ካቴድራሉም ተጠናቆ ተመርቆ ለአገልግሎት በመብቃቱ በጣም ደስተኞች ነን ብለዋል፡፡
ልዑካኑ ከብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ታዋድሮስ የግብጽ ኮፕቲክ ፓትርያርክ የተላከውን ስጦታ ለብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ያስረከቡ ሲሆን ቅዱስነታቸውም ስለ ስጦታው አመስገነዋል። ልዑካኑም ስለተደረገላቸው መልካም አቀባበልና ይሁንታ መደሰታቸውን ገልጸዋል።
አያይዘውም የቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በኢትዮጵያውያን ምእመናን ዕድሳቱ ተሠርቶ ማለቁ እጅግ ደስ እንዳሰኛቸው በመግለጽ የግብጽ ኮፕቲክ እንደተለመደው በካቴድራሉ መገልገል የሚችሉበት መንገድ ስለ ተመቻቸላቸው አመስገነዋል፡፡
ሜትሮፖሊታን በመጨረሻም ለኦርቶዶክሳውያን ምእመናን ባስተላለፉት መልእክት “ኢትዮጵያውያን በእምነታችሁ ጠንካራ ክርስቲያኖች ናችሁ፡፡ የሰይጣን ፈተና በመላው ዓለም ለምንኖር ክርስቲያኖች ቢሆንም እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ነው፤ ፈተናውን ያሳልፍልናል፡፡ በቤተክርስቲያን ሁናችሁ ጸልዩ" ሲሉ አባታዊ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡
ምንጭ :- የኢኦተቤ መገናኛ ብዙኀን አገልግሎት ሥርጭት ድርጅት
ልዑካኑ ከብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ታዋድሮስ የግብጽ ኮፕቲክ ፓትርያርክ የተላከውን ስጦታ ለብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ያስረከቡ ሲሆን ቅዱስነታቸውም ስለ ስጦታው አመስገነዋል። ልዑካኑም ስለተደረገላቸው መልካም አቀባበልና ይሁንታ መደሰታቸውን ገልጸዋል።
አያይዘውም የቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በኢትዮጵያውያን ምእመናን ዕድሳቱ ተሠርቶ ማለቁ እጅግ ደስ እንዳሰኛቸው በመግለጽ የግብጽ ኮፕቲክ እንደተለመደው በካቴድራሉ መገልገል የሚችሉበት መንገድ ስለ ተመቻቸላቸው አመስገነዋል፡፡
ሜትሮፖሊታን በመጨረሻም ለኦርቶዶክሳውያን ምእመናን ባስተላለፉት መልእክት “ኢትዮጵያውያን በእምነታችሁ ጠንካራ ክርስቲያኖች ናችሁ፡፡ የሰይጣን ፈተና በመላው ዓለም ለምንኖር ክርስቲያኖች ቢሆንም እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ነው፤ ፈተናውን ያሳልፍልናል፡፡ በቤተክርስቲያን ሁናችሁ ጸልዩ" ሲሉ አባታዊ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡
ምንጭ :- የኢኦተቤ መገናኛ ብዙኀን አገልግሎት ሥርጭት ድርጅት