! ሁለት ዝንጀሮዎች። አንዱ ዕድለኛ ነው። ሁለተኛው ዕድለ ቢስ ነው። ሁልጊዜ ወደ ሙዝ እርሻው ሲሄዱ ዕድለኛው ዛፉ ላይ ወጥቶ ሙዝ እየቆረጠ ታች ወዳለው ዕድለ ቢስ ይወረውርለታል።
እንዲህ ሲሆን የሙዝ እርሻው ባለቤት ሌሎች ገበሬዎችን አስተባብሮ ታች ያለውን ዕድለቢስ ዝንጀሮ ይዘው በዱላ ይቀጠቅጡታል። ለብዙ ጊዜ ዕድለ ቢሱ ዝንጀሮ ሲደበደብ ከረመ።
ዕድለቢሱ ዝንጀሮ ሁልጊዜ መቀጥቀጡ ሰለቸውና "ዛሬ እኔ ከላይ ሆኜ ሙዙን ወደ ታች ልወርውርልህ" አለውና ቦታ ተቀያይረው ሙዝ መቁረጥ ጀመሩ።
ዝንጀሮዎቹን ያዩት ገበሬዎች ዱላ ይዘው ደረሱባቸው። በዚህን ጊዜ ገበሬዎቹ ታች ያለውን ዕድለኛውን ዝንጀሮ ይዘው ሊቀጠቅጡት ሲሉ የሙዙ ባለቤት እንዲህ አላቸው፣
"ይሄንን ዕድለ ቢስ ዝንጀሮ አትምቱት። ሁልጊዜ እንደቀጠቀጥነው ነው። ዛሬ ግን ከላይ የተሰቀለውን ዝንጀሮ አውርዱልኝ። ደህና አድርገን እንቀጥቅጠው"
! እኛ ዕድለ ቢሱ ዝንጀሮ ነን። ማንም ቢመጣ ያለርህራሄ ይቀጠቅጠናል። ቦታና ጊዜ ቢቀያየርም መቀጥቀጡ አይቀርልንም። ቀጥቃጩ ቢቀያየርም እኛ አንቀየርም። የዱላው ዓይነት ብዙ ነው ። የኑሮ ውድነት፣ የዋጋ ግሽበት፣ የማያልቀው የታክስና ግብር አዋጅ፣ የማያልቀው መዋጮ ....... ዕድለ ቢስ ዝንጀሮ።
እንዲህ ሲሆን የሙዝ እርሻው ባለቤት ሌሎች ገበሬዎችን አስተባብሮ ታች ያለውን ዕድለቢስ ዝንጀሮ ይዘው በዱላ ይቀጠቅጡታል። ለብዙ ጊዜ ዕድለ ቢሱ ዝንጀሮ ሲደበደብ ከረመ።
ዕድለቢሱ ዝንጀሮ ሁልጊዜ መቀጥቀጡ ሰለቸውና "ዛሬ እኔ ከላይ ሆኜ ሙዙን ወደ ታች ልወርውርልህ" አለውና ቦታ ተቀያይረው ሙዝ መቁረጥ ጀመሩ።
ዝንጀሮዎቹን ያዩት ገበሬዎች ዱላ ይዘው ደረሱባቸው። በዚህን ጊዜ ገበሬዎቹ ታች ያለውን ዕድለኛውን ዝንጀሮ ይዘው ሊቀጠቅጡት ሲሉ የሙዙ ባለቤት እንዲህ አላቸው፣
"ይሄንን ዕድለ ቢስ ዝንጀሮ አትምቱት። ሁልጊዜ እንደቀጠቀጥነው ነው። ዛሬ ግን ከላይ የተሰቀለውን ዝንጀሮ አውርዱልኝ። ደህና አድርገን እንቀጥቅጠው"
! እኛ ዕድለ ቢሱ ዝንጀሮ ነን። ማንም ቢመጣ ያለርህራሄ ይቀጠቅጠናል። ቦታና ጊዜ ቢቀያየርም መቀጥቀጡ አይቀርልንም። ቀጥቃጩ ቢቀያየርም እኛ አንቀየርም። የዱላው ዓይነት ብዙ ነው ። የኑሮ ውድነት፣ የዋጋ ግሽበት፣ የማያልቀው የታክስና ግብር አዋጅ፣ የማያልቀው መዋጮ ....... ዕድለ ቢስ ዝንጀሮ።