የ ኦርቶዶክስ ቅዱሳን አባቶች ትምህታዊ ንግግሮች Wise sayings of holy fathers of orthodox


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: Religion


This channel's aim is to help us learn from the spritual life of holy fathers .

ከቅዱሳን አባቶች ትምህታዊ ንግግሮች እንማር ዘንድ የ ተዘጋጀ channel ነው።

ከቅዱሳን አባቶች ትምህታዊ ንግግሮች group https://t.me/joinchat/FXPZVEUP8KLHay0v0d0LuQ
አስተያየት ካላቹ በ @Wiseholyfathers_comment ይላኩልን።

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
Religion
Statistics
Posts filter


​​የካቲት 23 ከጠዋቱ 11 ሰዓት ሁሉም ከቅዳሴ ወጥተው ተባርከውና ተመርቀው ወደ ጦርነቱ ገቡ ። ካህናቱም ታቦታቸውን ይዘው ለሠራዊታቸውም ደጀን ሆነው የወደቀውን እያነሱ ፣ የጀገነውን እያበረቱ ውጊያው ጦፈ ። የሚገርመው " ነገር ሥጋወደሙ ለመቀበል ተዘጋጅተው የነበሩት ንጉሥ ተክለሃይማኖት ናቸው በግራ ክንፍ በኩል ሲዋጋ የነበረውን ጀነራል አልቤርቶኒን የማረኩት ። እውነት ይሄ የእግዚአብሔር እጅ የለበትም?

ልብ በሉ የጊዮርጊስ ዕለት በአዲስ አበባ አራዳ ከገነተ ጽጌ መናገሻ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ጸሎት አድርገው ። ከዚያው ከመናገሻ ገነተ ጽጌ ታቦተ ጊዮርጊስን ፣ ይዘው ወደ ጦር ሜዳ የሄዱት አጼ ምኒሊክ ፤ ጣልያንን የካቲት 23 የቅዱስ ጊዮርጊስ ዕለት በአድዋ ላይ ገጠሙት ። ይኽንን ቀን እምዬ ምኒልክ ለጦርነት አልመረጡትም ። የካቲት 22 ተነስቶ ሌሊቱን ስጓዝ ያደረው ራሱ የጣልያን ጦር ነው በድንገት ውጊያውን የከፈተው ። ምን አልባት ቅዳሴ ሳይጨርሱ አይዋጉም ብሎም አስቦ ሊሆን ይችላል ።

እጅግ የሰለጠነውና በዘመኑ እጅግ የረቀቀ የተባለ የጦር መሣርያ የታጠቀው የጣልያን ጦር ገና ሲነሳ ጀምሮ እስካሁን በመላ ምት እንጂ በውል ባልታወቀ ሁኔታ ሲተራመስ አድሮ እንዴት ከእንቅልፉ ሳይነቃ ጧት ላይ ጦርነት ገጠመ ? ያልን እንደሆነ መልሱ እንጃአባቱ ምንአባቱ እናውቅለታለን የሚል ይሆናል ።
ያም ሆነ ይህ አስቀዳሹ የኢትዮጵያ ጦር ከሰባት ሰዓታት ውጊያ በኋላ የካቲት 23/1888 ዓም የቅዱስ ጊዮርጊስ ዕለት ወራሪው ጣልያንን ፣ መንገድ መሪና ስንቅ አቀባይ ሰላዩን ባንዳና የባንዳ ዘርና ዘርማንዘሩን ሁሉ እስከ ልጅልጁ ጭምር አፈር ከድሜ አብልቶ ድባቅም መትቶ አሸነፈው ።

አባቶቻችን የቅዱስ ጊዮርጊስ ዕለት ከአዲስ አበባ ተነስተው ፣ የቅዱስ ጊዮርጊስን ታቦት ደጀን ይዘው ፣ የቅዱስ ጊዮርጊስ ዕለት ጦርነት ገጥመው ማሸነፋቸው ግጥምጥሞሽ አይደለም ። አይመስለኝምም ።

በደንብ እስከ አፍንጫው ታጥቆና ተዘጋጅቶ የመጣ ግዙፉ አውሮፓዊ ወራሪ የጦር ኃያል ፤ ቅዳሴ ላይ በነበረ የኢትዮጵያ የጦር ሠራዊት አይቀጡ ቅጣት ተቀጥቶ ተሸነፈ ።
መጽሐፍ " መንገድህን ለእግዚአብሔር አደራ ስጥ " እርሱም ያከናውንልሃልና ይላል ። በጦር ሠራዊት ብዛት ብቻ አታሸንፍም !!!
የአድዋው ጦርነት ሥጋዊ ብቻ አልነበረም መንፈሳዊ እጆችም ነበሩበት ።
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
@wiseholyfathers
አስተያየት ካላቹ በ @rafato_el ይላኩልን


​​ክፍል ሁለት

ቅዳሴ ላይ የነበረው የኢትዮጵያ ጦር
በማግስቱ የካቲት 23 ( የዓመቱ የጊዮርጊስ በዓል)

አድዋ የከተተው በንጉሠ ነገሥት ዳግማዊ እምዬ አጼ ምኒልክ እና በንግሥቲቱ እቴጌ ጣይቱ የሚመራው የኢትዮጵያ ሠራዊትና የጦር አዛዦቻቸው ደግሞ ቃኚ ጦር በየመንገዱ በተጠንቀቅ እንዲቆም አዝዘው እነሱ አድዋ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስትያን ቅዳሴ እያስቀደሱ ነው ። ማኅሌቱም ፣ ቅዳሴውም የተጀመረው ሌሊት ነው ። እነሱ ቅዳሴ ላይ እንዳሉ - ሊነጋጋ ሲል ከጠዋቱ አስር ሰዓት ላይ የተኩስ ድምስ ተሰማ ። ልብ በሉ ሁሉም የኢትዮጵያ አዛዦች ቅዳሴ ላይ ነበሩ ።ግብጻዊው ፓትርያርክ አቡነ ማቴዎስም ቀዳሽ ነበሩ ። ይህን ክስተት ጣልያናዊው የታሪክ ጸሐፊ እንዲህ ይተርከዋል

" ጦርነቱ ሲጀመር ንጉሥ ሚኒልክ ፣ ንጉሥ ተክለሃይማኖት ፣ ራስ መንገሻ ፣ ራስ መኮንን ፣ ፊታውራሪ ገበየሁ እና ሌሎችም ብዙ አለቆች አድዋ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስትያን ያስቀስድሱ ነበር ። ቀዳሹም አቡነ ማቴዎስ ነበሩ ። እሳቸውም በሚቀድሱበት ግዜ ክፍት በሆነው በር በኩል የጦርነቱ ተኩስ ወደ ውስጥ እየገባ ተሰማ ። ወድያው ተመልሰው የኢጣልያኖችን መምጣት ተናገሩ ። በዚህ ግዜ አጼ ምኒልክ የመደንገጥም ሆነ የመበርገግም ምልክት አልታየባቸውም ። በጸጥታ ቆመው ጥቂት ደቂቃዎች እንደቆዩ ወደ አቡነ ማቴዎስ ጠጋ ብለው ትንሽ ንግግር ከተለዋወጡ በኋላ ተመልሰው እስፍራቸው ቆሙ ። ከዚህ በኋላ አቡነ ማቴዎስ በቀኝ እጃቸው መስቀላቸውን ከፍ አድርገው ይዘው በዚያ ላሉት ሁሉ አስተዛዝነው በልቅሶ ጭምር እንዲህ አሉ።

"ልጆቼ ሆይ ዛሬ የእግዚአብሔር ፈቃድ የሚፈጸምበት ቀን ነው ። ሂዱ ለሃይማኖታችሁና ለንጉሣችሁ ሙቱ ። ኃጥአታችሁም ይሰረይላችኋል ። እግዚአብሔር ይፍታችሁ" አሉ ። አቡኑ ይህን ተናግረው ሲጨርሱ መኳንንቱ ሁሉ እየተሽቀዳደሙ የአቡኑን መስቀል ተሳልመው በመውጣት እያንዳንዳቸው በችኮላ ወደ ጦር ሰፈራቸው ሄዱ ። ":.. ንጉሥ ተክለሃይማኖት ብቻ ግን ቁርባን ለመቀበል አስበው ነበር ። አጼ ምኒልክም ኃጥአትዎ ወርዷል ይልቁንስ እዚህ መቆየት አደጋ ነው ስላሏቸው ወጥተው ሄዱ ። በቤተ ክርስትያኑ ውስጥ ግን ምኒሊክ ብቻ ቀሩ" ።


​​የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን በዐድዋ ድል የነበራት ድርሻ

ክፍል አንድ

ለጦርነቱ በቤተ ክርስቲያን ጸሎተ ምህላ ታውጇል፤ ዘማች ታቦታት ተመርጠው የአዝማች ኮሚቴም ተቋቁሟል፤ ታቦተ ቅዱስ ጊዮርጊስ የዘማች ታቦታቱ መሪ ነበር፤ ለመላው ዘማች ሠራዊት ሥነ ልቡናዊ ጥንካሬን (የሰማዕትነት ወኔን) የሰጠ የሰባት ቀናት የቁም ፍትሐት ተደርጓል፤ ሊቃውንቱ ከጦርነቱ በድል እንደምንመለስ በቅኔያቸው ትንቢት ተናግረዋል፤ ዐፄ ምኒልክ የክተት ዐዋጅ ካስነገሩ በኋላ ወደ አዲስ አበባ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ሄደው “አምላከ ቅዱስ ጊዮርጊስ ድሉን ቢሰጠኝ ይህን ቤተ ክርስቲያን የሣር ክዳኑን ለውጨ ባማረ ሕንጻ አሠራዋለሁ” ብለው ብፅዓት አድርገዋል፡፡

ከምርኮኛ የጣሊያን ወታደሮች አንዱ በዐውደ ውጊያው “በነጭ ፈረስ ተቀምጦ ወደ ቀኝ እና ወደ ግራ እየተመላለሰ ‹ወደ ጦርነቱ ግቡ፤ ኢጣሊያኖችን ማርኩ› እያለ ትእዛዝ ሲሰጥ እና ሲወጋን የዋለ ማነው?” ብሎ ጠይቋል፡፡ በጦር ሜዳ ለበቁት ሰዎች ተገልጦ እየታየ ከአርበኞቻችን ጋራ የዋለው ፍጡነ ረድኤት ቅዱስ ጊዮርጊስ የኢትዮጵያ ዐቃቤ መልአክ (Patron Saint) ነው፡፡ በዐድዋ ድል የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን የአንበሳ ድርሻ አላት፡፡

🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
@wiseholyfathers
አስተያየት ካላቹ በ @rafato_el ይላኩልን


​​ጾመ ሰብአ ነነዌ

‹‹ጾመ ሰብአ ነነዌ፤ የነነዌ ሰዎች ጾም›› የሦስት ቀን ጾም የጾሙት በነነዌ ይኖሩ የነበሩ ሰዎች ናቸው፡፡ ከተማዋም (ነነዌ) በጤግሮስ ወንዝ ዳርቻ የምትገኝ ስትኾን መሥራቿም ናምሩድ ነው (ዘፍ.፲፥፲፩-፲፪)፡፡ ጥንታዊቷ የነነዌ ከተማ ለአሦር መነሻ የሆነች፤ እጅግ ሰፊና ያማረች፤ የቅጥሯ ርዝመትም ፲፪ ኪሎ ሜትር የሚሸፈን ነበር፡፡ በከተማዋ ንጉሡ ሰናክሬም ብዙ ሕንጻዎችን ገንብቶ ነበር (ዮናስ ፬፥፲፩)፡፡
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
@wiseholyfathers
አስተያየት ካላቹ በ @Wisecomment_bot ይላኩልን

ሙሉውን ለማንበብ ይህን ይጫኑ 👇


​​"ቃለ እግዚአብሔር እምድንግል አስተርአየ ፤ ኤልሳቤጥ ኮነት ዓባየ ፤ እስመ ወለደት ነቢየ።" ቅዱስ ያሬድ

እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም መታሰቢያዋን ለሚያደርግ ስሟን ለሚጠራ በስሟ ለድኆችና ለችግረኞች ቀዝቃዛ ውኃ ለሚሰጥ የክብር ባለቤት ከሆነ ከተወደደ ልጅዋ ከጌታችንና ከመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የምሕረት ቃል ኪዳንን የተቀበለችበት በዓል ነው።

🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
@wiseholyfathers
አስተያየት ካላቹ በ @Wisecomment_bot ይላኩል


​​++++++ወይን እኮ የላቸውም++++++

የቃና ዘገሊላ ታሪክ ውስጥ አስደናቂ ከኾኑ ክስተቶች ውስጥ አንዱ የወይን ማለቅ ጉዳይ ነው። በእርግጥ ቃና ዘገሊላ ውስጥ የተፈጸመው የሰርግ ጉዳይ ጥልቅ መልእክቶችን የተሸከመ መኾኑ በብዙ የሚብራራ ነው። ታሪኩን በጥልቀት ለመረዳት ግን ወደ ታሪኩ ጥልቀት ውስጥ የምንገባበትን በር ማግኘት አለብን። የዮሐንስን ወንጌል ምሥጢራዊነት ወደ መረዳት ከፍታ እስካልወጣን ድረስ በወንጌሉ ውስጥ የተፈጸሙትን አስደናቂ ክስተቶች በአግባቡ መረዳት አንችልም። ማክሲመስ ተናዛዚው መጽሐፍ ቅዱስን በጥቅሉ በቤተ ክርስቲያን ይመስልና የዮሐንስን ወንጌል ደግሞ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ያለችውን ቅድስተ ቅዱሳን ትመስላለች ይላል። ይህ የሚያመለክተው ወንጌሉ የተሸከመውን ጥልቅ ምሥጢር ነው። እንዲያውም ቀለሜንጦስ ዘእስክንድርያ ሦስቱን ወንጌላት በሥጋ የዮሐንስን ወንጌል ደግሞ በመንፈስ ይመስላል። የሌሎቹ ወንጌላት እስትንፋሳቸው የዮሐንስ ወንጌል ነውና!!

@@ከዚህ ሁሉ በላይ ደግሞ የዮሐንስን ወንጌል ለመረዳት ሊቁ ኦሪገን እንዳለው ወደ ጌታ ደረት ጋር ጠጋ ብሎ እንደ ዮሐንስ ከጌታ እመቤታችንን መቀበልን ይጠይቃል። ይህ ኹሉ የሚያመለክተው በወንጌሉ ላይ የተጻፉ ክስተቶችን በችኩልነትና በለብ ለብ ስሜት አልፈን እንዳንሄድና በጥልቀት እንድንመረምር ነው። ሰርግ የተፈጸመባት የገሊላዋ ቃና ንጽሕት ቅድስት ድንግል ማርያምን በመያዟ ከሚመጣባት ጉድለት ስትድን እንመለከታለን። ከክርስቶስ ጋር ለምናደርገው ግንኙነት የእመቤታችን ልመና እጅግ አስፈላጊ ነው። እርሷ ቀድማን ጉድለታችንን ባታሰማልን ኖሮ መሽራው ክርስቶስ እንዴት ይቀበለን ነበር!!

@@እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከቤተ አይሁድ ወገን ስለ ኾነች የአይሁድን ጉድለት በእጅጉ ታውቀዋለች፤ ስለዚህ የሚጠቅማቸውን ወይን ይሰጣቸው ዘንድ ትለምናለች። በመጽሐፍ እንዲህ ተብሏል “እናንተ ሰካራሞች ንቁ ለመስከርም ወይን የምትጠጡ እናንተ ሁላችሁ! ተድላና ደስታ ከአፋችሁ ጠፍተዋልና አልቅሱ፤ እዘኑም።" ኢዩ 1፥5። በመኾኑም አይሁድ የድኅነትን ደስታ በማጣት በኀዘን ውስጥ ናቸው፤ ይህ ነውና የወይን ማጣት!! ወይን እኮ የላቸውም የድኅነት ደስታ ከደጃቸው ጠፍታለችና ስጣቸው ማለቷ ነበር። በተራው ምድራዊ ወይን ሰክረው የድኅነትን ወይን በማጣት ጨለማ ውስጥ ገብተው ነበርና ጉድለታቸውን የምታውቅ ፈጣኗ እናት ለመነችላቸው።

@@ወይን እኮ የላቸውም ርቱዕ እምነት የላቸውም። አኹንም በኦሪታቸው ውስጥ የምትታየውን አንተን ወደ ማወቅ አልመጡምና አይኖቻቸውን ከፍተህ ብርሃነ ወንጌልህን ግለጥላቸው። በጨለማ ውስጥ ያለን ነገር ለማየት የግድ ብርሃን እንዲያስፈልግ በእምነት ጨለማ ውስጥ ያሉትን ወይን ርቱዕ እምነትን ሰጥተህ አድናቸው ማለቷ ነው። ያለ እምነት እግዚአብሔርን ደስ ማሰኘት አይቻልም ብሎ ቅዱስ ጳውሎስ እንደ ተናገረው በሐዲስ ኪዳኗ ትክክለኛዋ እምነት በኩል ከእግዚአብሔር ጋር እስካልተገናኘን ድረስ በእርግጥም ወይን እኮ የለንም!!

##እመቤታችን ወይን እኮ የላቸውም ማለቷ ሰዎች ከፈሪሓ እግዚአብሔር በመራቃቸው ምክንያት የደረሱበትን መልከ ጥፉነት ለማመልከትና ከዚያ እንድንፈወስ ለማስደረግ ነው። መዝ 127 “ብፁዐን ኩሎሙ እለ ይፈርሕዎ ለእግዚአብሔር ወለ እለ የሐውሩ በፍናዊሁ። ፍሬ ጻማከ ተሴሰይ፣ ብፁዕ አንተ ወሠናይ ለከ፤ ብእሲትከ ከመ ወይን ሥሙር ውስተ ጽርዓ ቤትከ - እግዚአብሔርን የሚፈሩ ኹሉ የተመሰገኑ ናቸው፣ የድካምህን ዋጋ ትበላለህ፤ ምስጉን ነህ መልካምም ይኾንልሀል፤ ምስትህም በቤትህ ውስጥ እንደ ወይን የተወደደች ናት።" በማለት በብዙ አንቀጽ ጀምሮ በአንድ አንቀጽ ወደ ማውራት ይመጣል። ይህ የሚያመለክተው የክርስቶስንና የእርሱ የኾነችውን ቤተ ክርስቲያን ግንኙነት ነው። በቤትህ እንደ ወይን የተወደደች ናት በማለት የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ውበት ያነሣል። ስለዚህ በፈሪሓ እግዚአብሔር ውስጥ የሚኖሩ የቤተ ክርስቲያን አካሎች የምግባር ውበታቸውን ሳያጡት እንደሚኖሩ፤ ወይን እኮ የላቸውም የተባሉት በዚህ ዓለም ፍልስፍናና ፍቅር የነጎዱትን ነው። የጠፉትን ወደ በረቱ ለመሰብሰብ የተደረገ የፍቅር ጥሪ ነው!!

##ወይን እኮ የላቸውም። ፍቅረ ቢጽ ወፍቅረ እግዚአብሔር የላቸውም። የራሳቸውን ስሜት በመውደድ የሠለጠኑ ናቸውና ወይን ፍቅር የላቸውም!! ወይን ጣዕሟ እንደሚያረካ ነፍሳቸው የምትረካባቸው ቃለ እግዚአብሔር የላቸውም!! ቃልህ ለእግሬ መብራት ለመንገዴ ብርሃን ነው ተብሏል እነርሱ ግን ይህ በአንተ ቃል የመመራት ሐሳብ የላቸውምና በቃልህ የመመራት ኃይልን ሙላባቸው!! እንግዳ ክፉ ፈቃድ ተነሥቶባቸዋልና ይህን ድል የሚያደርጉበትን ወይን ትዕግሥትን ስጣቸው። መናፍቃን ለሚያቀርቡባቸው ጥያቄዎች መልስ ሰጥተው ሰውነታቸውን በእውነት መሠረት ላይ ይገነቡት ዘንድ ወይን ማስተዋል የላቸውምና ማስተዋሉን አድላቸው!!

###ወይን ሕገ ወንጌል ናት። በሕገ ወንጌል ወይን ውስጥ ገብተው ይኖሩ ዘንድ ወይን የወንጌል ምሥጢራትን የሚረዱበት ሀብተ ትርጓሜ የላቸውም። በወንጌል ውስጥ የተዘገበው ሰላም ቀድሞ ባለበሳቸው ጥላቻ ምክንያት አልተገኘላቸውምና “ወይን እኮ የላቸውም" ። የሕይወት ወይን አንተን ራስህን በማጣት ሕማም ውስጥ ገብተው ቆስለዋልና አምላክነትህን ገልጠህ አሳያቸው። በሕይወት ውጣ ወረድ ውስጥ የሚገጥማቸውን መከራ በጽናት ይቀበሉ ዘንድ ወይን እኮ የላቸውም። በእርግጥ የእመቤታችን ድምጿ በልጇ ዘንድ ይሰማል። የእኛ ጉድለትም ስለ እርሷ ሲባል ይሟላል። ብቻ እናችን ቅድስት ኾይ ከመዝሙር ይልቅ ዘፈን ደስ የሚያሰኘንን እኛን ወይን እኮ የላቸውም በይልን!! ጌታ ሆይ ወይን ደምህን ጠጥተን ምሬተ ኃጢአታችንን ታስወግድ ዘንድ ስለ እናትህ ብለህ ወይንህን ስጠን!! አሜን።

ከዲያቆን ዮሐንስ ጌታቸው ገጽ

🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
@wiseholyfathers
አስተያየት ካላቹ በ @Wisecomment_bot ይላኩል


​​“ስንጠመቅ በጲላጦስ ዘመን ከተሰቀለው ከክርስቶስ፣ በነብያት አንደበት ስለ ክርስቶስ ከተናገረው ከመንፈስ ቅዱስ፣ በዮርዳኖስ የምወደው የምወልደው ልጄ እርሱ ነው ካለው ከአብ ዳግመኛ እንወለዳለን”

ሰማዕቱ ቅዱስ ዮስጢኖስ

🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
@wiseholyfathers
አስተያየት ካላቹ በ @Wisecomment_bot ይላኩል


​​ወነአምን በአሐቲ ጥምቀት ለሥርየተ ኃጢያት"✞︎
‘’ኃጥያትን በምታስተሠርይ በአንዲት ጥምቀት እናምናለን ‘’
እንኳን አደረሰን!


​​አንድን አባት ሰዎች መጡና "ዘወትር ጸሎት በማድረግህ በሕይወትህ ላይ የጨመረልህን ነገር ንገረን?" አሉት:: እርሱ ግን "ጸሎት በማድረጌ ከጨመርሁት ይልቅ የቀነስሁት ይበዛልና እርሱን ልንገራችሁ:: ጸሎት በማድረጌ ከሕይወቴ ውስጥ ጭንቀት ፍርሃት ተስፋ መቁረጥና ቁጡነትን ቀንሻለሁ አላቸው::

🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
@wiseholyfathers
አስተያየት ካላቹ በ @Wisecomment_bot ይላኩል


​​​ተ ዓ ም ር እ ና ታ ሪ ክ
አ ን ድ ላ ይ ሲ ጋ ገ ር
እ የ ሞ ቱ መ ብ ዛ ት
ይ ቻ ላ ል በ ዚ ህ ሀ ገ ር


​​♱ ተወልደ ኢየሱስ በቤተልሄም ዘይሁዳ፣ አዋልደ ጢሮስ አሜሃ ይሰግዳ፡፡
♱ ኢየሱስ በቤተልሄም ይሁዳ ተወለደ፣ የጢሮስ ልጆች እጅ መንሻ ያቀርባሉ፡፡
⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️

የጌታችን ይቅርታ እና ቸርነት የእመቤታችን ፍቅር ከኛ ጋር ይሁን!
መልካም በዓል::

🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
@wiseholyfathers
አስተያየት ካላቹ በ @Wisecomment_bot ይላኩል


​​ከ ማትዮስ ወንጌል የተወሰደ 🕊🕊🕊

25:33 በጎችን በቀኙ ፍየሎችንም በግራው ያቆማቸዋል።
25:34 ንጉሡም በቀኙ ያሉትን እንዲህ ይላቸዋል። እናንተ የአባቴ ቡሩካን፥ ኑ፤ ዓለም ከተፈጠረበት ጊዜ ጀምሮ የተዘጋጀላችሁን መንግሥት ውረሱ።
25:35 ተርቤ አብልታችሁኛልና፥ ተጠምቼ አጠጥታችሁኛልና፥ እንግዳ ሆኜ ተቀብላችሁኛልና፥ ታርዤ አልብሳችሁኛልና፥
25:36 ታምሜ ጠይቃችሁኛልና፥ ታስሬ ወደ እኔ መጥታችኋልና።

25:37 ጻድቃንም መልሰው ይሉታል። ጌታ ሆይ፥ ተርበህ አይተን መቼ አበላንህስ? ወይስ ተጠምተህ አይተን መቼ አጠጣንህ?
25:38 እንግዳ ሆነህስ አይተን መቼ ተቀበልንህ? ወይስ ታርዘህ አይተን መቼ አለበስንህ?

25:39 ወይስ ታመህ ወይስ ታስረህ አይተን መቼ ወደ አንተ መጣን?
25:40 ንጉሡም መልሶ። እውነት እላችኋለሁ፥ ከሁሉ ከሚያንሱ ከእነዚህ ወንድሞቼ ለአንዱ እንኳ ስላደረጋችሁት ለእኔ አደረጋችሁት ይላቸዋል።
25:41 በዚያን ጊዜ በግራው ያሉትን ደግሞ ይላቸዋል። እናንተ ርጉማን፥ ለሰይጣንና ለመላእክቱ ወደ ተዘጋጀ ወደ ዘላለም እሳት ከእኔ ሂዱ።

25:42 ተርቤ አላበላችሁኝምና፥ ተጠምቼ አላጠጣችሁኝምና፥ እንግዳ ሆኜ አልተቀበላችሁኝምና፥
25:43 ታርዤ አላለበሳችሁኝምና፥ ታምሜ ታስሬም አልጠየቃችሁኝምና።
25:44 እነርሱ ደግሞ ይመልሱና። ጌታ ሆይ፥ ተርበህ ወይስ ተጠምተህ ወይስ እንግዳ ሆነህ ወይስ ታርዘህ ወይስ ታመህ ወይስ ታስረህ መቼ አይተን አላገለገልንህም? ይሉታል።

25:45 ያን ጊዜ። እውነት እላችኋለሁ፥ ከሁሉ ከሚያንሱ ከእነዚህ ለአንዱ ስላላደረጋችሁት ለእኔ ደግሞ አላደረጋችሁትም ብሎ ይመልስላቸዋል።

25:46 እነዚያም ወደ ዘላለም ቅጣት፥ ጻድቃን ግን ወደ ዘላለም ሕይወት ይሄዳሉ።

🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
@wiseholyfathers
አስተያየት ካላቹ በ @Wisecomment_bot ይላኩል


​​​ትልቅ ስቃይ ንስሃ ሳይገቡ መሞት ነው።
ትልቅ ስቃይ የገነት ጣእሟን አለመቅመስ ነው።
ትልቅ ስቃይ የሞት ሞት የዘላለም ሞት መሞት ነው።
ኦ አምላኬ ሆይ ከዛ ከሚነደው እሳት አንተው አድነን

ንስሃ እንግባ ሁል ጊዜ መንገደኞች ነን
መቼህና እንዴት የምንሄድበትን ሰአትና ጊዜ የማናውቅ ጌታሆይ እርዳን ይች ምድር ከንቱ ናት

የሰማይ ቤታችን እንዳይቆሽሽ ለህሊናችን ስንል መልካም እናድርግ ዛሬ የሰራነው መልካም ስራ ነገ ደመወዝ ሆኖ ይከፈለናልና።

ስንቶቻችን ነን ለጊዜው ብርሃን መስሎን ለጨለማ ተታለን ከእግዚአብሔር ቤት የራቅነው?

ለዚህ ለማያልፈው ነገር ብለን ሂሊናችንን ነፍሳችን እናቆሽሻለን ቅጣት አለ በሰማይ የማያልፈውን እግዚአብሔር ተስፋ እናድርግ።

ሁላችንም የምናስበው በምድር ላለው ሂወታችን ነው በዚች ምድር የምንኖረው ለአንድና ለአንድ ጊዜ ብቻ ነው ሀገራችን ከሰማይ ነው።

እግዚአብሔር ለንስሃ ሞት ያብቃን እንደወጡ ከመቅረት ይጠብቀን
እማምላክ ቅድስት ሆይ ልጅሽ ለፍርድ ሲመጣ እንዳታሳፍሪን በወለድሽው ልጅሽ እንማፀንሻለን አዛኝቱ ረህረተ ልቦና ነፍሴን አደራ እመቤቴ።

በጨለማ ሳለን ብርሃንን ይዘሽ ወደ አለም መተሻልና ቅድስት ሆይ ልጅሽ ይቅርታውን ያደርግልን ዘንድ ለምኝልን
አቤቱ አምላኬ ሆይ ከማያቀላፋው ትልና ከማይጠፋ እሳት አንተ ጠብቀን ዘንድ ቅዱስ ፍቃድህ ይሁንልን አሜን።

ወስበሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክብር ይቆይልን ለዘላለሙ አሜን

🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
@wiseholyfathers
አስተያየት ካላቹ በ @Wisecomment_bot ይላኩልን


​​የመላዕክት ፡ አለቃ ፡ ገብርኤል ፡ ሆይ፤
ሰላም ፡ ላንተ ፡ ይሁን። የጥንቱን ፡ የመዳን ፡ ተስፋ ፡ በመስበክ ፡ አዲስ ፡ የምሥራች ፡ ዜና ፡ ለመናገር ፡ በክብር ፡ ወደ ፡ ድንግል ፡ ማርያም ፡ ተላክህ ፡ ገብርኤል ፡ ሆይ ፡ ሰላም ፡ እልሃለሁ።
፳፱. የኤልሳቤጥ ፡ ልጅ ፡ ዮሐንስ ፡ ከተፀነሰ ፡ በኋላ ፡ ለዳዊት ፡ ልጅ ፡ ምስራች ፡ ትነግር ፡ ዘንድ ፡ ወደ ፡ ገሊላ ፡ ምድር ፡ የተላክህ ፡ ገብርኤል ፡ ሆይ ፡ ሰላም ፡ እልሃለሁ።
፴. ገብርኤል ፡ ሆይ ፤ ሰላም ፡ ላንተ ፡ ይሁን ፡ ድንግል ፡ ማርያምን ፡ ቃልህ ፡ ሰላም ፡ ላንቺ ፡ ይሁን ፡ ባላት ፡ ጊዜ ፡ ከሥጋዋ ፡ ሥጋ ፡ ከነፍሷ ፡ ነፍስ ፡ ነሥቶ ፡ ያን ፡ ጊዜ ፡ መለኮት ፡ ከሷ ፡ ሰው ፡ ሆነ።
፴፩. ገብርኤል ፡ ሆይ ፡ ፤ ሰላም ፡ ላንተ ፡ ይሁንና ፡ ድንግል ፡ ማርያምን ፡ ተፈሥሒ ፡ ደስ ፡ ይበልሽ ፡ ባልካት ፡ ጊዜ ፡ መንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ ሥጋዋን ፡ አነጻ ፡ የልዑል ፡ ኃይልም ፡ ጋረዳት ። ድንግል ፡ ማርያምና ፡ ሕፃኑ ፡ ልጅዋ ፡ ኢየሱስ ፡ ክርስቶስ ፡ ክርስቶስ ፡ ካሉበት ፡ ምድረ ፡ ይሁዳ ፡ እስኪደርሱ ፡ ድረስ ፡ ሰብአ ፡ ሰገልን ፡ በኮከብ ፡ ምልክት ፡ የመራኻቸው ፡ ገብርኤል ፡ ሆይ ፤ ሰላም ፡ እልሃሁ።
፳፫. ገብርኤል ፡ ሆይ ፤ ለድንግል ፡ ደስታን ፡ በተመላ ፡ ቃል ፡ ሰላም ፡ ባልካት ፡ ጊዜ ፡ መለኮት ፡ ከሥጋዋ ፡ ሥጋ ፡ ከነፍሷ ፡ ነፍስ ፡ ነሥቶ ፡ ሰው ፡ ሆነ። ስለዚህም ፡ ምሐረትንና ፡ ፍርድን ፡ ታሰጠኛለህ ፡ በማለት ፡ እየተቀኘሁና ፡ ንጹሕ ፡ ዝማሬንም ፡ እየዘመርኩ ፡ ሰላም ፡ እልህ ፡ ዘንድ ፡ አቤቱ ፡ ተገለጽልኝ።
፴፬. በነደ ፡ እሳት ፡ ለተፈጠረክ ፡ ገብርኤል ፡ ሆይ፤ ሰላም ፡ እልሃለሁ። የብርሃን ፡ ራስ ፡ ወርቅ ፡ የተቀዳጀህ ፡ ገብርኤል ፡ ሆይ፤ ሰላም ፡ እልሃለሁ።
፴፭. የአሸናፊና ፡ የኃይል ፡ መልአክ ፡ ገብርኤል ፡ ሆይ፤ ሰላም ፡ እልሃለሁ። ከፍጹም ፡ ጥፋት ፡ እድን ፡ ዘንድ ፡ ክንፍህን ፡ ጋርድልኝ።
፴፮. ወደ ፡ ድንግል ፡ የተላክህ ፡ ገብርኤል ፡ ሆይ ፡ ሰላም ፡ ላንተ ፡ ይሁን። የደስታ ፡ ምሥራች ፡ ተናጋሪ ፡ ገብርኤል ፡ ሆይ፤ ሰላም ፡ ላንተ ፡ ሁን። ነበልባላዊ ፡ ዖፈ ፡ ሰማይ ፡ ሆይ ፡ ሰላም ፡ ላንተ ፡ ይሁን ። ደስታን ፡ አብሣሪ ፡ ሆይ ፡ ሰላም ፡ ላንተ ፡ ሁን። የአካላዊ ፡ ቃልን ፡ የመጸነስ ፡ ብሥራት ፡ በማኅፀነ ፡ ማርያም ፡ ላሳደርክ ፡ ሰላም ፡ ላንተ ፡ ይሁን።
፴፯. በመልአከ ፡ ሞት ፡ ከመውደቅ ፡ የምትታደግ ፡ ገብርኤል ፡ ሆይ ፡ ሰላም ፡ ላንተ ፡ ይሁን። አማላጅነትህን ፡ በመታመን ፡ ተስፋ ፡ እናደርጋለንና ፡ በመዓልትም ፡ በሌሊትም ፡ አንተ ፡ ጠብቀን ፡ አሜን።

መልክአ ገብርኤል።

🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
@wiseholyfathers
አስተያየት ካላቹ በ @Wisecomment_bot ይላኩልን


​​አንድ ሰው በእግዚአብሔር ፊት ቆመና፡- «ጌታ ሆይ፡- ተመልከት እጆቼ ንጹሐን ናቸው፡፡ ደም አላፈሰሱም፣ የሰው ገንዘብ አልቀሙም» አለ፡፡ እግዚአብሔርም ሲመልስለት፡- «ልጄ ሆይ፣- አዎ እጆችህ ንጹሐን ናቸው፣ ግን ባዶዎች ናቸው» አለው ይባላል፡፡ ንጹሕ እጅ ግን ባዶ እጅ፣ ያልገደለ እጅ ግን ያላዳነ እጅ፣ ያልሰረቀ እጅ ግን ያልመጸወተ እጅ በእግዚአብሔር ፊት ሞገስ የለውም፡፡ ፖሊስ ንጹሕ እጅን፣ እግዚአብሔር ሙሉ እጅን ይወዳል፡፡ እውነተኛው መልካምነት ክፉ አለማድረግ ብቻ ሳይሆን መልካም ማድረግም ነው፡፡ የሚጎዳንን መተው ብቻ ሳይሆን ስለ ሌሎች ጥቅም መድከምም ነው፡፡ ሌላውን ያለ መንካት ግብረ ገባዊነት የተሟላ የሞራል ኑሮ አይደለም፡፡ ሌላውን መዳሰስም ይገባል፡፡

🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
@wiseholyfathers
አስተያየት ካላቹ በ @Wisecomment_bot ይላኩልን


​​"አንተ ውስጥ ካለው ኃጢአት ፤ እግዚአብሔር ጋር ያለው ፍቅርና ምህረት እጅግ ብዙ ነውና ኃጢአትህን ተናዘዘው!"

ቅዱስ አርሳንዮስ

🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
@wiseholyfathers
አስተያየት ካላቹ በ @Wisecomment_bot ይላኩልን


​​( በአጠቃላይ ምድራዊ ነው ስንል ሰማያዊ፤ ሰማያዊ ነው ስንል ምድራዊ (ብእሲ ሰማያዊ ወመልአክ ምድራዊ) ሁኖ እናገኘዋለን፡፡
ዜማውን በግዕዝ ዕዝል አራራይ የዜማ ስልት የደረሰ፤
በዓለም ደረጃ የዜማ ምልክቶች ባልታወቁበት ጊዜ ዜማዎቹን በምልክት የቀመረ፤
የዜማ ሥርዓትን በመንደፍ የዓመቱን ቀለም ያዘጋጀ
ዜማውን በ4ት ዘመናት ከፋፍሎ፤ ዘመናቱን በንዑሳን ዘመናት ከፋፍሎ ለወራቱና ለሰሙኑ ለእለቱ የሚገባውን ቀምሮ የደረሰ፤
እንኳን በእርሱ ዘመን ዛሬ እንኳን ብዙ ነገሮች ተሰባስበዋል በተባለበት ዘመን ሊሠራ አይደለም ሊታሠብ በማይችሉ መልኩ መጽሕፍትን እንደ ንብ እየቀሰመ፤ እንደ ወይን እየጨመቀ፤ እንደ አረቂ እያጣራ፤ እየተረጐመ ላሰበው ድርሠት ያዋለ፤ … ስለ ቅዱሱ ምኑን ተናግረን እንጨርሰዋለን፡፡ …
.. ይኼማ ኢትዮጵያዊ ሊኾን አይችልም ብለው ብዙ የውጭ ሃገራት ወደ ራሳቸው ለመውሰድ የሚዳዳቸው፡፡
የቅዱስ ያሬድ ልደትና የስሙ ትርጓሜ
ꔰ ኢትዮጵያዊው ቅዱስ ያሬድ ሚያዚያ 5 ቀን በ505 ዓ.ም. ከአባቱ ይስሐቅ(አብድዩ) ከእናቱ ክርስቲና (ታውክልያ) በአኵሱም ከተማ ተወለደ፡፡ (አንዳንዶች /መሪጌታ ልሳነ ወርቅ/ ልደቱን 493 ዓ.ም. ነው ይላሉ/፤ እንዲሁም አቶ በላይ ግደይና መሪጌታ ልሳነ ወርቅ አባቱ ኖኅ ነው ይሉና መሪጌታ ይስሐቅ የቀለም አባቱ/መመህሩ/ ነው ይላሉ፡፡
ꔰ የስሙም ትርጓሜም ያሬድ ማለት እንዚራ፣ በገና፣ መሰንቆ ማለት ነው ፡፡ እነዚህ መሣሪያዎች በስልት በስልት ሲመቱ ለሚሰማቸው ደስ እንዲያሰኙ የያሬድም ዜማ በንጉሠ ነገሥቱ ክርስቶስ አደባባይ በቤተ ክርስቲያን ሲሰማ መላእክትን፥ ሰውንና እንስሳትን ደስ ያሰኛልና፡፡
( አንድም ያሬድ ርደት፣ ወሪድ፤ መውረድ ማለት ነው፡፡ ቅዱስ ያሬድ ሰማያዊውን ልዩ ጣዕመ ዜማ ወደ ኢትዮጵያ አውርዷልና፡፡
( አንድም ያሬድ ማለት ንብ ማለት ነው፤ ንብ የማይቀስመው አበባ እንደሌለ ሁሉ ቅዱስ ያሬድም ከመጻሕፍት የማይጠቅሰው የማይቀሰመው የለም፤
( አንድም ያሬድ ማለት ረአዬ ምሥጢር፥ ነጻሬ ኅቡአት ማለት ነው፤ የመላእክት ምሥጢራት የነበሩትን ጸዋትወ ዜማ አምልቶ አስፍቶ ተናግሯልና፣ ነጻሬ ኅቡአት አለ፥ ኅቡእ (ስውር) የሆነ የጻድቃን፣ የሰማዕታት የነቢያት የሐዋርያትን ገድል አምልቶ አስፍቶም ይናገራልና፡፡
-ዐፄ ካሌብ ቤተ እስራኤል፣ ገብረክርስቶስና ገብረ መስቀል የሚባሉ ልጆች ነበሩት፤ ቅዱስ ያሬድ የተነሳው ከእነዚህ ውስጥ በዓፄ ገብረመስቀል ዘመን ነው፡፡
ሌሎች ቅጽል መጠሪያ ስሞቹ፤
ሊቅ (ርእሰ ሊቃውንት )
ዓርከ ሊቃውንት፤
ደራሲ፤
የመጽሐፍ መምህር፤ (ብሉያትንና ሐዲሳትን የሊቃውንትንም መጻሕፍት አስማምቶ የተረጐመ)
ባለቅኔ (የቅኔ ጀማሪ)፤
ጥዑመ ልሳን፤
የሱራፌል አምሳያ፤
የቤተ ክርስቲያን እንዚራ፤
የቤተ ክርስቲያን ብርሃን፤
የቤተክርስቲያን ጌጧና መሠረቷ ሕይወቷና እስትንፋሷ
ካህን (ካህነ ስብሐት)
መዓርዒረ ዜማ፤
ማኅሌታይ፤
መዘምር ዘበድርሳን፤
ልዑለ ስብከት፤
ሰማዕት፤
ባሕታዊ፤
መናኝ
የዜማ አባት፤
በየኢትዮጵያ ብርሃን፡፡ ..
የሚታወቁት ድርሠቶቹ፤
1ኛ) ምዕራፍ (ውዳሴ ማርያም በዜማን፣ መስተጋብዕ፣ አርባዕት፣ አርያም፣ ሠለስት፣ ክስተተ አርያምን) ያጠቃለለ
የውዳሴ ማርያም ዜማው ልብን የሚመስጥ፤
መስተጋብዕ፤ ስብስብ ማለት ሲኾን፡፡ ከዳዊት መዝሙር (ከ180ው የመስተጋብእ ድርሰት 1ድ ድርሰት በስተቀር) ለጸሎትና ለዝማሬ ተስማሚ የኾነው እየተውጣጣ ለመዝሙር ተስማሚ የኾነው የተቀመረ ነው፡፡ መስተጋብዕ ሲጀምር ‹‹ወለቡ ጽራኅየ (ጩኸቴን ልብ አድርግ›› ብሎ ነው፡፡ በዐቢይ ጾም ከሰኞ እስከ ቅዳሜ ጠዋት ጠዋት ይዘመራል፤ የቀድሞ መምህራን በፍልሠታም ይዘምሩት ነበር፤ ዜማው በዋነኛነት በግዕዝና በዕዝል ሲኾን በአራራይ ከሐሙስ ‹‹አንተሰ እግዚኦ ለዓለም›› የሚለውና ከቅማዴ ‹‹መንግሠትከሰ መንግሥት›› የሚለው ይገኙበታል፡፡ በየእለቱ እንዲደርስ (ከእሑድ በስተቀር) አድርጎ የደረሰው ነው፤
አርባዕት፤ አራት አራተኛ ማለት ሲን በዳዊት መዝሙር በአራተኛው መሥመር ውስጥ እየገባ የሚዘመር ነው፤ ‹‹ቃልየ አጽምእ እግዚኦ ወለቡ ጽራኅየ፤ ወአጽምአኒ ቃለ ስእለትየ፤ ንጉሥየኒ ወአምላኪየኒ፡፡ ከፈጸመ በኋላ አርባዕት ይገባል፡፡ አርባዕት ሲጀመር ‹‹ቃልየ፤ ከመ ያፈቅርለ ጐሥዓ፤ ዐቢይ፤ ተሣሃለኒ›› ብሎ ነው (በዳዊት መዝሙር ጀምሮ ቀጥሎ በቅዱስ ያሬድ ድርሠት በኾነው በአርባዕት ያጠናቅቃል፡፡አብዛኛው በግጥም መልክ የተቀመረ ሲኾን አልፎ አልፎም በስድ ንባብ መልክ ይገኛል፡፡ ግእዝ ዕዝልና አራራይ ዜማ አለው፡፡
አርያም፤ አርያም ልዑል፥ ከፍተኛ ማለት ሲኾን፤ ቅዱስ ያሬድ ከአርያም ሰምቶ ‹‹ቀዳሚ ዜማ፤ አንድም ቀዳሚሃ ለጽዮን ሰማየ ሣረረ›› ስላመጣው ነው፡፡ ሃሌ ሉያ ለአብ ሃሌ ሉያ ለወልድ ሃሌ ሉያ ለመንፈስ ቅዱስ ብሎ የግጥም መል ባለው አእያም በተባለው ይጀምራል፡፡ በግጥም መልክና በስድ ንባብ ሲገኝ የግጠም አገጣጠሙ ከፍ ያለ የግጥም አገጣጠምን የተከተለነው፡፡ የሚባልበት ጊዜ በጾም ጊዜ በጾመ ድጓው እየገባ፣ በተለይ ደግሞ በክብረ በዓል ክሥተተ አርያም ሲደርስ ይዘመራል፡፡
ሠለስት፤ ስምዐኒ ብሎ የሚጀምር ባለ ብዙ ሃሌታ ያለው፤ በዳዊት መዝሙር በሦስተኛው መሥመር እየገባ የሚዘመር፤ አንድም 3 መዝሙሮች ብቻ የሚዘመሩለት ብዙውን ጊዜ በግጥም የሚቀርብ ሲኾን፤ ይኽ ዜማ የሚደርሰው በክብረ በዓላት ዋይዜማ፤ በስብሐተ ነግህ፣ በአርያም፣ በጾመ ድጓ ውሎ፣ በአርያም፣ በሰንበት፣ በፍትሐት ጊዜ ነው፡፡
ክስተተ አርያም፤ የሰማይ መከፈት ማለት ሲኾን በታላላቅ በዓል ቀን እንዲሁም ታላላቅ? ሰዎች ሲሞቱ የሚዘመር ነው፤ ክስተትን ቅዱስ ያሬድ ያዘጋጀው ከዳዊት መዝሙራት፥ ከጸሎተ ነቢያትና ከራሱም ጭምር ኀይለ ቃል ያላቸውን ባለሁለት መስመሮች ሐረግ በመውሰድ ሲኾን ዜማው እጅጉን ነፍስና ሥጋን፥ ልብንና ኅሊናን የሚመስጥ ነው፡፡
2ኛ) ጾመ ድጓ፤ በዐቢይ ጾም የሚባል ነው፡፡
3ኛ) ድጓ፤ በ4ት ክፍላተ ዘመናት የተቀመረ ነው፡፡
4ኛ) ዝማሬ፤ ቅዱስ ቊርባን ድርገት ሲወርድ ለቅዱስ ቊርባን ክብር የሚዘመር ነው፡፡
5ኛ) መዋሥዕት፤ ሰው ሥጋው ከነፍ ስትለይ ፍትሐት የሚደረግበት ጸሎት ነው፡፡
6ኛ) የ14ቱን ቅዳሴያት ዜማ
7ኛ) አንቀጸ ብርሃንን፤ ድርሠቱ ነው፡፡
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
@wiseholyfathers
አስተያየት ካላቹ በ @Wisecomment_bot ይላኩልን




​​The boy who fed the baby Christ

When he was 4-5 years old, Onufrij saw in the monastery an icon on which the Most Holy Mother is holding Christ. However, when he noticed that no one gives Christ bread (nafora) in the church, and everyone gets it, he felt sorry for himself...
When the crowd dispersed, he went to a nearby inn and asked the innkeeper for bread. He gives him a piece of bread. Onufrij went to the temple and in front of the icon said to little Jesus - I brought you bread, I see that no one is giving it to you! At that moment, the hand of Christ came to life from the icon and took the bread. This was repeated in the following days. However, the innkeeper wondered where the boy Onuphrije was carrying the bread, that he might not be feeding some hidden animal. So suspicious and curious he followed him, when he had something to see. Onuphrius usually went to the monastery temple in front of the icon and gave bread to Jesus, and Jesus stretched out his hand and took it, then the bread disappeared in the icon.

The innkeeper was so horrified by this miracle that he almost became speechless, ran to the abbot of the monastery and told him everything.
The abbot advises him that the next day he should not give bread to the boy Onufri, but to tell him - To whom you brought bread until now, let him give it to you.

Onufrij went to the temple in front of the icon and said to the little Christ - They don't give me bread anymore. They say I'm asking for you to give me.

All this was watched by the abbot, monks and the innkeeper stealthily from a hidden part of the temple. O wonder, at that moment Christ stretched out his hand as if alive from the icon and gave Onuphrio a large loaf of bread. He smelled the bread with heavenly peace so much that the abbot, monks and innkeeper fell on the floor of the church in tears. The boy Onuphrije saw them and shared bread with them. They had never eaten anything better in their life and they couldn't eat it all.
When this boy grew up, he became a monk and lived in the desert. Every Sunday, the Lord Jesus Christ sent him angels to give him communion from Heaven and to bring him this bread. For sixty-one years he lived in the desert of Onuphrije and became one of the Great Saints.


🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
@wiseholyfathers
አስተያየት ካላቹ በ @rafato_el ይላኩልን


​​እመቤቴ ማርያም ሆይ፤

በራስ ፀጉሬ ቁጥር አመሰግንሻለሁ። በአጥንቶቼም ቁጥር አመሰግንሻለሁ።

ድንግል ሆይ፤

በሚታየውና በሚዳሰሰው ሁሉ ቁጥር አመሰግንሻለሁ።

ንግሥት ሆይ፤

በማይታየውና በማይዳሰሰው ሁሉ ቁጥር ሰላም እያልሁ። የድንግልናሽን ምስጋና አፌ ሁል ጊዜ ይናገራል። እስከ ዘላለሙ አሜን።

🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
@wiseholyfathers
አስተያየት ካላቹ በ @rafato_el ይላኩልን

20 last posts shown.