TGStat
TGStat
Type to search
Advanced channel search
  • flag English
    Site language
    flag Russian flag English flag Uzbek
  • Sign In
  • Catalog
    Channels and groups catalog Search for channels
    Add a channel/group
  • Ratings
    Rating of channels Rating of groups Posts rating
    Ratings of brands and people
  • Analytics
  • Search by posts
  • Telegram monitoring
ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

21 Jul 2023, 01:00

Open in Telegram Share Report

"እናንተን ንጹሐን ቅዱስ ሲኖዶስን ተወቃሽ የሚያደርገው አንዳችም ነገር የለም"

"በትግራይና በፌደራል መንግሥት፣ በትግራይና በአማራ ክልል ባለው አለመግባባት ችግሮችን ለመፍታት በምልዓተ ጉባኤ ቅዱስ ሲኖዶስ ፊት እናንተም ባላችሁበት ይህ ችግር በዚህ ሊቀጥል አይገባውም ችግር ከመፈጠሩ በፊት የሰላም ኮሚቴ ይቋቋም ብሎ ቅዱስ ሲኖዶስ ጮሗል? አልጮህም? እናንተስ በዚያን ጊዜ ምን ትሉ ነበር?

በመጨረሻም ቅዱስ ሲኖዶስ ጉዳዩን ተመልክቶ ችግሩን ለመፍታት በፌደራል መንግሥት፣ በትግራይና በአማራ ክልል ያለው ችግር እንዲፈታ እንደ ጥንቱ ታቦት ይዘን፣ መስቀል ይዘን፣ ሕዝባችንን እናገናኝ ዝም ብለን ማየት የለብንም ብሎ ቅዱስ ሲኖዶስ ሲጮህ ምን ነበር ያላችሁት አባቶች?

ደም በሚፈስበት ቦታ ላይ ሄዳችሁ አስታርቁ ትግራይ ለምን ሰላም ሆነ ነው ወይ ይህንን የምትሉ አላላችሁንም?

ቤተክርስቲያን ዝም አለች አላችሁ፤ ምነው ቤተክርስቲያን ምንም እንዳልተናገረች ደግማችሁ ደጋግማችሁ ተናገራችሁ፡፡ ያውም ከብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ስሕተትን ለማረም ስሕተት መደገም የለበትም፡፡ ቅዱስ ሲኖዶስ ዛሬም ጉዳዩን አይቶ ችግሩን ለመፍታት ይቅርታ የሚለውን ጥያቄም አቅርቧል፡፡ ነገም ያቀርባል በሚገባው በመልኩ በአንጻሩ ደግሞ የሠራው ያደረገው ነገር ሊቀበር አይገባውም ሊነገርለት ይገባል፡፡ ስለዚህ በዚህ ጥፋት ከሆነ እናንተም እኛም የጋራ ተወቃሾች እንሆናለን እንጂ እናንተን ንጹሐን ቅዱስ ሲኖዶስን ተወቃሽ የሚያደርገው አንዳችም ነገር የለም፡፡"

ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተ ክህነት
ዋና ሥራ አስኪያጅና የባህር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ

11k 0 20 189
Catalog
Channels and groups catalog Channels compilations Search for channels Add a channel/group
Ratings
Rating of Telegram channels Rating of Telegram groups Posts rating Ratings of brands and people
API
API statistics Search API of posts API Callback
Our channels
@TGStat @TGStat_Chat @telepulse @TGStatAPI
Read
Blog Telegram Research 2019 Telegram Research 2021 Telegram Research 2023
Contacts
Справочный центр Support Email Jobs
Miscellaneous
Terms and conditions Privacy policy Public offer
Our bots
@TGStat_Bot @SearcheeBot @TGAlertsBot @tg_analytics_bot @TGStatChatBot