የ ቅዱስ ጴጥሮስ ግቢ ጉባኤ ዲጅታል ቤተ-መጽሐፍ


Channel's geo and language: Ethiopia, English
Category: Books


ይህ የተለያዩ መንፈሳዊ መጻሕፍት የሚጋሩበት የ ቅዱስ ጴጥሮስ ግቢ ጉባኤ ዲጅታል ቤተ-መጽሐፍ ነው።
ለመወያየት : ለገንቢ ሀሳባት እና ለመጻሕፍት ጥቆማ @timbri7 እንዲሁም @YNSel

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, English
Category
Books
Statistics
Posts filter


ሰላም ውድ የእግዚአብሔር ልጆች እንዴት ሰነበታችሁ

💫 እግዚአብሔር ወዶ እና ፈቅዶ እስከ ዛሬዋ እለት የነበረንን የዲያቆን ሄኖክ ሀይሌን የብርሃን እናት የተሰኘውን መፅሀፍ የንባብ challenge በዛሬው እለት አጠናቀናል።

🌷 እግዚአብሔር ይመስገን 🌷

አብራችሁን ለነበራችሁ ውድ አንባቢያን እንዲሁም አድማጮቻችን በሙሉ በቅዱስ ጴጥሮስ ግቢ ጉባኤ ቤተ መፅሐፍት ክፍል ስም እግዚአብሔር ይስጥልን




የብርሃን እናት የመጨረሻዎቹ ገፆች .pdf
3.4Mb



🌷🌷የዝምተኛዋ ንግግሮች🌷🌷




የብርሃን እናት ከገፅ 340-375.pdf
3.0Mb
🌹የጻድቃን ቀጠሮ🌹


✨️ ብፅዕትና ብፁዓን
✨️ነቢይት ማርያም
✨️የዝምተኛዋ ንግግሮች..


🌺🌺🌺የብርሃን እናት🌺🌺

🌹🌷ቅምሻ🌺🌷🌷
አንዳንድ አሳዛኝ ሰው ድንግል ማርያምን 'አንደ እኔ ሰው እኮ ናት' የሚል ምክንያት በማቅረብ ከእርሱ በምንም የማትለይ እንደሆነች ሊከራከርና ክብርዋን ሊያሳንስ ይሞክራል፡፡ ወዳጄ እውነት አንተ እንደ እርስዋ ነህ? ብርሃናዊ መልአክ ከፊትህ ቆሞ አመስግኖህ ያውቃል? እንኳንስ ከሰማይ የተላከ እንግዳ መልአክን ቀርቶ አብሮህ ያለውን ጠባቂ መልአክህንስ አይተኸው ታውቃለህ? እንደ ድንግሊቱ የመላእክትን ዝማሬ ከሆድህ ውስጥ ሰምተሃል? እግዚአብሔር እንኳንስ በእንተ
ሊያድር በሕልም እንኳን አነጋግሮህ ያውቃል? እውነቱን ንገረኝ ካልከኝ እንኳን ሊወለድብህ በቃል ሊያነጋግርህም አልመረጠህም፡፡
በዚህ ትዕቢትህ ከጸናህ ደግሞ ለሰማዩም እፈራልሃለሁ፡፡ በሰማይ በእግዚአብሔር ፊት ቁም ብትባል ስለድንግሊቱ አሁን የተናገርከውን
ነገር በፊቱ ደግመህ ትለዋለህ? እግዚአብሔርን 'አናትሀ ከእኔ በምንም አትበልጥም" - ልትለው - ትደፍራለህ? በክንፎቻቸው ተሸፍነው የሚያመሰግኑት በንጽሕናቸው ወንድሞችዋ የተባሉ ኪሩቤልና ሱራፌል እንኳን እንዲህ ሊሏት አይደፍሩም፡፡ ይህ ዓይነቱ አነጋገር እግዚአብሔር
'በውኑ ባሪያዬን ኢዮብን ተመለከትኸውን? በምድር ላይ አገደ አርሱ ፍጹምና ፥ አግዚአብሔርንም የሚፈራ፣ ከክፋትም የራቀ ሰው የለም' ብሎ ሲነግረው እግዚአብሔር ደስ የተሰኘበትን ጻድቅ ሰው የኢዮብን ከብር ለማሳነስ ምክንያት ከደረደረው ከዲያብሎስ ንግግር ጋር ተመሳሳይ
ነውና አስተውለህ ተናገር፡፡




የብርሃን እናት ከገፅ 308-340.pdf
2.6Mb
🌹የጻድቃን ቀጠሮ🌹


✨️ መዝሙረ ድንግል
✨️ያመነች ብፅዕት


🌺🌺🌺🌺የብርሃን እናት🌺🌺🌺

🌹🌹ቅምሻ🌹🌹

ድንግል ማርያም ለእርስዋ የተደረገላትን ለኤልሳቤጥ ከተደረገው ነገር ጋር አላነጻጸረችም፡፡ 'ኤልሳቤጥ ካረጀች በኋላ መፅነስዋ ምን ይገርማል? አኔ ያለ ወገድ ዘር የፀነሰሁ አይደለሁምን? ኤልሳቤጥ የልጅ እናት ልትሆን መብቅትዋስ ምን ይገርማል? አኔ የአምላክ እናት ልሆን አይደለምን?" ብላ ሳትኩራራ የኤልሳቤጥን ታናሽ ደስታ ልትካፈል ተነሣች፡፡ በብርሃናዊ መልአክ 'ደስ ይበልሸ' የተባለችው ድንግል በማግስቱ አንዲትን ሴት 'ደስ ይበልሽ' ልትል ጉዞ መጀመርዋ ምንኛ የሚያስደንቅ ነው? 'ከሴቶች ሁሉ የተባረክሽ ነሸ የተባለላት ድንግል ከእርስዋ የምታንሰውን ከሴቶች አንዲቱን ልትጎበኝ መቸኮሏስ ምንኛ ድንቅ ነው?




የብርሃን እናት ከገፅ 286-308.pdf
2.0Mb
✨️ምዕራፍ ፬✨️
🌹የጻድቃን ቀጠሮ🌹

🔶 ፈጥና ወጣች
🔶 ያልተወለደው ባለቅኔ




የብርሃን እናት ከገፅ 257-286.pdf
2.5Mb
🌹ምዕራፍ ፫🌹

☀ከፀሐይ አጠገብ የነበረው ኮከብ✨️


.....በእውነት ይህች ድንግል ስለእርስዋ 'ታማልዳለች ወይስ አታማልድም' በሚል ተራ ክርክር ላጠፋነው ጊዜ ይቅር ትበለን፡፡ ወዳጄ የአንተን ጊዜያዊ ችግር ለመፍታትስ ማንኛውም ተራ ሰው  ሊጸልይልህ ይችላል፡፡ ቅዱስ ጳውሎስም ለሁላችን 'ምልጃ ይደረግ ሰለ አናንተ ሲያማልዱ ይናፍቋችኋል ክፋት ሲናገሩን አንማልዳለን ብሎ እርስ በእርሳችን አንዳችን ለሌላችን ልንማልድ እንደምንችል ጽፎአል፡፡ መቼም አብዛኛው ጥያቄያችን ከሥጋ አያልፍምና ደህና ገንዘብና ሥልጣን ያለውም ሰው የአንተን ችግር ለመፍታት አያንስም፡፡ 'ይሁንልኝ' የሚል የእምነት ቃልዋን ተናግራ ሰማይና ምድርን በማሕፀንዋ ያስታረቀች የእግዚአብሔር ውድ ፍጥረት ድንግል ማርያም አንተን አማልዶ ማስታረቅ ትልቅ ነገር የሚሆንባት ይመስልሃል?
✨እውነት ለመናገር ለእኛ ተራ ጉዳይ 'አታማልድም' ብሎ መወዛገብ ቀርቶ 'ታማልዳለች'" ብሎ መናገርም ከክብርዋ ጋር የማይመጥን ተራ መልስ ነው፡፡ ስለ ሌሎች ጻድቃን እንኳን 'የጌታ ዓይኖች ወደ ጻድቃን ናቸው ፤ ጆሮዎቹም ለጸሎታቸው ተከፍተዋል' ተብሏል፡፡ ድንግል ማርያም ግን እናት ለልጅዋ እንደምታወራ የሰማይና ምድርን ፈጣሪ በእቅፍዋ ይዛ በጆሮቹ የእናትን የፍቅር ቃል ያፈሰሰች ናትና ከየትኛውም ሰው ድምፅ በላይ የእርስዋ ቃል ለፈጣሪ ጆሮ ጣዕም ያለው ነው፡፡
ከ" የብርሃን እናት " መጽሐፍ የተወሰደ




የብርሃን እናት ከገፅ 232-257.pdf
2.3Mb
🌹የምሕረት አዋጅ🌹
                 •
                 •
                 •
    🌸የፍጥረት ናፍቆት




የብርሃን እናት ከገፅ 208-232.pdf
1.9Mb
🌹የምሕረት አዋጅ🌹
                 •
                 •
                 •
    🌸የአብርሃም ድንኳን


​​​​🥖 ደብረ ታቦር 🥖

          ክፍል ሦስት [፫]

ከዚህ በኋላ ጴጥሮስ "ጌታ ሆይ በዚህ መሆን ለእኛ መልካም ነው" ሲል ተደምጧል፡፡ ይህም የተለያየ ትርጉም አለው፡፡ ቃል በቃል (Literaly) ስናየው ቅዱስ ጴጥሮስ ጌታ ሆይ በዚህ መኖር ለእኛ መልካም ነው ማለቱ "አንተ እያበላኸን እየፈወስከን፣ ሙሴ እነዚህ መከራ ያደርሱቡኛል ይገድሉኛል ያልካቸውን ጸሐፍትና ፈሪሳውያን እንዳይመጡ በደመና እየጋረደ፣ ቢመጡም አልያስ እሳት እያዘነመ እያባረራቸው በዚህ መኖር ለእኛ መልካም ነው" ማለቱ ሲሆን ምሥጢራዊው መልእክቱ ግን "የኢየሱስ ክርስቶስ የባሕርይ አምላክነት በሚታመንበት፣ ወልድ ዋሕድ በምትለው ሃይማኖት መኖር ለእኛ መልካም ነው፡፡
ሰይጣን ድል በተደረገባት በታቦር ተራራ ምሳሌም በምትሆን በወንጌል ሕይወት፣ አንድም በቤተ ክርስቲያን መኖር ለእኛ መልካም ነው"
ማለቱ ነው፡፡

ታቦር ተራራ የወንጌል ምሳሌ ነው!

ተራራ ሲወጡት ያደክማል፣ ከወጡት በኋላ ግን ጭንጫውን፣ ግጫውን ሲያሳይ ደስ ያሰኛል፡፡ ወንጌልም ሲማሯት ትከብዳለች በኋላ ግን ጽድቅን እና ኃጢአትን ለይታ ስታሳውቅ ደስ ታሰኛለች፡፡

ታቦር ተራራ የቤተክርስቲያን ምሳሌ ነው!

ሀ/⏩ በታቦር ተራራ ከብሉይ ኪዳን ነቢያት ኤልያስና ሙሴን፣ ከሐዲስ ኪዳን ሦስቱን ሐዋርያት እንደተገኙ በቤተክርስቲያን ብሉይ ከሐዲስ እንዲነገር ያጠይቃል ፤ ሐዋርያት የሰበኩት ወንጌል አስቀድመው ነቢያት በምሳሌና በትንቢት የተናገሩት እንደሆነ ያስረዳል፡፡ "ነቢያት በቀየሱ ሐዋርያት ገሰገሱ" እንዲል ጳውሎስም "በሐዋርያት በነቢያት መሠረት ላይ ታንጻችኋል" ይላልና ኤፌ ፪፥፳

ለ/⏩ በታቦር ተራራ ከመዓስባን (ባለትዳር) ሙሴን ከደናግል ደግሞ ኤልያስ እንደተገኙ በቤተክርስቲያን በድንግልና የሚኖሩ መናንያን መነኮሳት፣ በሕግ በሥርዓት የሚኖሩ ባለትዳሮችም ይገኛሉና፡፡

ታቦር ተራራ የመንግሥተ ሰማያት ምሳሌ ነው!

1/➡️ ተራራ በብዙ ችግር እንዲወጡት ወደ እግዚአብሔር መንግሥትም በብዙ መከራ እንገባ ዘንድ ያስፈልገናልና
ሐዋ ፲፬፥፳፪

2/⏩ በታቦር ተራራ የብሉይ ኪዳን ነቢያት ከሐዲስ ኪዳንም ሐዋርያት እንደተገኙ መንግሥተ ሰማያትን ነቢያትም፣ ሐዋርያትም አንድ ሆነው ይወርሷታልና፡፡

3/⏩ በታቦር ተራራ ከመዓስባን ሙሴ ከደናግል ደግሞ ኤልያስ እንደተገኙ መንግሥተ ሰማያትንም ደናግልም መዓስባንም በአንድ ላይ ይወርሷታልና፡፡

4/⏩ በታቦር ተራራ ሞተው ከተቀበሩት መካከል ሙሴን በብሔረ ሕያዋን ካሉት ደግሞ ኤልያስን እንደመጡ መንግሥተ
ሰማያትንም ሞተው የተቀበሩትም በብሔረ ሕያዋን ያሉትም በአንድነት ይወርሷታልና፡፡

5/⏩ ደብረ ታቦር የቤተ መቅደስ ምሳሌ ናት በቅድስት ቤተክርስቲያን ለሥርዓተ ቅዳሴ የሚሰየሙ ካህናት (ልዑካን)
አምስት ናቸው ሙሴና ኤልያስ የካህናት ጴጥሮስ ፣ዮሐንስ፣ያዕቆብ የዲያቆናት ምሳሌ ጌታችን አምላካችን
የሊቀካህናት ምሳሌ ናቸው።

6/⏩ ደብረ ታቦር የቤተ ክርስቲያን ምሳሌ ናት በብሉይ የክርስቶስን መገለጥ የተናገሩ ነብያት በሐዲስ ኪዳን የተገለጠውን የእግዚአብሔር አብ የባህርይ ልጅ ኢየሱስ ክርስቶስ ለዓለም የሰበኩ ሐዋርያት በአንድ ሆነው የተገኙባት ጌታቸውንበአንድነት ያመሰገኑባት ናት።

በአጠቃላይ ታቦር ተራራ የክርስቶስ የባሕርይ አምላክነት የተመሠከረበት፣ የምሥጢረ ሥላሴ ትምህርት የተሰጠበት፤ ፈጣሪ ከቅዱሳን ሰዎቹ ጋር የተገኘበት፤ በልበ ሐዋርያት የነበረ ሰይጣን ድል የተደረገበት፤ የሐዋርያት በተለይም የሦስቱ ባለሟልነት የተገለጠበት፤ አሉባልታና ተራ ወሬ የከሸፈበት፤ የቅዱሳንን ክብር ለሚያናንቁ ተራራም እንኳን "ቅዱስ" እንደሚባል የተማርንበት፤ የብሔረ ሕያዋን መኖር የተመሰከበረበት፤ የትንሣኤ ሙታን ዋስትና የተገለጠበት የክብር ሰገነት፣ የምሥጢር መቅደስ፣ ታላቅ ትምህርት ቤትም ጭምር ነው፡፡

ፈጣሪያችን እግዚአብሔር እስከ መጨረሻዋ ሕቅታ ድረስ በታቦር ተራራ በተመሰለች ቤተ ክርስቲያን በሃይማኖታችን ጸንተን የመንግሥተ ሰማያት ወራሾች የስሙ ቀዳሾች እንድንሆን የእግዚአብሔር ቸርነት የድንግል ማርያም አማላጅነት አይለየን፡፡ አሜን!!

     ወስብሐት ለእግዚብሔር
               ~ተፈጸመ~


              🌺  ክፍል ሁለት [፪]  🌺

✝ለምን ሦስቱን ሐዋርያት ብቻ ይዞ ወጣ?

1⃣ጌታ "እሞታለሁ፤ እሰቀላለሁ" ባለው ጊዜ ጴጥሮስ "ልትሞት አይገባም፤ ይህ ላንተ አይገባም" ብሎ ተቃውሞት ነበርና በአብ ቃል "እርሱ ያላችሁን ስሙት፤ ይህ ለአንተ አይገባም አትበሉት፤ አትቃወሙት" ለማለት፡፡

2⃣ ጌታ "እናንተስ ማን ትሉኛላችሁ?" ብሎ ደቀመዛሙርቱን በጠየቃቸው ጊዜ ጴጥሮስ "አንተ የሕያው የእግዚአብሔር ልጅ ነህ" ብሎት ነበርና አሁንም አብ "አዎ ልክ ነህ! እመለክበት ዘንድ ለተዋሕዶ የመረጥኩት የምወደው ልጄ ይህ ነው" ብሎ ለማረጋገጥ፡፡

3⃣ ለፍቅሩ ስለሚሳሱ ነው፡፡ ይህም በዕብራይስጡ ኬፋ ፤ በግሪኩ ጴጥሮስ ፤ በግዕዙ ኰኲሕ (ዐለት) የተባለው የዮና ልጅ ስምዖን ጌታችን "እሞታለሁ" እያለ ሲናገር "እሞታለሁ" ማለቱ አስቀድመን እንደተናገርን "ለጌታ ካለው ፍጹም ፍቅር የተነሣ ነው" ይላል ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ፡፡

ዮሐንስም በወንጌል "የጌታ ወዳጅ" ተብሎ ተጽፏል፡፡ ያዕቆብ ደግሞ ጌታን በእጅጉ እንደሚወደው በኋላ ታውቋል፡፡ ይኸውም "እኔ የምጠጣውን ጽዋ ትጠጣላችሁ?" ማቴ ፳፥፳ ሲባሉ "አዎ" ብሎ መመለሱና በዚህም በሄሮድስ ዘአግሪጳ ሰማዕት ሆኖ መሞቱ ምስክር ነው፡፡

4⃣በይሁዳ ምክንያት ነው፡፡ "ኃጥእ ሰው የእግዚአብሔርን ክብር እንዳያይ ያርቁታል" እንዲል ኢሳ ፳፮፥፲፫ እርሱን ጥሎ አሥራ አንዱን ወደ ተራራ ይዞ ቢወጣ ከምሥጢር ቢለየኝ በሞቱ ገባሁበት እንዳይል፡፡ ያም ባይሆን ስምንቱ ደቀ መዛሙርት ለምን ይከለከላሉ ቢሉ አልተከለከሉም በርእሰ ደብር (በተራራው አናት) ለሦስቱ ደቀ መዛሙርት የተገለጸው ምስጢር በእግረ ደብር (በተራራው ግርጌ) ለነበሩት ስምንቱ ደቀ መዛሙርት ተገልጦላቸዋል፡፡

ይህም በደብረሲና ለሰባው ሊቃናት የተገለጠ ምሥጢር በከተማ ለነበሩት ለኤልዳድና ሙዳድ እንደተገለጠ ማለት ነው ዘኁ፲፩፥፳፮

✝ኤልያስና ሙሴን ለምን አመጣቸው?

1⃣ በአንድ ወቅት ሙሴ እግዚአብሔርን  "በአንተ ዘንድ ባለሟልነትን ማግኘቴ እውነት ከሆነስ ፊት ለፊት ተገልጸህልኝ ልይህና በአንተ ዘንድ ባለሟልነትን ማግኘቴን ልወቀው" ሲል ጠይቆት ነበር፡፡ እግዚአብሔርም "ጀርባዬን ታያለህ ፊቴን ግን አታይም" ብሎት ነበር ዘጸ ፴፫፥፲፫-፳፫ የዚህ ኃይለ ቃል ትርጓሜና ሐተታ በደብረ ታቦር ተፈጽሟል፡፡

እንዲህ ማለቱ "አምስት ሺሕ አምስት መቶ ዘመን ሲፈጸም ሰው ሆኜ ሥጋ ለብሼ ኋላ በደብረ ታቦር እስክገለጽልህ ድረስ አንተ በመቃብር ተወስነህ ትኖራለህ" ማለቱ ነበርና፡፡ ይህን ማለቱ እንደሆነ የታወቀው ግን በደብረ ታቦር ሙሴን ከብሔረ ሙታን አምጥቶ ባቆመው ጊዜ ነበር፡፡

2⃣ ልዑል እግዚአብሔር ነቢዩ ኤልያስን፡- "አንተ በኋለኛው ዘመን ምስክር ትሆነኛለህ" ብሎት ነበር፡፡ ይኸውም ኃይለ ቃል ኤልያስ ከብሔረ ሕያዋን መጥቶ "የእኔን የኤልያስን ጌታ ማን ኤልያስ ነው ይልሃል? እግዚአ ኤልያስ፤ አምላከ ኤልያስ ይበሉህ እንጂ" ሲል በደብረ ታቦር ተፈጸመ፡፡ ታያለህ የተባለው ሙሴም አየ፣ ትመሰክራለህ የተባለው ኤልያስም መሰከረ፡፡

3⃣ በፊልጶስ ቂሳርያ ጌታ ሐዋርያትን "ሰዎች የሰውን ልጅ ማን እንደሆነ ይሉታል?" ብሎ በጠየቃቸው ጥያቄ ሲመልሱ "ሙሴ ነው ይሉሃል ፤ እንዲሁም የኃይል ሥራህን ተመልክተው ኤልያስ ነው ይሉሃል" ብለው ነበርና ሙሴን ከመቃብር ፤ ኤልያስን ከብሔረ ሕያዋን አምጥቶ እግዚአ ሙሴ ፤ አምላከ ሙሴ ፤ እግዚአ ኤልያስ ፤ አምላከ ኤልያስ መሆኑን ለማስመስከር፡፡

4⃣ አይሁድ ፈሪሳውያን ጌታን እንደ ሕግ ተላላፊና የእግዚአብሔርን ክብር ለራሱ የሚወስድ አድርገው ያስቡት ስለነበረ ዮሐ፱፥፲፮ ፣ ፲፥፴፫ ሕግን የሰጣቸው ሙሴንና ለሕገ እግዚአብሔር ቀናተኛ የነበረው ኤልያስን አምጥቶ ሕግ አፍራሽ አለመሆኑን የእግዚአብሔር ተቃዋሚም አለመሆኑን ለማስረገጥ፡፡

5⃣ ጌታችን በሙታንና በሕያዋን ላይ ሥልጣን ያለው እንደሆነ ይታወቅ ዘንድ ሞተው ከተቀበሩት ሙሴን ከብሔረ ሕያዋንም ደግሞ አልያስን አምጥቶ ሲነጋገር ታየ፡፡

6⃣ የሐዋርያቱን የወደፊት አገልግሎት ሲነግራቸው፡፡ ይኸውም ሙሴ እና ኤልያስ ለሕዝበ እስራኤል በጣም ታማኝ እንደነበሩ ሁሉ እነርሱም ለሚያገለግሉት ሕዝብ ታማኝ እረኞች እንዲሆኑ፡፡ ሆኖም ግን አገልግሎታቸው ከሙሴና ከኤልያስ ይልቅ ጠንከር እንደሚልም አሳይቶአቸዋል፡፡ ምክንያቱም ውጊያቸው እንደ ሙሴ ከፎርዖን እንደ ኤልያስም ከአክዓብ ጋር ሳይሆን ከክፋት መናፍስት ጋር ነውና፡፡

6⃣ ጽድቃቸው ከእነዚህ ከሙሴና ከኤልያስ የበለጠ ሊሆን እንደሚገባ ለማሳየት ማቴ፭፥፳ ምክንያቱም ሙሴ ሕዝበ እስራኤልን ቢመራ ምድረ ፍልሥጥኤምን ለማውረስ ነው፡፡ እነዚህ ግን ሕዝቡን መርተው የሚያስገቡት መንግሥተ ሰማያትን ነው፡፡ ኤልያስ ሰማያትን ቢለጉምም ከጊዜአዊ ዝናም ነው፡፡ እነዚህ ግን ለዘለዓለም መንግሥተ ሰማያትንም የመለጎም ሥልጣን አላቸውና፡፡

ከዚህ በኋላ ጴጥሮስ "ጌታ ሆይ በዚህ መሆን ለእኛ መልካም ነው" ሲል ተደምጧል፡፡ ይህም የተለያየ ትርጉም አለው፡፡ ቃል በቃል (Literaly) ስናየው ቅዱስ ጴጥሮስ ጌታ ሆይ በዚህ መኖር ለእኛ መልካም ነው ማለቱ "አንተ እያበላኸን እየፈወስከን፣ ሙሴ እነዚህ መከራ ያደርሱቡኛል ይገድሉኛል ያልካቸውን ጸሐፍትና ፈሪሳውያን እንዳይመጡ በደመና እየጋረደ፣ ቢመጡም አልያስ እሳት እያዘነመ እያባረራቸው በዚህ መኖር ለእኛ መልካም ነው" ማለቱ ሲሆን ምሥጢራዊው መልእክቱ ግን.....

 ክፍል ሦስት ይቀጥላል.....

20 last posts shown.