለፍና በደመኝነት መንፈስ ‘አሸባሪ’ ብሎ መሰየሙ ነው። 

ፋኖ የአማራ ህዝብ ተቋም ሆኖ እያለ የፋኖ አመራርና አባል የሆኑ ሰዎች አሸባሪ ናቸው ብሎ መክሰስ ህዝቡን እንደ ህዝብ ከመክሰሱም በላይ ለአማራ ህዝብ ተቋሙ ያሳየውን ንቀት የሚያረጋግጥ ሆኖ አግኝቼዋለሁ።

የአማራ ጠላት የሆነው ዘረኛው ስርዓትም ይሁን በመሳሪያነት እያገለገለ ያለው ጠቅላይ አቅቢ ህግ ሊያውቁት የሚገባ ጉዳይ ቢኖር ሁሉም አማራ ፋኖ መሆኑን ነው። የእኔ ‘ፋኖ’ መሆንም በቀጥታ ከአማራነቴ ጋር የተያያዘ ነው።

ሲወርድ ሲዋረድ የመጣው መላው የአማራ ህዝብ እስካሁን ድረስ ምናአልባትም በጉዲፈቻና በሞጋሳ ከተሸጡት ጥቂት የአብይ አህመድ ቡድን የሆኑ የካቢኔ አባላት ውጪ ሁሉም አማራ ፋኖ እንደሆነ ሁሉ እኔም በፋኖነቴ አላፍርም። እኮራለሁ እንጂ !

ቄሮነትና አባገዳነት ወንጀል እንዳልሆነው ሁሉ ፋኖነትን መንካት በአንድ ህዝብ ላይ ያነጣጠረ ጥቃት ከመሆኑም በላይ ምንጊዜም ቢሆን በማንነቴ ላይ የሚመጣን ጥቃት እንደ ባንዳዎችና በጉዲፈቻ እንደተሸጡ የስራዓቱ (የብልጽግና ቡድን) አባላት ዝም ብዩ ልቀበለው እንደማልችል በድጋሚ ላረጋግጥ እወዳለሁ። 

ፋኖነት ወንጀል ሳይሆይን በክብር የሚሰውለት አማራዊነት ነው
" ብለዋል።

አቶ ዮሐንስ ቧያለው ሙሉ የእምነት ክህደት ቃል ገለጻ የያዘው ሰነድ ከላይ የተያያዘ ሲሆን የአቶ ክርስቲያን ታደለ የእምነት ክህደት ቃል ደግሞ በቀጣይ ይቀርባል።  @tikvahethiopia




Video is unavailable for watching
Show in Telegram
"የትግራይ ህዝብ የመገንጠል መብቱን ለመጠቀም ወስኗል" አቶ ስዬ አብርሃ
    
ስዬ አብርሃ በርካታ ጉዳዮችን አንስቷል።
እስኪ  ለማንኛውም

ጥምረት ጥምረት እየተባለ ነው።ማን ከማን ጋር ነው የሚጣመረው።ባለፉት አመታት ብዙ ነገር ተበላሽቷል ።

በትግራይና በአማራ የታጠቁ ሃይሎች መካከል ስለታሰበው ጥምረት ይቅርና የአማራ ሃይሎች እንኳን ይህ ነው የሚባል ጥምረት የላቸውም።ሌላው ቀርቶ ተጣምረን በመታገል የምንታወቀው እኛ ተጋሩም እኮ ዛሬ ላይ አንድ አይደለንም።

ኦሮሞም እንደዛው ተመሳሳይ ነው።በጣም የሚገርመው ደግሞ ኢሳያስ አፈወርቂን ሸምጋይ በማድረግ የሚፈጠር ጥምረት ምን አይነት ነው ? የትግራይ ህዝብ የራስን እድል በራስ የመወሰን መብቱን ተጠቅሞ የወደፊት እጣ ፈንታውን ለመወሰን መቁረጡ

በኢሳያስ አፈወርቂ ዘንድ እንደማይወደድ እየታወቀና  የኢትዮጵያን ህገመንግስት ከጅምሩም አምርሮ እንደሚጠላው እየታወቀ ኢሳያስ ይደግፈናል ብሎ ማሰብ ምን አይነት ድንቁርና ነው ?ምን አይነት እብደት ውስጥ ነው የገባነው?


Commercial Bank of Ethiopia
Exchange Rate Applicable for Friday, 07 February 2025.


👉"ከእኛ ክፋት የተነሳ ነው መከራ እየመጣብን ነው በዚህም በሀጥያታችን ፈጣሪያችንን አስቆጥተናል" አቡነ ማቲያስ

👉"ከእኩይ ስራችን መመለስ አለብን ከቃል ባለፈ የሰው ልጅ በሰራው ነው ለሰላም በተግባር ዘብ መቆም ይገባናል"ሐጅ ኢብራሂም

👉"ሰላም ትልቁ ጸጋ ነው " ብፁዕ ካርዲናል

👉"የምንሰብከው ወንጌል የሰላም ነው"ቄስ ደረጀ

በኢትዮጵያ የሲቪል እና የሙያ ማኅበራት ም/ቤት(ኮንግረስ) አዘጋጅነት ልዩ የጸሎት እና የሰላም ጥሪ አገራዊ ጉባኤ የተደረገ ሲሆን በየአቅጣጫው የሚታየው ግጭት እንዲቆም "ሰላም ለሀገራችን፤ ሰላም ለህዝባችን!!" ይሆን ዘንድ የየሃይማኖቱ አባቶች ለኢትዮጵያ ህዝብ የሰላም ጥሪ እና መልእክት በዛሬው እለት አስተላልፈዋል።
                                                                
📌በመድረኩም ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ፓትርያርክ ሊቀጳጳሳት ዘአክሱም  ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሀይማኖት ፤ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በመወከል ባስተላለፉት መልዕክት " ከእኛ ክፋት የተነሳ ነው መከራ እየመጣብን ነው በዚህም በሀጥያታችን ፈጣሪያችንን አስቆጥተናል ያሉ ሲሆን በዚህም እግዚአብሔርን በማሳዘናችን በቀጣይ የካቲት 3 እስከ 5 ድረስ በሚቆየው ጾመ ነነዌ በንሰሀ በመመለስ ከልብ ይቅርታ በመጠየቅ እና ከክፉ ተግባር መታቀብ" እንደሚያሻ መልዕክት አስተላልፈዋል።

📌የክብር ዶክተር ሸይክ ሐጂ ኢብራም ቱፋ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት እና የዑለማዎች ምክር ቤት ሰብሳቢ፤ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት በመወከል ባስተላለፉት መልዕክት " ከእኩይ ስራችን መመለስ አለብን ከቃል ባለፈ የሰው ልጅ በሰራው ነው ለሰላም በተግባር ዘብ መቆም ይገባናል ብለዋል።

📌ብፁዕ ካርዲናል ብርሃነ እየሱስ ሊቀጳጳሳት ዘካቶሊካውያን የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን የጳጳሳት ጉባኤ ፕሬዝዳንት በበኩላቸው ባስተላለፉት መልዕክት
ሰላም ትልቁ ጸጋ ነው የክርስትና እምነት የገባው በሰላም ነው የሚል መልዕክት አስተላልፈዋል።

📌ቄስ ደረጀ ጀምበሩ የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲናት ካውንስል ጠቅላይ ጸሀፊ የምንሰብከው ወንጌል የሰላም ነው ስለዚህ ሰላምን አብዝተን ልንፈልግ እና ልንከታተል ይገባል ብለዋል።

የሀይማኖት አባቶቹ ከሰላም ጥሪ ባለፈ እንደየ እምነታቸው ለፈጣሪያችን ስለ ሰላም በጸሎታቸው ተማጽነዋል።




የአውስትራሊያ ማእከል  ገዳማትንና የአብነት ትምህርት ቤቶችን ለመደገፍ   ውይይት ተደረገ

በማኀበረ ቅዱሳን በአውስትራሊያ ማእከል ከ10 የጽዋዕ ማኀበራት ጋር ገዳማትን እና የአብነት ትምህርት ቤቶችን መደገፍ በሚቻልበት መንገድ እንዲሁም የገዳማት ነባራዊ ሁኔታን አስመልክቶ በቨርችዋል(በበይነ መረብ)  የግንዛቤ ማስጨበጫ ዉይይት መካሄዱ ተገልጿል፡፡

አቶ ፍጹም መንገሻ የአውስትራሊያ ማእከል ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ከማኀበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ጣቢያ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት የገዳማትና የአብነት ትምህርት ቤቶች ተጨባጭ ሁኔታቸውን ለማሳወቅና ድጋፍ እንዲደረግላቸው ውይይቱ በመሠረታዊነት ተከናውኗል ብለዋል።

ኃላፊው አክለዉም በጦርነትና በድርቅ ምክንያት በከፍተኛ ችግር ያሉ በተለይም በሰሜኑና በምስራቅ የሚገኙ ገዳማትን ከጽዋዕ ማኀበራት ጋር በመሆን ድጋፉ ተደራሽ እንደሚደረግላቸው ተናግረዋል፡፡

ገዳማትና የአብነት ትምህርት ቤቶች ድጋፍ እንዲያገኙ ሁሉም የቤተ ክርስቲያን ባለድርሻ አካላት የበኩላቸውን እንዲወጡ ጥሪያቸውን ያስተላለፉ ሲሆን በውይይቱ ላይ የተገኙት የማኀበራቱ ተወካዮች ለተግባሩ ቁርጠኛ መሆናቸው ተመላክቷል፡፡

ድጋፉ በሀገሪቱ በተለያዩ አካባቢዎች በጦርነትና በድርቅ ለተጎዱ ገዳማትንና አብነት ትምህርት ቤቶችን የሚያካትት መሆኑ ተጠቅሷል።


በ76 ዓመታቸው ወንድ ልጅ የወለዱት


ወ/ሮ መድህን ሓጎስ የተባሉ የመቐለ ከተማ ነዋሪ በ 76 ዓመታቸው ወንድ ልጅ ወልደዋል።  

ወ/ሮ መድህን ከዚህ በፊት ልጅ የወለዱ አለመሆናቸውን እና ይህ የመጀመሪያቸው መሆኑን ኢቢሲ ከቤተሰቦቻቸው አረጋግጧል።

የልጃቸው ክርስትና ባለፋት ቀናቶች መከናወኑም ተገልጿል፡፡  

ኢቢሲ ባለ ታሪኳን ለማነጋገር ያደረገው ጥረት ባይሳካም ወ/ሮ መድህን የወንድ ልጅ እናት ስለመሆናቸው ከቤተሰባቸው ማረጋገጥ ችሏል። 

ወ/ሮ መድህን ሓጎስ በ76 ዓመታቸው ልጅ የመውለዳቸው ጉዳይ በማሕበራዊ ሚዲያው ብዙዎች እየተነጋገሩበት ይገኛል።
በሙሉጌታ ተስፋይ (ከመቐለ)


በአዲስ አበባ አንዳንድ የመንግስት አገልግሎቶችን  በ3ተኛ ወገን ለማሰራት የሚያስችል ደንብ ፀደቀ

በሶሶተኛ ወገን ለማሰራት የታሰቡት የመንግስት ስራዎች የትኞቹ እንደሆኑ አልተገለፀም።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ 4ተኛ ዓመት 7ተኛ መደበኛ ስብሰባው በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ  ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል።

ወሳኔ ከተላለፈባቸው መካከል አንዳንድ የመንግስት አገልግሎቶችን በውል ለ3ተኛ ወገን ለማስራት የወጣውን ረቂቅ  ደንብ  ካቢኔዉ ያፅደቀበት ይገኝበታል።

በከተማዉ  አስተዳደር በጀት ተመድቦላቸዉ የተገነቡ እና በመጠናቀቅ ያሉትን  አዳዲስ ሆስፒታሎችን ዘመኑን በዋጀ ህክምና መሳሪያ ለማሟላት እና አለም አቀፍ ደረጃን የሚያሟላ  አገልግሎት መስጠት ያስችላቸው ዘንድ  በዘርፉ ትልቅ ልምድ ካከበቱ የግል ሴክተር ጋር በአጋርነት ለመስራት ዉሳኔ አሳልፏል።

የተለያዩ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ላላቸው እና ተኪ ምርቶችን ለሚያመርቱ ኢንዱስትሪዎች ባቀረቡት የማስፋፊያ ቦታ ጥያቄዎች በሙሉ ድምፅ ፅድቋል።

ካቢኔው የኮሪደር ልማት ውጤት ከሆኑት ሥራዎች አንዱ የብዙሀን ትራንስፖርት መሠረተ ልማት ችግሮች የሚያቃልል እና የትራፊክ ፍስቱን የሚያሻሽለው የብስክሌት መጋራት አገልግሎት እና የብስክሌት መስመር አጠቃቀም ደንብንም  አፅድቋል።


ዳሽን ባንክ እና ኤም-ፔሳ ሳፋሪኮም ዓለም አቀፍ ሃዋላን የሚያዘምን አገልግሎት በጋራ አስጀመሩ

ተቋማቱ ለዓለም አቀፋ የሀዋላ አገልግሎት ካሽ ጎን እንደሚጠቀሙም ዛሬ ስምምነት ባደረጉበት ወቅት ተናግረዋል።

ስምምነቱ፤ ኢትዮጵያዊያን ከውጭ በቀጥታ በካሽ ጎ ሞባይል አፕልኬሽን አማካይነት ወደ ኤምፔሳ ገንዘብ የሚላክበትና መቀበል የሚቻልበትን ዕድል የሚፈጥር እንደሆነም ተነግሮለታል፡፡

ዛሬ ይፋ የተደረገው ስምምነት፤ የሐዋላ ገንዘብ ልውውጥን አስተማማኝና ቀልጣፋ የሚያደርግ ነው ሲሉ የዳሸን ባንክ ዋና ስራ አስፈፃሚ ተወካይና ቺፍ ሬቴይል እና ኤም ኤስ ኤም ኢ ኦፊሰር አቶ ይህንዓለም አቅናው አስረድተዋል።

የኤም-ፔሳ ሳፋሪኮም በመወከል በመድረኩ ንግግር ያደረጉት፤ ኤልሳ ሙዞሊኒ ስምምነቱ የፋይናንስ አካታችነትን የሚያበረታታና አዳዲስ የዲጂታል የፋይናንስ መፍትሄዎችን ለማቅረብ ተጨማሪ ዕድል የሚፈጥር መሆኑን ተናግረዋል።

ይህን አገልግሎት ለሚጠቀሙ ደንበኞች ከዛሬ ጥር 29 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ለሶስት ወራት ከውጭ ሀገራት ገንዘብ ሲልኩ በዕለቱ ካለው ምንዛሪ የ10 በመቶ ተጨማሪ ጉርሻ እንደሚያገኙ በመድረኩ ሲነገር ሰምተናል፡፡


ስምንተኛው የአፍሪካ ቢዝነስ ፎረም ከአፍሪካ ህብረት ጉባኤ ጎን ለጎን እንደሚካሄድ ተገለጸ

ስምንተኛው የአፍሪካ ቢዝነስ ፎረም ከ38ተኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች መደበኛ ስብስባ ጎን ለጎን በመጪዉ የካቲት 10 በአዲስ አበባ  ይካሄዳል ተብሏል።

ፎረሙ " ከአቅም ወደ ብልፅግና ፤ የአፍሪካን ክልላዊ የእሴት ሰንሰለቶች ማንቀሳቀስ
በሚል መሪ ቃል አዲስ አበባ በሚገኘው የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን አዳራሽ (ኢሲኤ) ውስጥ ይደረጋል።

ፎረሙን የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን፣ የአፍሪካ ፋይናንስ ኮርፖሬሽን እና የአረብ ባንክ ለአፍሪካ የኢኮኖሚ ልማት በትብብር በትብብር ያዘጋጁታል።

ከመንግስት እና ከግል ኢንተርፕራይዞች፣ ከልማት አጋሮች ፣ የሀገር ውስጥ እና አለም አቀፍ አልሚዎች፣ የፋይናንስ ተቋማት እና የማህበረሰብ ድርጅት ተወካዩች በፎረሙ እንደሚሳተፉ የመንግስት ሚዲያ ዘግቧል።


"ዓይነ ርግብ" መጽሐፍ ነገ ይመረቃል

በደራሲ ትዕግሥት ሳሙኤል የተዘጋጀው "ዓይነ ርግብ" መጽሐፍ ነገ አርብ ጥር 30 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 11:00 ጀምሮ በወመዘክር (ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወ/ሥላሴ አዳራሽ)ውስጥ ይመረቃል።

በዕለቱም ልዩ ልዩ ኪነጥበባዊና የትውውቅ መርሐግብሮች እንደሚኖሩ አዘጋጆቹ አስታውቋል።


በኤሌክትሮኒክ የነዳጅ ግዥ ስርአት ሁሉም ባንኮች ሊካተቱ ነዉ

በነዳጅ ሽያጭ እየተሳተፉ የሚገኙት ቴሌ ብር፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና አንድ የግል ባንክ ብቻ የነበሩ ሲሆን አሁን ግን መንግስት ሌሎች የፋይናንስ ተቋማት መሳተፍ እንዲችሉ የወሰነ መሆኑ ታውቋል።

የነዳጅ ገበያውን ለማዘመን እና ህገወጥ አሰራርን ለማስቀረት በማሰብ መንግስት የነዳጅ ሽያጭ በሞባይል የክፍያ ስርአት ብቻ እንዲከናወን ወስኖ እየተተገበረ እንደሚገኝ ይታወሳል።

በዚህም ዘመናዊውን የግዥ መተግበሪያ/አፕ ያበለፀገው ኩባንያ ሌሎች ባንኮችን ለማካተት እየሰራ ሲሆን ባንኮቹ ግን ከመቼ ጀምሮ ወደ ስርአቱ ይገባሉ የሚለው አለመታወቁን ነው የተገለጸው ።

capitalethiopia


የሲቪልና የቤተሰብ ምዝገባ ስርዓት አዋጅ ጸደቀ

በዚሁ ጊዜ ምክር ቤቱ የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሲቪልና የቤተሰብ ምዝገባ ስርዓትን ለመወሰን የወጣውን ረቂቅ አዋጅ አስመልክቶ ያቀረበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሀሳብ አድምጧል።

የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ ዲማ ነጎ (ዶ/ር)፥ የሲቪልና የቤተሰብ ምዝገባ የመንግስት አገልግሎቶችን ለማቀላጠፍና የዜጎችን የወሳኝ ኩነቶች መረጃ በተደራጀ መልኩ ለመያዝ ያስችላል ብለዋል።

በአግባቡና በወቅቱ የተመዘገቡ ወሳኝ ኩነቶችና የቤተሰብ ምዝገባ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ የልማት ዕቅዶችን በማሳካት ዜጎችን ተጠቃሚ ለማድረግ ሚናቸው የላቀ መሆኑንም ጠቁመዋል።

ከዚህ አኳያ የሲቪልና የቤተሰብ ምዝገባ አዋጅ ከኢትዮጵያውያን ባለፈ ነዋሪነታቸውን በኢትዮጵያ ያደረጉ የውጭ አገር ዜጎች እንዲመዘገቡና የተሻለ የደህንነት ጥበቃ እንዲኖር እንደሚያስችልም ነው ያነሱት።

አዋጁ የሚመለከታቸው አካላት በህግ በሚሰጣቸው ስልጣንና ሃላፊነት መሰረት በቅንጅት እንዲሰሩ ዕድል ይፈጥራል ብለዋል።

የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ሰላማዊት ዳዊት በበኩላቸው፥ ቀደም ሲል በነበረው አዋጅ የሲቪል ምዝገባው በአግባቡና በተደራጀ  መልኩ ባለመቀመጡ በጉዞና በተለያዩ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ላይ ክፍተት ፈጥሯል ብለዋል።

በሌሎች አገሮች የተጠናከረ የሲቪልና የቤተሰብ ምዝገባ በመኖሩ አገልግሎቶችን ፈጣንና ቀልጣፋ ማድረግ ማስቻሉንም ጠቅሰዋል።

ልደትና ጋብቻን ጨምሮ ወሳኝ ኩነቶችን በአግባቡ መዘግቦ መያዝ ለሀገር የልማት ፖሊሲ ዝግጅትና ክለሳ ወሳኝ ነው ብለዋል።

አዋጁ በሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች በሚደረጉ የሲቪልና የቤተሰብ ምዝገባዎች በቴክኖሎጂ ታግዘው በተናበበ መልኩ እንዲሆን አጋዥ መሆኑንም ጠቅሰዋል።


የሆስፒታሉ የቀዶ ጥገና ዋርድ በቅርቡ በተገደለው ዶ/ር አንዱአለም ስም እንዲሰየምና ሓውልት እንዲቆምለት ዩኒቨርሲቲው ወሰነ

የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሴኔት፤ የጥበበ ግዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የቀዶ ጥገና ዋርድ በቅርቡ በተገደለው ዶ/ር አንዱ አለም ስም እንዲሰየምና በሆስፒታሉ ግቢ ሓውልት እንዲቆምለት ወሰነ። በግድያው ላይም ጥልቅ ምርመራ እንዲደረግ እና እጃቸው ያለበት አካላት በአፋጣኝ ለህግ እንዲቀርቡ እንዲደረግ ጠይቋል።

ዩኒቨርቲው ዛሬ ባወጣው መግለጫ፤ የ37 አመቱ ዶ/ር አንዱአለም የቀረቡለትን በርካታ ዓለምአቀፍ የስራ ቅጥር ግብዣዎች ባለመቀበል ወገኑን ለማገልገል ቆርጦ የነበረ ባለሙያ መሆኑን ገልጿል።

ዶ/ር እንዱአለም በጥበበ ግዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ታሪክ “የመጀመሪያውን ቀዶ ጥገና ስራ መስራቱን” የገለጸው ዩኒቨርሲቲው እስከ ህልፈቱ ድረስ ሆስፒታሉ ደረጃውን በጠበቀ መልኩ ለማሳደግ ከፍተኛ ጥረት ሲያደርግ እንደነበርም አስረድቷል።


የአሜሪካ ተራድኦ ድርጅት እርዳታ ማቋረጡ ኢትዮጵያ በኤች አይ ቪ ላይ የምታደርገውን ትግል አደጋ ላይ የሚጥል መሆኑን የመንግስታቱ ድርጅት አስታወቀ

ከሩብ ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ የቫይረሱ ተጠቃሚዎችን ለአደጋ ያጋልጣል ሲል አስጠንቅቋል

ከኤች አይ ቪ/ኤድስ ጋር በተያያዘ #የአሜሪካ መንግስት ለኢትዮጵያ የሚሰጠው ድጋፍና እርዳታ መቋረጥ በኦሮሚያ እና ጋምቤላ ክልሎች እንዲሁም በአዲስ አበባ ከተማ ለሚገኙ ከ270 ሺ በላይ ለሚሆኑ የቫይረሱ መከላከያ መድሃኒት ተጠቃሚዎችን ህይወት ይበልጥ ከባድ ያደርገዋል ሲል የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የኤች አይ ቪ/ኤድስ ፕሮግራም አስጠንቀቀ።

በርካቶች ኤች አይቪን ጨምሮ በግብረ ሥጋ ግንኙነት ወቅት የሚተላለፉ በሽታዎችን ለመከላከል የሚውል ኮንዶም ከአሁን በኋላ አይደርሳቸውም ብሏል።

በተጨማሪም የገንዘብ ድጋፍ መቋረጡ የአካባቢ ጤና አጠባበቅ አቅም ለመገንባት የሚደረገውን ጥረት እንዳያደናቅፈው ስጋት እንዳለው አስታውቋል፤ የጤና ባለሙያዎች የሚሰጡት ስልጠና ላይ ተፅዕኖ በማሳደር በኢትዮጵያ የኤችአይቪ በሽታ መከላከል ሂደት ላይ እየተመዘገበ ያለውን እድገት ያዘገየዋል ሲል አመልክቷል።

18 last posts shown.