የ ኦርቶዶክስ ቅዱሳን አባቶች ትምህታዊ ንግግሮች Wise sayings of holy fathers of orthodox


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: Religion


This channel's aim is to help us learn from the spritual life of holy fathers .

ከቅዱሳን አባቶች ትምህታዊ ንግግሮች እንማር ዘንድ የ ተዘጋጀ channel ነው።

ከቅዱሳን አባቶች ትምህታዊ ንግግሮች group https://t.me/joinchat/FXPZVEUP8KLHay0v0d0LuQ
አስተያየት ካላቹ በ @Wiseholyfathers_comment ይላኩልን።

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
Religion
Statistics
Posts filter


​​እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ጥምቀት አደረሰን

ክርስቶስን መሠረት ያደረገ እምነት ሁሉ “ሰው ዳግመኛ ካልተወለደ በቀር የእግዚአብሔርን መንግሥት ሊያይ አይችልም” ዮሐ. ፫፥፫ የሚለው የጌታ ትምህርት መመሪያው ሊሆን ግድ ነው። ጌታ እንዳስተማረውም ያለጥምቀት ድኅነት የለም።

ጥምቀት በሚታየው አገልግሎት በውኃ ውስጥ ገብቶ መነከር፣ መዘፈቅ፣ ውኃ ውስጥ ገብቶ መውጣት ማለት ሲሆን በሚታየው አገልግሎት የሚገኘው የማይታይ ጸጋ ግን ብዙ ነው።
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
@wiseholyfathers
አስተያየት ካላቹ በ @Wisecomment_bot ይላኩልን

ሙሉውን ለማንበብ ይህን ይጫኑ👇


​​♱ ተወልደ ኢየሱስ በቤተልሄም ዘይሁዳ፣ አዋልደ ጢሮስ አሜሃ ይሰግዳ፡፡
♱ ኢየሱስ በቤተልሄም ይሁዳ ተወለደ፣ የጢሮስ ልጆች እጅ መንሻ ያቀርባሉ፡፡
⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️

የጌታችን ይቅርታ እና ቸርነት የእመቤታችን ፍቅር ከኛ ጋር ይሁን!
መልካም በዓል::

🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
@wiseholyfathers
አስተያየት ካላቹ በ @Wisecomment_bot ይላኩል


​አበው ስለ እመቤታችን እንዲህ አሉ

"አምላክ ከንጉሥ ሔሮድስ ሴት ልጅ ቢወለድ ኖሮ አልጋ ወራሽ በሆነና ባልተሰደደ ነበር። እርሱ ግን የድሆች ልጅ የሆነችውን ድንግል መረጠ" አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ

"ታላቁ ተራራ ሆይ ታናሽዋ ብላቴና የተሸከመችህ ራስህን በሚቻላት መጠን አድርገህላት ነው ፣ ታላቁ እሳት ሆይ ታናሽዋ ብላቴና ተሸክማህ ያልተቃጠለችው ኃይልን ትችል ዘንድ አጽንተሃት ነው " ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ

"ይህ ዓለም የእግዚአብሔርን ልጅ በቀጥታ ከእግዚአብሔር አብ እጅ ለመቀበል የተገባ ሆኖ ስላልተገኘ ፣ ዓለም ከእርስዋ ይቀበል ዘንድ አንድያ ልጁን ለድንግል ማርያም እናት ትሆነው ዘንድ ሠጣት" ቅዱስ አውግስጢኖስ

"ሔሮድስ የማይያዘውን ይይዝ ዘንድ ተነሣ ፣ ዓውሎ ነፋስንም በቤቱ አስገብቶ ሊዘጋ ታገለ" አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ

"ጌታ ሆይ እናትህን ማን ብለን እንጥራት? እናት ብቻ እንዳንላት ድንግል ሆና አገኘናት ፣ ድንግል እንዳንላት ልጅ ታቅፋ አየናት። ጌታ ሆይ እናትህን ለመጥራት እንዲህ የሚያስቸግር ከሆነ አንተን ከቶ ምን ብለን እንጠራሃለን??"

ቅዱስ ኤፍሬም

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ


​"በፈጣሪ ፊት ከአዕላፍ መላዕክት መቆሚያ ይልቅ
ከፍታ ለአላት መቆሚያኽ ሰላም እላለሁ።
ተፈጥሮህም ከነፋስ የኾነ ቅዱስ ሚካኤል ሆይ
በክፋት ማዕበል እየተንገላቱ የሚጨነቁትንና
በበረኃ የሚሠቃዩትን በፍጹም ረድኤትህ ደርሰህ
የምታድናቸው አንተ ነህ።"

መልካም በዓል!


​​☘️☘️"ለመዋረዴም ከፍታ ለህመሜም ጤና ናት" ☘️☘️

🌹አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ


​​"በመስቀል ክርስቶስ ተሰቀለ ዲያብሎስ በመስቀሉ ተገደለ። ክርሰቶስ በመስቀል እጆቹን ዘረጋ በዚህን ጊዜ ለዓለም ድሕነት ተፈፀመ። ክርሰቶስ በመስቀል ላይ ተቸነከረ ነፍሳት ከእስራት ወጡ። ክርሰቶስ በመስቀል ላይ ዋለ የሰው ልጆች  ከባርነት ቀንበር እና ከሞት ነፃ ወጡ።"
        ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
ሞታችንን በሞቱ ለሻረበት ለሰላማችን መገኛ፤ ኃይላችን፣ መድኃኒታችን፣ መመኪያችንና መጠጊያችን ለሆነን በዓለ መስቀል እንኳን አደረሰን።
       መልካም በዓል!!!!!!
                      


​​​"በቸርነትህ ዓመታትን ታቀዳጃለህ ምድረ በዳውም ስብን ይጠግባሉ'' መዝ 65÷11
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
እንኳን ከዘመነ ዮሐንስ ወደ ዘመነ ማቴዎስ በሰላም አሸጋገረን!
🌼እንኳን አደረሳችሁ🌼
🌼መልካም አዲስ አመት🌼


🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
@wiseholyfathers
አስተያየት ካላቹ በ @Wisecomment_bot ይላኩልን


​​እንኳን ለሊቀ መላእክት ቅዱስ ሩፋኤል ዓመታዊ መታሰቢያ በዓል በሰላም በጤና አደረሳችሁ!

ጌታችን ሩፋኤልን "የክብርህን ታላቅነት ያውቁ ዘንድ ስምህን ለሐዋርያት ንገራቸው" አለው።
ሩፋኤልም. . .


"እኔ. . . _#ልቡናን_ደስ_የማሰኝ፤ \#የዋህ፤ \#ለኃጥኣን_የምራራ_ነኝ።
አንድ ሰው በእኔ ስም በዚህ ዓለም መከራ ላአገኘው ሰው በጎ ቢያደርግ፣ የሹመቴን መጽሐፍ የሚጽፍ፤ በእኔ ስምም ከድሆቹ አንዱን የሚያስብ ሰው ቢኖር \#ጳጉሜን_ሦስት ቀን በምትሆነው እግዚአብሔር እኔን በሾመባት በመላእክት ሹመት ባከበረባት በመታሰቢያዬ ቀን ፍሬ ግብር ዕጣን ጧፍ የሚሰጥ ቢኖር፣ እኔ ወደ ሰማያዊት ኢየሩሳሌም እስኪገባ ድረስ በብርሃን ሠረገላ አሳርገዋለሁ።

በዚህ ዓለም ፈጽሞ እንደሱ ያለ የማይገኝ ሽታው እጅግ የተወደደ የሽቱ አበባ በእጁ እንዲይዝ አደርጋለሁ።"

*የከበረ መልእክ የሩፋኤል ተአምራቱ ብዙ ነው።

እኛም ሁልጊዜ መታሰቢያውን እናደርግ ዘንድ ይገባናል። እሱ ስለእኛ ወደ እግዚአብሔር ይማልዳልና።
*
☘️
ድርሳነ ሩፋኤል ጳጉሜ☘️

🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
@wiseholyfathers
አስተያየት ካላቹ በ
@Wisecomment\bot ይላኩልን


​​የእመቤታችን በዓለ ዕርገት

እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ያረገችበት ዕለት ነሐሴ ዐሥራ ስድስት ቀን በቤተ ክርስቲያናችን ይከበራል፡፡

ሐዋርያት ከእመቤታችን ድንግል ማርያም ዕረፍት በኋላ ከእነርሱ በመለየቷ ባዘኑበት ወቅት የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተገለጠላቸው፤ እርሷን በሥጋ ያዩ ዘንድም ተስፋ ሰጣቸው፡፡

በዚያን ጊዜ ወንጌላዊ ዮሐንስ እስያ በሚባል አገር እያስተማረ በነበረበት በነሐሴ ወር ዐሥራ ስድስተኛ ቀን ተድላ ደስታ ወደ አለባት ገነት በመንፈስ ቅዱስ ተነጠቀ፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስንም የእመቤታችን ማርያም ሥጋዋ ካለበት ከዕፀ ሕይወት ዘንድ ተቀምጦ አየው፡፡

የንጽሕት እናቱንም ሥጋ ታወጣ ዘንድ ምድርን እንዲጠሩዋት ሰባቱን የመላእክት አለቆች አዘዛቸው፤ እነርሱም ‹‹የንጽሕት እናቱን ሥጋ ታወጪ ዘንድ እግዚአብሔር አዞሻል›› አሏት፡፡ ያን ጊዜም ከዕፀ ሕይወት በታች ካለ መቃብር የእመቤታችን ማርያም ሥጋዋ ወጣ፡፡ ጌታችንም እንዲህ እያለ አረጋጋት፤ ‹‹የተወደድሽ የወለድሽኝ እናቴ ሆይ! ዘላለማዊ ወደ ሆነ መንግሥተ ሰማያት አሳርግሽ ዘንድ ነዪ፡፡›› ከዚያም በገነት ያሉ ዕፅዋት ሁሉም አዘነበሉ፤ መላእክት፣ የመላእክት አለቆች፣ ጻድቃን ሰማዕታትም እየሰገዱላትና ፈጽሞ እያመሰገኗት አሳረጓት፡፡ ቅዱስ ዳዊትም ‹‹ንግሥት እመቤታችን! ወርቀ ዘቦ ለብሳ ደርባ ደራርባ በቀኝህ ትቀመጣለች›› እያለ በበገና አመሰገናት፡፡

በኪሩቤል ሠረገላ ተቀምጣ ከዐረገች በኋላም በልጆችዋና በፈጣሪዋ ቀኝ በታላቅ ክብር ተቀመጠች፡፡ በዚህን ጊዜ ወንጌላዊ ዮሐንስ ከእርሷ በረከትን ተቀብሎ ከሰገደላት በኋላ ተመልሶ ወደ ምድር ወረደ፤ ሐዋርያትንም ተሰብስበው ስለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሥጋ ፈጽሞ ሲያዝኑና ሲተክዙ አገኛቸው፡፡ እርሱም እንዳየ፣ እንደሰማና ሥጋዋንም በታላቅ ክብር በምስጋና እንዳሳረጓት ነገራቸው፡፡

ሐዋርያትም ይህን በሰሙ ጊዜ ዮሐንስ እንዳየና እንደሰማ ባለማየታቸውና ባለመስማታቸው እጅግ አዘኑ፡፡ ከዚያም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተገልጦ ‹‹የፍቅር የአንድነት ልጆች፤ ሰላም ይሁንላችሁ! ስለ እናቴ ማርያም ሥጋ ለምን ታዝናላችሁ፡፡ እነሆ እኔ እርስዋን በሥጋ ላሳያችሁ፤ ልባችሁም ደስ ሊለው ይገባዋል›› ብሏቸው ወደ ሰማይ ዐረገ፡፡

ሐዋርያትም ለዓመት ከቆዩ በኋላ የነሐሴ ወር በሰባት ቀን ዮሐንስ ለሐዋርያቱ እንዲህ አላቸው፤ ‹‹አምላክን የወለደች የእመቤታችንን ሥጋዋን ለማየት የተዘጋጀን አድርጎ ያሳየን ዘንድ ኑ! ይህን ሁለት ሱባዔ በጾም የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን እንለምነው፤ በልጅዋ በወዳጅዋ ቀኝ ተቀምጣ አይተን በእርሷ ደስ እንዲለን፡፡››

ዮሐንስም እንዳላቸው በጾም በጸሎት ሱባዔ ያዙ፤ በነሐሴ ዐሥራ ስድስትም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሁሉንም ሐዋርያት ወደ ሰማይ አወጣቸው፡፡ በታላቅ ክብር በተወደደ ልጇ ቀኝ ተቀምጣ፣ ከሥጋዋ ተዋሕዳ፣ ተነሥታ እመቤታችን ማርያምን አዩዋት፡፡ እጆቿንም ዘርግታ የከበሩ ሐዋርያትን ባረከቻቸው፤ በልባቸውም እጅግ ደስ አላቸው፡፡

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም በከበረ ሥጋውና ደሙ ላይ ሠራዔ ካህን ሆነ፡፡ እስጢፋኖስም አዘጋጀ፤ ዮሐንስም በመፍራት ቁሙ አለ፡፡ ሁሉም ሐዋርያት በመሰዊያው ዙሪያ ቆሙ፤ በዚያን ጊዜ ከቶ እንደርሱ ሆኖ የማያውቅ ታላቅ ደስታ ሆነ፡፡ ጌታችንም የቅዳሴውን ሥርዓት በፈጸመ ጊዜ ሥጋውንና ደሙን አቀበላቸው፡፡

ከዚያም በኪሩቤልና በሱራፌል ሠረገላ ተቀምጣ በምታርግ ጊዜ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እናቱ እመቤታችን ማርያምን እንዲህ አላት፡፡ ‹‹በዚች ቀን የሆነ የዕርገትሽን መታሰቢያ በዓለም ውስጥ እንዲሰበኩ ልጆችሽ ሐዋርያትን እዘዣቸው፡፡

መታሰቢያሽን የሚያደርገውን ሁሉ ተጠብቆም በዚች ቀን ቅዱስ ቁርባን የሚቀበለውን ኃጢአቱን እደመስስለታለሁ፡፡ የእሳትን ሥቃይ ከቶ አያያትም፤ መታሰቢያሽን ለሚያደርግ ሁሉ፣ በዚች ቀን ለድኆች በስምሽ ለሚመጸውትም ቸርነቴ ትገናኘዋለች፤ ይህም ሥጋሽ ወደ ሰማይ ያረገበት ነው፡፡››

እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም ክብር ይግባውና ጌታችንን እንዲህ አለቸው ‹‹ልጄ ሆይ! እነሆ በዐይኖቻቸውም አዩ፤ በጆሮዎቻቸውም ሰሙ፤ በእጆቻቸው ያዙ፤ ሌሎችም ታላላቅ ድንቆች ሥራዎችን አዩ፡፡›› እመቤታችንም ይህን ስትናገር ጌታችን ሰላምታ ሰጥቷቸው በታላቅ ደስታ ወደ ደብረ ዘይት ተመለሱ፡፡

የክርስቲያን ወገኖች ሆይ! እኛም በፍጹም ደስታ መታሰቢያዋን እናደርግ ዘንድ ይገባናል፡፡ እርሷ ስለ እኛ ወደ ተወደደ ልጅዋ ሁልጊዜ ትማልዳለችና፡፡

እግዚአብሔር አምላካችን በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነት ይምረን ዘንድ ፈቃዱ ይሁንልን! አሜን፡፡

ምንጭ፡-ስንክሳር ዘወርኀ ነሐሴ
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
@wiseholyfathers
አስተያየት ካላቹ በ @Wisecomment_bot ይላኩልን


​​#ቡሄ

ቡሄ ማለት ብራ፣ ብርሃን፣ ደማቅ ማለት ነው፡፡ ጌታችን ብርሃነ መለኮቱን የገለጠበት በዓል የሚዘከርበት እና ለበዓሉም ችቦ ስለሚበራ የብርሃን በዓል በማለት የቡሄ በዓል እንላለን፡፡ ወቅቱ የክረምት ፤ጨለማ አልፎ የብርሃን የሚወጣበት፤ ሰማይ ከጭጋጋማነት ወደ ብሩህነት የሚለወጥበት የመሸጋገሪያ ወቅት ነው፡፡ “ቡሄ ከዋለ የለም ክረምት፤ ዶሮ ከጮኸ የለም ሌሊት” እንዲሉ፡፡ በሌላ በኩልም “ቡኮ/ሊጥ” ተቦክቶ ዳቦ የሚጋገርበት “#ሙልሙል” የሚታደልበት በዓል በመሆኑ ቡሄ ተብሏል፡፡

#ጅራፍ

በደብረ ታቦር በዓል በትውፊታዊ መልኩ የሚታየው ምስጢር፤ በኢየሩሳሌም ስለሚሆነው የጌታችን ምስጢራዊ ሞቱ ነው፡፡ ጅራፍ መገመድ(መጥለፍ) እና ጅራፍ ማጮኽ ሁለት ዓይነት ምስጢር የያዘ ትውፊታዊ ተግባር ነው፡፡

የመጀመሪያው ግርፋቱንና ሞቱን እናስብበታለን፡፡ ሁለተኛው ደግሞ ፤ድምፁን ስንሰማ የባሕርይ አባቱን የአብን ምስክርነት ቃል፤ እንደ ነጎድጓድ ድምፅ ያስታውሰናል፡፡

የጅራፍ ትውፊታዊነት /ውርስ/፣ መጽሐፋዊ ትምህርትና ምስጢር ጠብቆ ለትውልድ እንዲተላለፍ ለማድረግ ጨዋታውን በተራራማ አካባቢ፣ ከመኖሪያ ቤት ርቆና፣ በሜዳ ማድረጉ ጠቃሚ ነው፡፡ ጅራፍን #በርችት መቀየር የሚያመጣውን የምስጢር ተፋልሶ ብቻ መመልከት ከማኅበራዊ ጎጂ ገጽታው በላይ እንድናስወግደው ያስገድደናል፡፡

#ችቦ

ችቦ የጌታችንን ብርሃነ መለኮት መገለጥ የሚያመለክት ነው፡፡ በመሆኑም ችቦ ለኩሰን በዓሉን እናከብራለን፡፡ የዚህ ትውፊታዊ አመጣጥ በብርሃኑ ድምቀት የቀኑን መምሸት ያልተረዱ እረኞች በሜዳ ቀርተዋልና ወላጆች ከመንደር ችቦ ለኩሰው ልጆቻቸውን ፍለጋ ሔደዋልና ታሪኩን እያዘከርን በዓሉት እናከብራለን፡፡

የችቦው መንደድም ሌላ ትርጉም አለው፡፡ አንድ ምእመን ለሌላው ምእመን መካሪ አስተማሪ መሆኑን፣ መከራ እየተቀበለም አርአያ፣ ምሳሌ፣ ብርሃን መሆኑን ያሳያል፡፡ በሃይማኖትም አርአያ ምሳሌ ይሆንላቸዋል፡፡ ከዚህ ጋርም ተያይዘዞ ችቦ በ13 ምሽት ይበራል ፣ብርሃኑ የተገለጠው በዚችው ዕለት ነውና ፡፡

#ሙልሙል

በችቦ ብርሃን ልጆቻቸውን ፍለጋ የወጡ ወላጆች ዳቦ ጋግረው ይዘውላቸው ወጥተዋል፡፡ ስጦታው ቤተሰባዊነትን፣ ፍቅርንና መተሳሰብን መግለጫ ነው፡፡ ወደ ቤታችን “ ቡሄ ” እያሉ ለሚመጡ አዳጊዎችም፤ ዘምረው እንዳበቁ የሚሰጥ “ሙልሙል” ዳቦ አለ፡፡ ሕፃናቱም ሊዘምሩ ሲመጡ ዳቦ መስጠት ልማዳዊ ብቻ አይደለም፡፡

ሕፃናቱ የደቀመዛሙርት ምሳሌ ናቸው፡፡ መዝሙራቸው ደግሞ ሐዋርያት “የምሥራች” ይዘው የመምጣታቸው ምሳሌ ነው፡፡ ሐዋርያት በገቡበት አገር አስተምረው አጥምቀው የጸጋ ልጅነትን አሰጥተው በረከት አድለው እንደሚሔዱም፣ ልጆችም ዘምረው፣ አመስግነው፣ መርቀው “ውለዱ ክበዱ፣ ሀብት አግኙ፣ የመንግሥተ ሰማያት ወራሾች ያድርጋችሁ ….” ይላሉ፡፡

በአጠቃላይ በዓለ ደብረ ታቦር ከእነዚህ ምስክር ካላቸው ትምህርቶቹ፣ ምሥጢር ከሚራቀቅባቸው ትርጓሜያቱና ከትውልድ ትውልድ በቅብብል በተላለፈው ቅዱስ ትውፊት ጋር ሃይማኖታዊ ባሕል ሆኖ ሊቀጥል ይገባዋል፡፡

ይህን ማድረግ የሚቻለው ግን አዳጊዎች ሃይማኖታዊ ትውፊቱን ይዘው እንዲያድጉ ጥቆማ በመስጠት፣ ግጥም በመግጠምና ምሥጢሩን በማብራራት የመጀመሪያዎቹ ባለድርሻዎች ወላጆች ናቸው፡፡

አንዳንድ ጊዜ የሚሰሙ ግጥሞች ስድብ፣ ፌዝና ሥላቅ የተቀላቀለባቸው ይሆናሉ፡፡ ሕፃናቱም ዝማሬውን ሲጀምሩ “ከሰጡን እንነሣ ከነሱን እናርዳ” ብለው ይጀምሩታል፡፡ ከሰጡን እንመርቃለን ካልሰጡን እንራገማለን በማለት፡፡

አሳሳቢው ነገር ደግሞ ሃይማኖታዊ ሥርዓቱን ወደ ገንዘብ ማግኛነት የቀየሩ ሁኔታዎች መታየታቸው ነው፡፡ ዳቦ /ሙልሙል/ ትምህርቱንም፣ ምስጢሩንም፣ ትውፊቱንም በአግባቡ ልንጠቀምበት ይገባል።

ከዚም ጋር ተያይዞ ሰንበት ት/ት ቤታችን ለበረካታ ዓመታት ሲወርድ የመጣውን የዝማሬ ሥርዓት ለአጥብያው ምእምን በየቤቱ በመሄድ የብሄን ዝማሬ ከነሥርዓቱ በመዘመር አገልግሎት ይሰጣል ፤የደብር ታቦርን በዓል በተመለከትም የወረቀት ጽሑፎችን ይበትናል በዝማሬ መኃል ያድላል፡፡

ቤተክርስቲያን የምሥጢር ግምጃ ቤት ናት፤ የምታከናውነውን ሁሉ ከበቂ መረጃ ጋር ነው ተግባራዊ የምታደርገው፡፡ በተለይ ወጣቱ ክፍል ይህንን አውቀን ተረድተን ለቀሪው ትውልድ ማስተላለፋ እንችል ዘንድ ከክፉ ጠላት ከሰይጣን ፈተና፣ በሽታ ከመሳሰሉት ችግሮች ለመዳን ወደ ተራራዋ ወደ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በመሸሽ ከክፉ ነገሮች ሁሉ ማምለጥ ይቻላል፡፡

በቤተ ክርስቲያን ጥላ ሥር የሚጠለሉ ሁሉ ዕድሜያቸው ይረዝማል፡፡ አስተዋዮችም ይሆናሉ ሁሉን ማየትና የሚጠቅማቸውን መምረጥ ይችላሉ በሥነ-ምግባር የታነፁ አገርንና ወገንን የሚጠቅሙ ወደ ቅድስት ቤተክርስቲያን በመጠጋት ከክፉ ሁሉ የሚያመልጡ ይሆናሉ ለዚህም የቅዱሳን አምላክ እግዚአብሔር ይርዳን፡፡

🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
@wiseholyfathers
አስተያየት ካላቹ በ @Wisecomment_bot ይላኩልን


​​✞✞ ፆመ ፍልሰታ✞✞
(ጾመ ፍልሰታ) ፍልሰታ ፆም(ጾመ ማርያም) ሞት በጥር በነሀሴ መቃብር የፍልሰታ ፆም ከነሀሴ 1እስከ15 ነው ቤተ ክርስትያናችን እደሚገለፀው "እመቤታችን ያረፈችው ጥር 21ቀን ነው ሐዋርያት በድኗን ሊቀብሯት ወደ ጌተሰማኒ ይዘዋት ሲሄዱ አይሁድ አይተዋቸው በተኗቸው በዚህ ጊዜ መላእክት የእመቤታችንን አስክሬን ወስደው በገነት አኑረውታል በ8ወር በነሀሴ ሐዋርያት አስክሬኗን እንደገና ከጌታ ተቀብለው በፀሎትና በምህላ ቀብረዋታል በዚህ የቀብር ስነስርዓት ላይ ከ12 ሐዋርያት አንዱ ቶማስ አልነበረም።
ቅዱስ ቶማስ ከሀገረ ስብከቱ በደመና ተጭኖ ወደ እየሩሳሌም ሲመጣ ያገኛታል በዚህ ጊዜ ትንሳኤዋን ሌሎች ሐዋርያቶች አይተው ለእሱ የቀረበት መስሎት ተናዶ በፊት የልጅሽን ትንሳኤ ሳላይ ቀረው አሁን ደግሞ የአንቺን ትንሳኤ ሳላይ ቀርቼ ነበር ብሎ ከደመና ሊወረወር ቃጣው በዚህ ጊዜ እመቤታችን ቶማስን አፅናንታ ከእሱ በቀር ሌላ ትንሰኤዋን እንዳላየ ነገረችው።
ቶማስም ሐዋርያት ወዳሉበት እየሩሳሌም በደረሰ ጊዜ እመቤታችንን ቀበርናት ብለው ነገሩት እሱም አውቆ ምስጥሩን ደብቆ አይደረግም ሞት በጥር በነሀሴ መቃብር አላቸው ለማሳየትም መቃብር ሲከፍቱ አጧት በዚህ ጊዜ"እመቤታችን ተነስታ አርጋለች ብሎ ሁኔታውን ተረከላቸው ለምስክርም ይሆናል ብሎ የሰጠችውን (ሰበኗን) አሳያቸው ሰበኗንም ለበረከት ቆራርጠው ተከፋፍለው ወደ ሀገረ ስብከት ተበታትነዋል በዓመቱ ትንሳዬሽን ቶማስ አይቶ እንዴት እኛ ይቅርብን ብለው ከነሀሴ 1 ጀምሮ ሱባዬ ገቡ በነሀሴ14ቀንም ትኩስ በድን አድርጕ አምጥቶ ሰጣቸው ከቀበሯትም በጟላ በነሀሴ16 ተነስታለች በዚህ ቀን ጌታ ቀድሶ እመቤታችንም በልጇ እጅ ቆርባለች ከዚህ ጊዜ ጀምሮ የሐዋርያት ቤተክርስትያን የእመቤታችንን በረከት ለማግኘት ይህች ጊዜ ትፆማለች።


🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
@wiseholyfathers
አስተያየት ካላቹ በ @Wisecomment_bot ይላኩልን


​​ሐምሌ 22 ሁለት ታላላቅ ኢትዮጵያውያን አባቶች በክብር ያረፉበት ታላቅ ቀን ነው። ሰማዕቱ አቡነ ጴጥሮስ እና ታላቁ ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ ዘሸዋ (ሀገረ ስብከት):: በረከታቸው ይደርብን። ጸሎታቸው እና አማላጅነታቸው የሚወዷትን ሀገራቸውን ሀገራችንን እና ሕዝቡን ይጠብቅልን። በዚሁ አጋጣሚ በ2006 ዓ.ም የጻፍኩትና አዲስ ጉዳይ ላይ የወጣውን ጽሑፍ እንድታነብቡ ልጋብዛችሁ።
+++++++++

“ምንም ብትሉ፣ ምንም ብትሉ፤ ይህ ሕዝብ አንድ ሕዝብ ነው!!!!” (ታላቁ ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ፤1933 ዓ.ም - ሐምሌ 22/ 1982 ዓ.ም)
+++++
(ከቀሲስ ኤፍሬም እሸቴ፤ አዲስ ጉዳይ መጽሔት ሐምሌ 2ዐዐ6 ዓ.ም)

ሐምሌ 22/1982 ዓ.ም በመኪና አደጋ ሕይወታቸውን ያጡት በ20ኛው መቶ ክ/ዘመን የወንጌልና የታሪክ ብርሃንን በተለይ በወጣቱ ሕይወት ላይ የፈነጠቁት ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ፤ በድሮው የክፍላተ ሀገር አከፋፈል የሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ነበሩ። ከዚህ ዓለም ከተለዩ እነሆ 24 ዓመት ሞላቸው። መታወቂያቸው የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ጳጳስነታቸው እና አባትነታቸው ቢሆንም በጽሑፋቸው፣ በትምህርታቸው እና ለኢትዮጵያና ለአፍሪካ ባላቸው ጽኑዕ ፍቅር ከእምነት ድንበር ባሻገር የሁሉንም ኢትዮጵያዊ ልቡና ሊገዛ የሚችል ስብዕና የነበራቸው አባት ነበሩ።

ብፁዕነታቸው ሚያዚያ 23/1982 ዓ.ም፣ ሻሸመኔ ቅ/ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ያስተማሩት ትምህርት ኢትዮጵያ አገራችን በዚያን ወቅት የነበረችበትን የጦርነት እሳት እና መጻዒውን የሕዝቧን ሁናቴ በቅጡ የሚያመለክት ነበር። ከተናገሯቸው ዐበይት ቃላት መካከል “ምንም ብትሉ ምንም ብትሉ፣ ይህ ሕዝብ አንድ ሕዝብ ነው። ቤተ ክርስቲያኒቱ ደህና አድርጋ መሥራታዋለችና” የሚለውን አባባላቸውን ዛሬም ድረስ በቃሌ አስታውሰዋለሁ። “ምንም ብትሉ ምንም ብትሉ” ያሉት በዓይነ ልቡናቸው ማን ምን እያለ ታይቷቸው ይሆን? እያልኩ ራሴን እጠይቃለሁ።

በተለይም የሃይማኖት አባቶች መንፈሳዊ እና አገራዊ አቋማቸው በሚዋዥቅበት በዚህ ዘመን እጅግ በጣም ባልራቀው ዘመን የነበሩትን የነአቡነ ጎርጎርዮስን ሕይወት መጥቀስ ዙሪያ ገባው ጨለማ እንዳልሆነ ለማሳየት አንድም በእውነት እና በዕውቀት ብርሃን ለመመላስ አንገቱን ቀና ለማድረግ ለሚታትር ማንም ሰውም ጥብዓት ለመስጠት ይጠቅማል።

ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ በጵጵስና ያገለገሉባቸው ዓመታት 10 ዓመታት ብቻ ናቸው። በነዚህ ጥቂት ዓመታት ያበረከቷቸው ተግባራት ግን ዛሬም ሕያው ሆነው ይታያሉ። ከአገር ቤት አገራዊውን ዕውቀት በቅጡ በማደላደል፣ ወደ ውጪውም ዓለም በመሔድም ከዘመናዊው ዓለም የዕውቀት ገበያ በመገብየት ሚዛናዊነቱን የጠበቀ ኅሊና ባለቤት የሆኑት ገና ከማለዳው ነው።

የአገሩን ዕውቀት ሲጨብጥ የውጪው፣ የውጪውን ሲይዝ የአገሩ ለሚጎድልበት አገርና ምሁር ጥሩ ማሳያ ናቸው። የአገራቸውን ሳያውቁ የውጪውን ብቻ በማነብነብ ያልተፈተነ መፍትሔ ለአገራቸው ችግር ለመስጠት በመሞከር መክነው የቀሩ ብዙ ትውልዶቻችንን ያጣነው በዚህ ምክንያት ነው። አገራችን ከአፍሪካዊ ማንነት በአንድ ጊዜ ተነቅላ ፈረንጃዊ ለመሆን ሞክራ በመካከል ደክማ የቀረችው መሠረቷን ሳታጠብቅ በውጪው ላይ ለመንጠላጠል ባደረገችው ሙከራ ነው።

ዕብራይስጥ፣ እንግሊዝኛ፣ ፈረንሳይኛ እና አረብኛ ቋንቋዎችን በቅጡ የሚያውቁት ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ በዝዋይ ሐመረ ብርሃን በመሠረቱት የቅዱስ ገብርኤል ገዳም የዕውቀት ዓምባ አቋቁመው ኢትዮጵያዊውን ታሪክ ከዓለሙ ጋር እያነጻጸሩ ለደቀመዛሙርቶቻቸው ሲያሰተምሩ ቆይተዋል። ጭው ጭው የሚል የሩቅ አገር ሬዲዮ ድምጽ ከደጃፋቸው የሚሰማው እኒህ አባት ለገዳማውያኑና ለትምህርት ከየከተማው ለሚሰባሰቡት ተማሪዎቻቸው ዓለም አቀፍ ጉዳዮችን ለተማሪዎቹ ዕውቀትና ሥነ ልቡና በሚመጥን መልኩ ሲያቀርቡ መስማት ያስደንቃል።

የሃይማኖትና የታሪክ ጥናትና ምርምራቸውን “የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ታሪክ” እና “የቤተ ክርስቲያን ታሪክ ዓለም መድረክ” በሚሰኙ መጻሕፍቶቻቸው ቅልብጭ አድርገው አቅርበዋል። ለ፤መጻሕፍቱ መርጃነት የተጠቀሙባቸው ዋቤ መጻሕፍት ዝርዝር በሕዳግ በገጽ በገጹ ተጠቅሶ ይታያል። በአዋቂነት ድፍረት ሳይሆን በማስረጃ ጥንቁቅነት የቀረቡ፣ ከወጣት የሰንበት ት/ቤት ተማሪዎች እስከ ካህናት ብሎም ከየዩኒቨርሲቲው ትምህርት የዕረፍት ጊዜውን ወስዶ ከርሳቸው ሊማር ለሚመጣው ዘመናዊ ትውልድ በሚሆን መልኩ የተዘጋጁ የጥናት ሥራዎች ናቸው።

ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ የሃይማኖት አባቶች የሚያሳዩትን የቅምጥል ኑሮ እንደሚቃወሙ በአንድም በሌላም ቢገልጹም "እኛ የመነኮስነው ለፍትፍት አይደለም" የምትለው አባባላቸውን ብዙዎች ያስታውሱታል። መነኮሳት ይህንን መስመር የሚመርጡት እንደማንኛውም ተርታ አማኝ በተቀማጠለ ኑሮ ለመመላለስ ሳይሆን ራስን በሚጎስም መንፈሳዊ እና ማኅበራዊ አገልግሎት ለመጠመድ መሆኑን አበክረው ይናገራሉ። ለኑሮ የማይመቸውንና ከዝዋይ ሐይቅ በተጎራበተው የቅዱስ ገብርኤል ገዳማቸው ጠንካራ ኑሮን በመቋቋም ገዳሙን ለወላጅ አልባ ሕጻናት ማሳደጊያነት እና ለትምህርት ማዕከልነት የሚመች ሥፍራ ያደረጉት በዚሁ መርሐቸው ነበር። በተለይም በዚህ ዘመን፣ በሃይማኖት አባቶች ላይ የሚታየው የቅምጥል ኑሮ በብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ሕይወት ሲመዘን እጅጉን ጎዶሎ ይሆናል።

ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ አባትና እናት የሌላቸውን ሕጻናት ሰብስቦ ማሳደግ የቤተ ክርስቲያን አንዱ ዓላማ መሆኑን በተግባር አሳይተዋል። እርሳቸው ባረፉበት ወቅት ከ200 በላይ ሕጻናት የሚያድጉበት የነበረው ያ ገዳም የነገ ተስፋ የሆኑ ልጆችን በመንከባከቡ በኩል የሃይማኖት መሪዎች ያለባቸውን ታላቅ ኃላፊነት የሚያመለክት ነው። የሌላውን እንኳን ብንተው የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በጥቂቱ ከሚታዩ ሙከራዎች ውጪ ይህ ነው የሚባል ሕጻናትን የመታደግ እንቅስቃሴ ስታደርግ አይታይም። በሀብት ደረጃቸው የናጠጡ የከተማ አብያተ ክርስቲያናት ለዚህ ዓይነቱ ጉዳይ ጊዜ ያላቸውም አይመስሉም። የድሃ መብዛት የፈጣሪ ጸጋ ይመስል ድህነትንና ድሃውን በእነርሱ ኑሮ ማድመቂያነት የወሰዱት ይመስላል።

ሌላውና የዚህ ዘመን የአገራችንና የቤተ ክርስቲያን ሁነኛ ፈተና የሆነውን ዘረኝነትን በተመለከተ የብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ሕይወት ብዙ አስተማሪነት አለው። የሚያውቋቸው ሰዎች በሙሉ በአንድነት የሚመሰክሩላቸው በወገን፣ በወንዝ፣ በመንደርተኝነትን የማይጠረጠሩ፣ ዘረኝነትን በፍፁም የሚጠየፉ አባት መሆናቸውን ነው። ቤተ ክርስቲያናችንን ጨምድዶ ለያዛት የዘመነ መሳፍንት ዓይነት መንደርተኝነት፣ ጠባብነት እና ጎሰኝነት እንደ ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ያለ ሰው ያስፈልጋል።

በምድራውያን ባለ ሥልጣኖች ፊት በሃይማኖታዊ ግርማ እንጂ በማጎብደድ መቆም ያልለመደባቸው ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ራሳቸውን አክብረው አባትነትን፣ ሃይማኖተኝነትን፣ ቤተ ክርስቲያንን የሚያስከብሩ መሆናቸውን ብዙዎች ይስማሙበታል። የታሪክ ተመራማሪ እንደመሆናቸው ቤተ ክርስቲያን በቤተ መንግሥት መዳፍ ሥር ስትወድቅ ያለውን ጣጣ በመጻሕፍቶቻቸው መጥቀስ ብቻ ሳይሆን እርሳቸውም ያ ነገር እንዳይደገም በሕይወታቸው አብነት ሆነዋል።


​​☞ሐምሌ 19 እንኳን ለቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፡፡
☞ቂርቆስ ማለት የኤፍራን ቀለም ማለት ነው፡፡ አባቱ ቆዠሞስ እናቱ ኢየሉጣ
ይባላሉ፡፡ ኢየሉጣ ማለት ምልእት ሃይማኖት ማለት ነው፡፡ ሀገሯ ሮም (አንጌቤን)
ነው፡፡
☞እስክንድሮስ በነገሠ ጊዜ በሃይማኖት ምክንያት በምእመናን ላይ ስደት
ደረሰባቸው፡፡
]☞እየሉጣም የ3ዓመት ሕፃን ቂርቆስን ይዛ ከሮም ወደ ጠርሴስ ቸሰዳ
ተቀመጠች፡፡
☞ንጉሡ ክርስቲያኖችን እያደነ ወደ ሸሹበት ሀገር ደርሶ አገኛትና ተይዛ ቀረበች፡፡
መኩንኑም ሀገርሽ የት ነው ስምሽ ማን ይባላል፡፡ ወገንሽስ ማን ነው ብሎ
ጠየቃት፡፡ ኢየሉጣም ሀገሬ አንጌቤን ዘሮም ስሜ ክርስቲያን ነው፡፡ ከአንተ ሸሽቼ
ብመጣ አገኘኽኝ አለችው
☞መኮንኑም መልሶ ለጣዖት ስገጂ ሰምሽን ግለጪ እንዳትሞቺ ሲል ጠየቃት፡፡
እሷም እውነትን ለማወቅ ከፈለግሽ ወደ መንደር ልከ የ3 ዓመት ሕፃን አሰመጣና
የምናመልከውን እሱ ይንገረን አለችው፡፡
☞ህፃኑ ቂርቆስም መጣ ንጉሡ ለጣዎት ስገድ አለው ራሳቸውን ማዳን
ለማይቻላቸው ለረከሱ ጣዖታትኽ አልሰግድም አለው፡፡
☞በዚህ ምክንያት መኮንኑ ተቁጥቶ በታላቅ የብረት ጋን ውሃ አስፈልቶ
እንዲጨምሯቸው አዘዘ፡፡ የፍላቱም ድምፅ እንደ ክረምት ነጉድጎድ ኾነ ይህን
ሲጮኽ ሰምታ ኢየሉጣ ያን ጊዜ ፈራች፡፡ ቂርቆስ ግን እናቴ ጠንክሪ 3ቱ ደቂቃን
ያዳነ ያድነናል እያለ ወደ ጌታ ለመነላት፡፡
✞ጌታም ልባን ወደ ሰማይ አሳርጎ የተዘጋጁላትን የብርሃን ማደሪያዎች አሳያትና
ጽናት አግታ ጌታን አመሰገነች፡፡ ልጇንም አመሰገነች፡፡
☞ልጇንም እንዲህ አለችው ከዛሬ ጀምሮ አንተ አባቴ እኔ ልጅኽ ነኝ ከእኔ
የተወለድኽበት ቀን ብፅዕት ናት አለችው፡፡ ይህን እያለችው በጋን በፈላ ውሃ እና
አሳት ውስጥ ገቡ፡፡
☞ያን ጊዜ ቅዱስ ገብርኤል በጌታ ፈቃድ ከሰማይ ወርዶ የእሳቱን ኀይል እንደ
ንጋት ውርጭ ቀዠቃዛ አደረገውና ከእሳቱ በሰላም ወጥተዋል፡፡ ይቺ ሊቀ
መላዕክት ቅዱስ ገብርኤል ከእሳት የወጡበት ቀን ነች ሐምሌ 19 በዓመታዊ
በዓል ታስቦ በደማቅ ሁኔታ ከዋዜማው ጀምሮ በሊቃውንቱ በቅኔ ማህሌት
በምስጋና በቤተክርስቲያናችን ታከብረዋለች፡፡
☞(መድብለ ታሪክ መጻሐፍ ቁጥር 1)
☞ደስታን አብሳሪው ሊቀመላዕክት ቅዱስ ገብርኤል እኛንም እንደ አሳት
ከሚያቃጥል ሀጥያት ያውጣን፡፡
]በዚህ ሰአት በረሀብ እሳት ፤ በጥም አሳት ፤በስደት አሳት ውስጥ ያሉ
ወገኖቻችን ከዚህ እንደ አሳት ከሚያቃጡ ነገሮች ውሉ ያውጣልን፡፡


🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
@wiseholyfathers
አስተያየት ካላቹ በ @Wisecomment_bot ይላኩልን


​​ብራብ በሥላሴ እጠግባለሁ ብጠማም በሥላሴ እረካለሁ

ድሀ ብሆን በሥላሴ እበለፅጋለሁ ብራቆት በሥላሴ ቸርነት መጐናጸፊያ እጐናጸፋለሁ

በደዌ ብያዝ በሥላሴ እድናለሁ ብቆስልም በሥላሴ እፈወሳለሁ

ብስጭት ቢደርስብኝ በሥላሴ እደሰታለሁ ኀዘን ቢያገኘኝም በሥላሴ እጽናናለሁ

ብታመም በሥላሴ ቸርነት እድናለሁ ብሞትም በሥላሴ ሕይወት እንሣለሁ

ሥላሴ የራሴ አክሊል ናቸው ሥላሴ የአንጻረ ገጽታየ ማማተቢያ ናቸው ሥላሴ የዐይኖቼ ብርሃን ናቸው

☘️☘️☘️ ሰይፈ ስላሴ ☘️☘️☘️

🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
@wiseholyfathers
አስተያየት ካላቹ በ @rafato_el ይላኩልን


​​ብርሃናተ ዓለም ቅዱስ ጴጥሮስ ወጳውሎስ

ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስና ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ
መልካሙን የክርስትና ገድል ተጋድለው ሰማዕትነት የተቀበሉበት ዕለት ነው።

የቅዱሳኑ በረከት ዘወትር ከእኛ ጋር ይሁን! አሜን!
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
@wiseholyfathers
አስተያየት ካላቹ በ @Wisecomment_bot ይላኩልን


​​ወንበዴ ብታይ ፈያታዊ ዘየማን አዳምን ቀድሞት ገነት እንደገባ እኔንስ ይሄ ወንበዴ ቀድሞኝ ይገባ የለምን በል::

ኃጥእ ዘማዊም ብታደ ይህ ምናልባት ክርስቶስን ይወደው እንደሆነ ስለ ኃጥአቱም ከኔ በላይ ያለቅስ እንደሆን ምን አውቃለሁ በል እንጂ

ማንንም አትውቀስ::

ሁልጊዜ እንዲህ የሚያስብ ሰው ከፍቅረ እግዚአብሔር ተለይቶ አያውቅም::'

መልአከ ብርሃን አድማሱ ጀንበሬ

🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
@wiseholyfathers
አስተያየት ካላቹ በ @Wisecomment_bot ይላኩልን


​​"በመንፈስ ቅዱስም እናምናለን እርሱም ጌታ ሕይወትን የሚሰጥ ከአብ የሠረፀ ከአብ ከወልድ ጋር በአንድነት እንሰግድለታለን እናመሰግነዋለን እርሱም በነቢያት አድሮ የተናገረ ነው ።"
    ጸሎተ ሐይማኖት
እንኳን ለበዓለ መንፈስ ቅዱስ እና ጾመ-ሐዋርያት አደረሰን አደረሳችሁ።

መልካም ጾም ይሁንልን !!


​​ሊከተለኝ የሚወድ… መስቀሉን ተሸክሞ ይከተለኝ


የእግዚአብሔር ፍቅር በመስቀል እንደተገለጠ ሁሉ የሰው ልጆችም እርሱን የመውደዳችን መገለጫ መስቀሉን በመሸከም መከተል እንደሆነ በአምላካዊ ቃሉ አስተምሮናል፡፡ ይህም ማለት እንደ ጌታችን ረጅምና ክብደት ያለው ዕፀ መስቀልን በትከሻችን ተሸክመን ቀራንዮ እንድንጓዝ ሳይሆን መከራ መስቀሉ ስለ እኛ ሲል የፈጸመልን መሆኑን በማመን እና ተከታዮቹ በመሆናችን የሚመጣብንን መከራ በመታገሥ መኖር እንደሚገባን ሲያመለክተን ነው፡፡ በዚህም መሠረት “መስቀል መሸከም” የተባለው በዓለም ስንኖር በክርስትና ምክንያት የሚገጥመንን መከራ ነው፡፡ “በዓለም ግን መከራ ትቀበላላችሁ ነገር ግን ጽኑ እኔ ዓለሙን ድል ነስቼዋለሁና” እንዲል /ዮሐ.16÷33/፡፡ በወቅቱ ይህ ቃል የተነገራቸው ቅዱሳን ሐዋርያት መስቀሉን በመሸከም ማለትም ስለ ክርስትና ኑሮ የመጣባቸውን መከራ በመታገሥ እና ድል በመንሳት ኑረዋል ለዚህም ነው፡፡ “መንግሥተ ሰማያት በብዙ መከራ እንገባ ዘንድ ያስፈልገናል” በማለት በቃልም በተግባርም የገለጹት /ሐዋ.14÷22/፡፡ የክርስትና ጉዞ እንደ ቀራንዮ ጉዞ መከራ የበዛበት ነው፡፡ ፈቃደ ሥጋን እየታገሱ ለፈቃደ ነፍስ እየኖሩ ዓለምን፣ ዲያብሎስን እየተዋጉ እስከ ሞት በመጽናት ተጉዘው የክብር አክሊል የሚቀዳጁበት ሕይወት ነውና “እስከ ሞት ድረስም የታመንህ ሁን የሕይወት አክሊልንም እሰጥሀለሁ” ተብሎ እንደተጻፈ /ራእ.2÷10/፡፡

🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
@wiseholyfathers
አስተያየት ካላቹ በ @Wisecomment_bot ይላኩልን


​​መንፈሳዊነት ምንድነው ?

ለመሆኑ መንፈሳዊነት ምንድን ነው፡፡ ረዥምቀሚስ መልበስ ነው? ፀጉርን በአሮጌ ሻሽ መሸፈን ነው? ገላን ያለመታጠብ ነው? አንገትን መድፋት ብቻ ነው? ቀስ ብሎ መናገር ነው? ኋላ ቀርነት ነው? አይመስለኝም፡፡ ቴሌቭዥን አለማየት፣ኢሜይል አለመጠቀም ነው? ከጸሎት መጻሕፍት በቀር ሌላ ነገር አለማንበብ ነው? መንፈሳዊነትኮ በመንፈስ ቅዱስ መመራት ነው፡፡ ራስን ማሸነፍ ነው፡፡ አእምሮን እና ልቡናን ቀና እና ሰላማዊ ማድረግ ነው፡፡ ለመሆኑ የውስጡ መንፈሳዊነት አይደለም እንዴ ወደላይ መገለጥ ያለበት፡፡ ስለ ሐዋርያት ስንናገርኮ የነፍሳቸው ቅድስና ለሥጋቸው፣ የሥጋቸው ቅድስና ለልብሳቸው፣ የልብሳቸው ቅድስና ደግሞ ለጥላቸው ተረፈ ነው የምንለው፡፡ መንፈሳዊነቱ ከውስጥ ወደ ውጭ እንጂ ከውጭ ወደ ውስጥ አልነበረም፡፡ አንዳንድ ጊዜ «መንፈሳዊነት» ከ «መንፈሳይነት» ጋር እየተመሳሰለ የምንቸገር ይመስለኛል፡፡ ዲያቆን ኤፍሬም እሸቴ ነው ይህችን ቃል ያመጣት፡፡ ከሁለት ቃላት «መንፈሳዊ» እና «መሳይ» ከሚሉ ቃላት ቆራርጦ «መንፈሳይ» የሚል ቃል ፈጠረ፡፡ ትርጉሙም «መንፈሳዊ መሳይ» ማለት ነው፡፡ እነዚህ ሰዎች መንፈሳውያን ይመስላሉ እንጂ አይደሉም፡፡
አባ ኤፍሬም ሶርያዊ ባስልዮስን ለማየት በሄደ ጊዜ ስለ ክብረ ወንጌል ሲል ከላዩ የወርቅ ልብስ ለብሶ ፣ የወርቅ ወንበር ዘርግቶ፣ የወርቅ ጫማ ተጫምቶ በጉባኤው ላይ ባየው ጊዜ «ደገኛ መምህር የተባለው ባስልዮስ ይኼ ነውን?» ብሎ ነበር፡፡ በኋላ ግን ተአምራቱን አይቶ አድንቆታል፡፡ አንዳንድ ጊዜ የውጭ ገጽታ ውስጥን ሊገልጥም ላይገልጥም ይችላልና፡፡ ልክ ነው ክርስቲያናዊ አነጋገር፣ አለባበስ፣ አረማመድ፣ ገጽታ ያስፈልጋል፡፡ ይህ ማለት መንፈሳዊነት ጅልነት፣ ከርፋፋነት፣ ኋላ ቀርነት ወይንም ደግሞ፣ ንጽሕናን አለመጠበቅ ማለት ግን አይደለም፡፡ በመንፈሳዊነታቸው የሚደነቁት የቤተ ክርስቲያን ከዋክብት እነ ዮሐንስ አፈወርቅ፣ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ፣ጎርጎርዮስ ዘእንዚናንዙ፣ባስልዮስ ዘቂሳርያ በዘመኑ በነበረው የግሪክ ፍልስፍና እና ዕውቀት የበለጸጉ ነገር ግን ዕውቀታቸውን እናሥልጣኔያቸውን በወንጌል የቃኙ ነበሩ፡፡
ብዙዎቻችን ከውስጥ ለሚመነጩ ትዕግስትን፣ ደግነትን፣ ታዛዥነትን፣ ትኅትናን፣ አርቆ ማሰብን፣ ኀዘኔታን፣ ፍቅርን፣ ትጋትን ለመሰሉ ነገሮች ትኩረት አንሰጥም፡፡ ከዚያ ይልቅ ተዋንያን ሊያደርጉት የሚችሉትን የውጭ ገጽታን ብቻ በማየት መመዘን እንመርጣለን። እውነተኛው መንፈሳዊነት ግን ከመንፈሳይነት መለየት አለበት፡፡ መንፈሳይ ሰዎች የራሳቸው መለያ ባሕርያት አሏቸው፡፡ እነዚህ ሰዎች ከውስጣዊ መንፈሳዊነት ይልቅ ለውጫዊ ነገሮች ትልቅ ትኩረት ይሰጣሉ፡፡ አንዳንድ ጊዜ ውስጣዊ ማንነታቸውን ለመሸፈን ሲሉ ሕግ ከሚፈቅደው በላይ ለውጫዊ ገጽታ ይጨነቃሉ፡፡ ቤተ ክርስቲያን ስለ የፀጉር አያያዝ የራስዋ ባህል አላት፡፡ እነርሱ ግን ፀጉር መታጠብን ኃጢአት ያደርጉታል፡፡ ክርስቲያኖች የሚለብሱት ልብስ ራሳቸውን የማያጋልጥ እንዲሆን ትመክራለች፡፡ እነርሱ ግን ልብስ ሁሉ መሬት ካልጠረገ ይላሉ፡፡ ያደፈ በመልበስ፣ የአእምሮ ችግር ያለባቸው ይመስል እጅግ ቀሰስ ብለው በመናገር፣ ሰው መሆናቸውን ረስተው ምንም ነገር እንደማይበሉ እና እንደማይጠጡ በማሳመን፣ አረንጓዴ ቢጫ ቀይ በመልበስ፣ ሰንሰለት በመታጠቅ፣ ትልልቅ መቁጠርያ እጃቸው ላይ በመጠቅለል፡፡ ይበልጥ መንፈሳዊ ሆነው መታየት ይፈልጋሉ፡፡
ቀሲስ ደጀኔ ሺፈራው በዱርዬ እና በሴተኛ አዳሪዎች ዘንድ ያለውን ያህል ፈሪሃ እግዚአብሔር በአገልጋዮች ዘንድ የለም ይል ነበር፡፡
አንዳንዶች በአገልግሎት እየበረቱ ሲሄዱ ከመንፈሳዊነት ወደ መንፈሳይነት ስለሚለወጡ፡፡ጋሽ ግርማ ከበደ ከሚያስተምረው ነገር የማልረሳው ቃል አለ፡፡ «ሰው የሚጠላውን ኃጢአት ደጋግሞ ይሠራዋል» ይላል፡፡ ለምንድን ነው ደጋግሞ ይሠራዋል ያለው? እኔ እንደ ተረዳሁት መጀመርያውኑ ይህ ሰው ውስጡ ያላመነበትን እና ሊያደርገው የማይፈልገውን ነገር ነው ለማስመሰል ሲል እያወራ ያለው፡፡ ስለዚህም በውስጡ ያንን የጠላውን ነገር ላለማድረግ መንፈሳዊ ተጋድሎ ስለማያደርግ ደጋግሞ ሲሠራው ይገኛል፡፡ እንዲያውም አንዳንዶች መንፈሳያን ስለ አንድ ሰው መንፈሳዊነት ደጋግመው በጥላቻ ወይንም በንቀት፣ ወይንም ደግሞ በመመጻደቅ የሚያወሩ ከሆነ ያንጊዜ አንዳች ነገር ተረዱ፡፡ ሳያስቡት እየተናገሩ ያሉት ስለ ራሳቸው ነው፡፡ መንፈሳውያን ሰዎች ስለሌሎች ውድቀት ሲያነሡ ከርኅራኄ እና ከኀዘኔታ ጋር ነው፡፡ የደስታ ስሜት አይሰማቸውም፡፡ እንደ ጀብዱም አይቆጥሩትም፡፡ ለዚህም ነው በቅዳሴ አትናቴዎስ ሊቁ ስለ አዳምና ሔዋን አንሥቶ «እኛስ እናንተን ልንወቅሳችሁ አንችልም» በማለት የተናገረው፡፡ መንፈሳውያን ይነበባሉ፤መንፈሳያን ግን ይታያሉ፡፡ መንፈሳውያን ይቀመሳሉ፣ መንፈሳያን ግን ይላሳሉ፡፡ መንፈሳውያን ያዳምጣሉ፤ መንፈሳያን ግን ይለፈልፋሉ፡፡ መንፈሳውያን ያስተውላሉ፤ መንፈሳያን ግን ይቸኩላሉ፤ መንፈሳውያን ይመዝናሉ፤ መንፈሳያን ግን ያፈሳሉ፡፡ መንፈሳውያን ያርማሉ፤ መንፈሳያን ግን ይተቻሉ፡፡ መንፈሳውያን ጠላቶቻቸውን አንድ ሺ ዕድል ይሰጣሉ፤ መንፈሳያን ግን ወዳጆቻቸውን ጠላቶቻቸው ለማድረግ አንድ ሺ በር ይከፍታሉ፡፡ መንፈሳውያን ይጾማሉ፣ መንፈሳያን ይራባሉ፤ መንፈሳውያን ይጸልያሉ፣ መንፈሳያን ግን ይናገራሉ/ያነባሉ፡፡ መንፈሳውያን ሱባኤ ይይዛሉ፣ መንፈሳያን ግን ስለ ሱባኤያቸው ያወራሉ፡፡ መንፈሳውያን ይሰጣሉ፣ መንፈሳያን ግን ሲሰጡ ያሳያሉ፡፡ መንፈሳውያን ቃለ እግዚአብሔርን ያስተምራሉ፣ መንፈሳያን ግን በራሳቸው ቃላት ይጠበባሉ፤ መንፈሳውያን ወደ ውስጥ፣ መንፈሳያን ወደ ውጭ ያያሉ፡፡ መንፈሳውያን የነገን፣ መንፈሳያን የዛሬን ያያሉ፡፡ መንፈሳውያን ምክንያቱን፣ መንፈሳያን ድርጊቱን ያያሉ፡፡ መንፈሳውያን ራሳቸውን፣ መንፈሳያን ሌላውን ያያሉ፡፡

ራሳችንን እንመልከት እኛስ መንፈሳዊ ነን ወይስ መንፈሳያን


†✝† እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው በሰላምና በፍቅር አደረሳችሁ፤ አደረሰን። †✝†

†✝† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †✝†

†✝† ብርሃነ ትንሣኤ †✝†

†✝† የዓለማት ሁሉ ፈጣሪ : የዘለዓለም አምላክ ወልድ ዋሕድ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህች ዕለት መግነዝ ፍቱልኝ : መቃብር ክፈቱልኝ ሳይል በባሕርይ ኃይሉና ሥልጣኑ ተነስቷልና እንኳን ደስ አለን::

††† ከዚህ በኋላ ለ50 ቀናት እንዲህ እያልን ሰላምታ እንለዋወጣለን:-
††† ክርስቶስ ተንስአ እሙታን!
¤በዐቢይ ኃይል ወስልጣን!
††† አሠሮ ለሰይጣን!
¤አግዐዞ ለአዳም!
††† ሰላም!
¤እምይእዜሰ!
††† ኮነ!
¤ፍሥሐ ወሰላም!

በእርግጥም አምላካችን በሞቱ ሞትን ገድሎ : በትንሣኤው ሕይወትን አድሎናልና ደስታ ይገባናል:: መድኃኔ ዓለም በኅቱም ድንግልና እንደ ተወለደ በኅቱም መቃብር ተነስቷል:: ለደቀ መዛሙርቱም "ሰላም ለእናንተ ይሁን" ሲል በዝግ ደጅ ገብቷል::

በዕለተ ትንሣኤው የመጀመሪያውን ደስታ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ተካፍላለች:: የእርሷን ያህል በሃዘን የተጐዳ የለምና:: ቀጥለው ቅዱሳት አንስት እነ ማርያም መግደላዊት ትንሣኤውን አይተዋል:: ሰብከዋልም::

††† በዚሕች ቀን ማዘን አይገባም:: በትንሣኤው የደነገጡና የታወኩ የአጋንንትና የአይሁድ ወገኖች ብቻ ናቸውና::

††† አምላካችን ወልደ እግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስ ከትንሣኤው በረከት አይለየን:: በዓሉንም የሰላም : የፍቅርና የበረከት ያድርግልን::

††† የጌታችን በጐ ምሕረቱ በሁላችን ትደርብን::

††† "ሕያውን ከሙታን መካከል ስለ ምን ትፈልጋላችሁ? ተነስቷል እንጂ በዚህ የለም:: 'የሰው ልጅ በኃጢአተኞች እጅ አልፎ ሊሰጥና ሊሰቀል: በሦስተኛውም ቀን ሊነሣ ግድ ነው' እያለ ገና በገሊላ ሳለ ለእናንተ እንደተናገረ አስቡ::" †††
(ሉቃ. ፳፬፥፭-፰)

††† "አሁን ግን ክርስቶስ ላንቀላፉት በኩራት ሆኖ ከሙታን ተነስቷል:: ሞት በሰው በኩል ስለ መጣ ትንሣኤ ሙታን በሰው በኩል ሆኗልና:: ሁሉ በአዳም እንደሚሞቱ እንዲሁ ሁሉ በክርስቶስ ደግሞ ሕያዋን ይሆናሉና::" †††
(፩ቆሮ. ፲፭፥፳)

††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †††

🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
@wiseholyfathers
አስተያየት ካላቹ በ @Wisecomment_bot ይላኩልን

20 last posts shown.