📌ደራሲ ስብሐት በሞት ከተለየን ዛሬ 13 ዓመት ሆነው!!
"እኔ የምሞተው በሚወዱኝ ሰዎች ልብ ውስጥ መረሳት ስጀምር ነው" ስብሐት ገ/እግዚአብሔር
ስብሐት ከተለየን ዛሬ 13 ዓመታት ተቆጠሩ።ይህንን ቀን አስታውሶ ስለ ደራሲ ስብሃት አንድም ሰው ሲጽፍ አላጋጠመኝም።በእርግጥም ጋሽ ስብሃት በአንድ ወቅት ስለ"ሞት" እንዲህ ብሎ ነበር"እኔ የምሞተው በሚወዱኝ ሰዎች ልብ ውስጥ መረሳት ስጀምር ነው። ሥጋዬ ሞተ ብለሽ አትዘኝ። በልብሽ ረስተሽኝ በአፀደ ሥጋ ከምንከላወስ ሞቼ ብታስታውስሺኝ ለኔ ምርጫዬ ነው"።
2."እኛ ሟች ነን።ከመሞታችን በፊት ግን ሟች አምላክ አንሁን ፣ ሞትን እንቅደመው ።ተዘጋጀህም አልተዘጋጀህም ጉዳዩ አንድ ቀን ያበቃል።ከእንግዲህ የምትወጣ ፀሐይ አትኖርም።ደቂቃዎችም ፣ ቀኖችም የሉም።ጢምህ ፣ አትንኩኝ ባይነትህ፣ ኩምታዎችህ እና ቅናትህ ጨርሶ ይጠፋሉ።እንደዚሁም ተስፋዎች፣ ፅኑ ፍላጎቶችህ፣ እቅዶችህ፣ የስራ ዝርዝሮችህ ጊዜ ያለፈባቸው ይሆናሉ"።
3. "ሞት ብዙ ጊዜ fiction ነው። ብዙ ጊዜ ተረት ነው። ምክኒያቱስ እስከአሁን እኔ ይህውልህ ስንት ጊዜ ስለ ሞት ሳስብ፣ስፅፍ 74ዓመት ኖሪያለው ውሸት ነበር እስካሁን ድረስ። ሁልጊዜ ሞት ውሸት ነው። ስትሞት ብቻ ነው እውነት የሚሆነው ከዛ በኃላ ደሞ አታውቅም ከሞትክ በኃላ ምን እንዳለ።ሞት እኮ አንዲት ደቂቃ ናት። እንደ መወለድ፤እንዲህ እናበዛታለን ለተረት በተለይ ለኛ እንጀራ ተመቸ ይኸውልህ ስም ዘራን፤ ከሞትኩ በኃላ የሚበቅል ስም። አሁን ከሞትኩ፣ መሞቴን እንጃ እንጂ ከሞትኩ ምኔ ነው እዚህ ያለው? ለሚቀሩት ነው ለእናንተ።"
ስብሐት ገብረ እግዚአብሔር
(ከሚያዚያ 27 1928 እስከ የካቲት 12 2004)
ከጋሽ ስብሃት መጻህፍት የትኛውን ትወዳላችሁ?
ናቲ ማናዬ
"እኔ የምሞተው በሚወዱኝ ሰዎች ልብ ውስጥ መረሳት ስጀምር ነው" ስብሐት ገ/እግዚአብሔር
ስብሐት ከተለየን ዛሬ 13 ዓመታት ተቆጠሩ።ይህንን ቀን አስታውሶ ስለ ደራሲ ስብሃት አንድም ሰው ሲጽፍ አላጋጠመኝም።በእርግጥም ጋሽ ስብሃት በአንድ ወቅት ስለ"ሞት" እንዲህ ብሎ ነበር"እኔ የምሞተው በሚወዱኝ ሰዎች ልብ ውስጥ መረሳት ስጀምር ነው። ሥጋዬ ሞተ ብለሽ አትዘኝ። በልብሽ ረስተሽኝ በአፀደ ሥጋ ከምንከላወስ ሞቼ ብታስታውስሺኝ ለኔ ምርጫዬ ነው"።
2."እኛ ሟች ነን።ከመሞታችን በፊት ግን ሟች አምላክ አንሁን ፣ ሞትን እንቅደመው ።ተዘጋጀህም አልተዘጋጀህም ጉዳዩ አንድ ቀን ያበቃል።ከእንግዲህ የምትወጣ ፀሐይ አትኖርም።ደቂቃዎችም ፣ ቀኖችም የሉም።ጢምህ ፣ አትንኩኝ ባይነትህ፣ ኩምታዎችህ እና ቅናትህ ጨርሶ ይጠፋሉ።እንደዚሁም ተስፋዎች፣ ፅኑ ፍላጎቶችህ፣ እቅዶችህ፣ የስራ ዝርዝሮችህ ጊዜ ያለፈባቸው ይሆናሉ"።
3. "ሞት ብዙ ጊዜ fiction ነው። ብዙ ጊዜ ተረት ነው። ምክኒያቱስ እስከአሁን እኔ ይህውልህ ስንት ጊዜ ስለ ሞት ሳስብ፣ስፅፍ 74ዓመት ኖሪያለው ውሸት ነበር እስካሁን ድረስ። ሁልጊዜ ሞት ውሸት ነው። ስትሞት ብቻ ነው እውነት የሚሆነው ከዛ በኃላ ደሞ አታውቅም ከሞትክ በኃላ ምን እንዳለ።ሞት እኮ አንዲት ደቂቃ ናት። እንደ መወለድ፤እንዲህ እናበዛታለን ለተረት በተለይ ለኛ እንጀራ ተመቸ ይኸውልህ ስም ዘራን፤ ከሞትኩ በኃላ የሚበቅል ስም። አሁን ከሞትኩ፣ መሞቴን እንጃ እንጂ ከሞትኩ ምኔ ነው እዚህ ያለው? ለሚቀሩት ነው ለእናንተ።"
ስብሐት ገብረ እግዚአብሔር
(ከሚያዚያ 27 1928 እስከ የካቲት 12 2004)
ከጋሽ ስብሃት መጻህፍት የትኛውን ትወዳላችሁ?
ናቲ ማናዬ