አንጋፋው ፖለቲከኛ እና የምጣኔ ሀብት ምሁሩ ቡልቻ ደመቅሳ ከእዚህ ዓለም በሞት ተለዩ
በምዕራብ ወለጋ ዞን በቦጂ ብርመጂ ወረዳ በጊንቢ ዞን ከአባታቸው አቶ ደመቅሳ ሰንበቶ እና ከእናታቸው ነሲሴ ሰርዳ በ1923 ዓ.ም የተወለዱት አቶ ቡልቻ ደመቅሳ በተወለዱ 94 ዓመታቸው አርፈዋል።
አቶ ቡልቻ ደመቅሳ በተለያዩ የመንግስት ተቋማት ሃገራቸውንና ህዝባቸውን የገለገሉ፣ የኢትዮጵያ ብሄሮች መብት ሳይሸራረፍ እንዲከበር የታገሉ፣ ሕብረብሔራዊት ጠንካራ ኢትዮጵያ ተፈጥራ ለማየት እድሜያቸውን በሙሉ የታገሉ መልካም ስብእናን የተለበሱ ሰው ነበሩ።
የደርግ መውደቅን ተከትሎ የፋይናንስ ስርዓት ለውጥ ሲደረግ ወዳጆቻቸውን በማስተባበር የአዋሽ ባንክ እንዲመሰረት ከፍ ያለ ሚና ከመወጣት ባሻገር የባንኩ ፕሬዚዳንት በመሆን ባንኩ ዛሬ ለደረሰበት እድገት የበኩላቸውን ደማቅ አሻራ ያሳረፉ፣ ለውጥ ለማምጣት ተመራጩ መንገድ ሰላማዊ የፖለቲካዊ ትግል ነው በሚል የጸና እምነት የፖለቲካ ፓርቲ መስረተው ፖርላማ በመግባት በመንግስት ላይ የሰላ ትችት ሲያቀርቡ የነበሩ አባትም ነበሩ።
በዛሬው እለት ዜና እረፍታቸው መሰማቱን ተከትሎ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ እና ከንቲባ አዳነች አቤቤን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ሀላፊዎችን ጨምሮ በርካቶች የተሰማቸውን ሀዘን በመግለፅ ላይ ይገኛሉ።
የዝግጅት ክፍላችን ለጉምቱው ምሁር እና ፖለቲከኛ ህልፈተ ህይወት ማዘኑን እየገለፀ ለቤተ ዘመዶች እና አድናቂዎች መፅናናትን ይመኛል
በምዕራብ ወለጋ ዞን በቦጂ ብርመጂ ወረዳ በጊንቢ ዞን ከአባታቸው አቶ ደመቅሳ ሰንበቶ እና ከእናታቸው ነሲሴ ሰርዳ በ1923 ዓ.ም የተወለዱት አቶ ቡልቻ ደመቅሳ በተወለዱ 94 ዓመታቸው አርፈዋል።
አቶ ቡልቻ ደመቅሳ በተለያዩ የመንግስት ተቋማት ሃገራቸውንና ህዝባቸውን የገለገሉ፣ የኢትዮጵያ ብሄሮች መብት ሳይሸራረፍ እንዲከበር የታገሉ፣ ሕብረብሔራዊት ጠንካራ ኢትዮጵያ ተፈጥራ ለማየት እድሜያቸውን በሙሉ የታገሉ መልካም ስብእናን የተለበሱ ሰው ነበሩ።
የደርግ መውደቅን ተከትሎ የፋይናንስ ስርዓት ለውጥ ሲደረግ ወዳጆቻቸውን በማስተባበር የአዋሽ ባንክ እንዲመሰረት ከፍ ያለ ሚና ከመወጣት ባሻገር የባንኩ ፕሬዚዳንት በመሆን ባንኩ ዛሬ ለደረሰበት እድገት የበኩላቸውን ደማቅ አሻራ ያሳረፉ፣ ለውጥ ለማምጣት ተመራጩ መንገድ ሰላማዊ የፖለቲካዊ ትግል ነው በሚል የጸና እምነት የፖለቲካ ፓርቲ መስረተው ፖርላማ በመግባት በመንግስት ላይ የሰላ ትችት ሲያቀርቡ የነበሩ አባትም ነበሩ።
በዛሬው እለት ዜና እረፍታቸው መሰማቱን ተከትሎ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ እና ከንቲባ አዳነች አቤቤን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ሀላፊዎችን ጨምሮ በርካቶች የተሰማቸውን ሀዘን በመግለፅ ላይ ይገኛሉ።
የዝግጅት ክፍላችን ለጉምቱው ምሁር እና ፖለቲከኛ ህልፈተ ህይወት ማዘኑን እየገለፀ ለቤተ ዘመዶች እና አድናቂዎች መፅናናትን ይመኛል