"የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የመውጫ ፈተና ውጤት እስከ ነገ ይለቀቃል።" - ትምህርት ሚኒስቴር
በግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የ2017 ዓ.ም አጋማሽ ዓመት የመውጫ ፈተና የወሰዱ ተፈታኞች ውጤት እስካሁን አልተለቀቀም።
ከዚህ ጋር በተያያዘ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የመውጫ ፈተና ተፈታኞች ቅሬታቸውን ለቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ አቅርበዋል።
ውጤቱ ለምን ከመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች እኩል አልተለቀቀም ስንል የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራርን ጠይቀናል።
ለመጀመሪያ ጊዜ የመውጫ ፈተና የሚወስዱ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተፈታኞችን ክፍያ የሚፈፅሙት ተቋማቱ መሆናቸውን አመራሩ ገልፀዋል።
ይሁን እንጂ ተቋማቱ ክፍያውን ባለመፈፀማቸው ውጤት መለቀቅ ላይ መዘግየት እንዳጋጠመ ኃላፊው ተናግረዋል።
አሁን ላይ ብዙዎቹ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ክፍያውን እየፈፀሙ በመሆናቸው የተፈታኞቹ ውጤት እስከ ነገ ቅዳሜ የካቲት 8/2017 ዓ.ም እንደሚለቀቅ ኃላፊው ለቲክቫህ አረጋግጠዋል።
የመውጫ ፈተናውን በግል የወሰዱ ድጋሜ ተፈታኞች ውጤትም ወደየተፈተኑበት ተቋማት ይላካል ብለዋል።
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የትምህርት በቤቴ ቴሌግራም ገፃችንን JOIN እና ሼር ያድርጉ!
https://t.me/temhert_bebete
https://t.me/temhert_bebete
በግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የ2017 ዓ.ም አጋማሽ ዓመት የመውጫ ፈተና የወሰዱ ተፈታኞች ውጤት እስካሁን አልተለቀቀም።
ከዚህ ጋር በተያያዘ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የመውጫ ፈተና ተፈታኞች ቅሬታቸውን ለቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ አቅርበዋል።
ውጤቱ ለምን ከመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች እኩል አልተለቀቀም ስንል የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራርን ጠይቀናል።
ለመጀመሪያ ጊዜ የመውጫ ፈተና የሚወስዱ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተፈታኞችን ክፍያ የሚፈፅሙት ተቋማቱ መሆናቸውን አመራሩ ገልፀዋል።
ይሁን እንጂ ተቋማቱ ክፍያውን ባለመፈፀማቸው ውጤት መለቀቅ ላይ መዘግየት እንዳጋጠመ ኃላፊው ተናግረዋል።
አሁን ላይ ብዙዎቹ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ክፍያውን እየፈፀሙ በመሆናቸው የተፈታኞቹ ውጤት እስከ ነገ ቅዳሜ የካቲት 8/2017 ዓ.ም እንደሚለቀቅ ኃላፊው ለቲክቫህ አረጋግጠዋል።
የመውጫ ፈተናውን በግል የወሰዱ ድጋሜ ተፈታኞች ውጤትም ወደየተፈተኑበት ተቋማት ይላካል ብለዋል።
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የትምህርት በቤቴ ቴሌግራም ገፃችንን JOIN እና ሼር ያድርጉ!
https://t.me/temhert_bebete
https://t.me/temhert_bebete