“የኢትዮጵያ ህብረብሔራዊ አንድነት ግንባታ ተሞክሮና ተግዳሮት” በሚል ርዕስ ሴሚናር ተካሄደ፡፡
ጥር 27/2017 ዓ.ም፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ
በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ በታሪክና ቅርስ አስተዳደር ትምህርት ክፍል “የኢትዮጵያ ህብረብሔራዊ አንድነት ግንባታ ተሞክሮና ተግዳሮት” በሚል ርዕስ በተዘጋጀ ሴሚናር ውይይት ተካሄዷል፡፡
የውይይት መነሻ ጽሑፉን ያቀረቡት የወሎ ዩኒቨርሲቲ የታሪክ መምህርና ተመራማሪ አለማየሁ እርቅይሁን (ዶ/ር) ሲሆኑ ኢትዮጵያ በመንግስት መዋቅር ስትመራ ቀደምት ሀገር መሆኗን ጠቅሰው ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ብሔርን ያማከለ መንግስት ለመገንባት በሚደረገው ሂደት የሚስተዋሉ ክፍተቶችን በመጠቀም የአንዳንዶችን መብት የሚጥስ ድርጊት ይፈጸማል ብለዋል፡፡ ሀገራችን ኢትዮጵያም ብዝሀነትን የምታስተናግድበት መንገድ ላይ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን አንስተው በህብረ ብሄራዊ አንድነት እና ግንባታ ሂደት መፍትሄ ያሏቸውን ሃሳቦችንም ጠቁመዋል፡፡
በሴሚናሩ የተገኙት የምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዝደንት ክንዴ ብርሃን (ዶ/ር) የኢትዮጵያን ህረብሔራዊ አንድነት ግንባታ በአተገባበር ላይ የምሁራን ድርሻ በእንዲህ አይነት ትምህርታዊ ጉባኤዎች የኢትዮጵያዊያን አንድነትን የሚያጠነክሩ ጉዳዮችን ማምጣት ይጠበቃል ብለዋል፡፡ እንዲህ ዓይነት ውይይትና ምሁራዊ እይታን ወደ መድረክ ማምጣት ችግሮችን ለመፍታት ወሳኝ ነውም ብለዋል፡፡
በሴሚናሩ መምህራን እና ተመራማሪዎች የተሳተፉ ሲሆን በቀረበው መነሻ ጽሑፍ ላይ አስተያየት እና ጥያቄ ተነስተው ማብራሪያ እና ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል፡፡
ጥር 27/2017 ዓ.ም፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ
በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ በታሪክና ቅርስ አስተዳደር ትምህርት ክፍል “የኢትዮጵያ ህብረብሔራዊ አንድነት ግንባታ ተሞክሮና ተግዳሮት” በሚል ርዕስ በተዘጋጀ ሴሚናር ውይይት ተካሄዷል፡፡
የውይይት መነሻ ጽሑፉን ያቀረቡት የወሎ ዩኒቨርሲቲ የታሪክ መምህርና ተመራማሪ አለማየሁ እርቅይሁን (ዶ/ር) ሲሆኑ ኢትዮጵያ በመንግስት መዋቅር ስትመራ ቀደምት ሀገር መሆኗን ጠቅሰው ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ብሔርን ያማከለ መንግስት ለመገንባት በሚደረገው ሂደት የሚስተዋሉ ክፍተቶችን በመጠቀም የአንዳንዶችን መብት የሚጥስ ድርጊት ይፈጸማል ብለዋል፡፡ ሀገራችን ኢትዮጵያም ብዝሀነትን የምታስተናግድበት መንገድ ላይ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን አንስተው በህብረ ብሄራዊ አንድነት እና ግንባታ ሂደት መፍትሄ ያሏቸውን ሃሳቦችንም ጠቁመዋል፡፡
በሴሚናሩ የተገኙት የምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዝደንት ክንዴ ብርሃን (ዶ/ር) የኢትዮጵያን ህረብሔራዊ አንድነት ግንባታ በአተገባበር ላይ የምሁራን ድርሻ በእንዲህ አይነት ትምህርታዊ ጉባኤዎች የኢትዮጵያዊያን አንድነትን የሚያጠነክሩ ጉዳዮችን ማምጣት ይጠበቃል ብለዋል፡፡ እንዲህ ዓይነት ውይይትና ምሁራዊ እይታን ወደ መድረክ ማምጣት ችግሮችን ለመፍታት ወሳኝ ነውም ብለዋል፡፡
በሴሚናሩ መምህራን እና ተመራማሪዎች የተሳተፉ ሲሆን በቀረበው መነሻ ጽሑፍ ላይ አስተያየት እና ጥያቄ ተነስተው ማብራሪያ እና ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል፡፡