" ከዚህ በኋላ ምን እንደሚፈጠር አላውቅም፤ ስልክ መደወልም ሁሉም ነገር ያስፈራል " - ነሒማ ጀማል
ከጥቂት ሳምንታት በፊት በሊቢያ " ለባርነት ጨረታ ቀርባ " የነበረችው ኢትዮጵያዊቷ ነሒማ ጀማል ለአጋቾቿ 700 ሺህ ብር ተከፍሎ ነጻ መውጣቷን ተናግራለች።
በፎቶዎች እና በቪዲዮዎች ላይ አፏ በጨርቅ ተለጉሞ ስቃይ ሲደርስባት ትታይ የነበረችው ነሒማ በቤተሰቧ አማካይነት ገንዘብ ከኢትዮጵያ ተሰባስቦ ከተላከ በኋላ ከሁለት ቀናት በፊት አጋቾቿ ወደ ከተማ አምጥተው እንደለቀቋቸው ለቢቢሲ ተናግራለች።
ታግታ ከነበረችበት ስፍራ እሷን ጨምሮ በርካታ ሰዎች ቢኖሩም የተለቀቁት ገንዘብ የተከፈለላቸው " ውስን ሰዎች ነበሩ " ብላለች።
ነሒማ በአሁኑ ወቅት በሊቢያ የምትገኝ ሲሆን " ድካም እና ህመም ላይ " እንደሆነች ገልጻለች።
" ከዚህ በኋላ ምን እንደሚፈጠር አላውቅም፤ ስልክ መደወልም ሁሉም ነገር ያስፈራል " ስትል ጭንቀት ላይ እንደሆነች እና ማውራት እንደሚከብዳት ተናግራለች።
መረጃው የቢቢሲ አማርኛው አገልግሎት ነው።
@tikvahethiopia
ከጥቂት ሳምንታት በፊት በሊቢያ " ለባርነት ጨረታ ቀርባ " የነበረችው ኢትዮጵያዊቷ ነሒማ ጀማል ለአጋቾቿ 700 ሺህ ብር ተከፍሎ ነጻ መውጣቷን ተናግራለች።
በፎቶዎች እና በቪዲዮዎች ላይ አፏ በጨርቅ ተለጉሞ ስቃይ ሲደርስባት ትታይ የነበረችው ነሒማ በቤተሰቧ አማካይነት ገንዘብ ከኢትዮጵያ ተሰባስቦ ከተላከ በኋላ ከሁለት ቀናት በፊት አጋቾቿ ወደ ከተማ አምጥተው እንደለቀቋቸው ለቢቢሲ ተናግራለች።
ታግታ ከነበረችበት ስፍራ እሷን ጨምሮ በርካታ ሰዎች ቢኖሩም የተለቀቁት ገንዘብ የተከፈለላቸው " ውስን ሰዎች ነበሩ " ብላለች።
ነሒማ በአሁኑ ወቅት በሊቢያ የምትገኝ ሲሆን " ድካም እና ህመም ላይ " እንደሆነች ገልጻለች።
" ከዚህ በኋላ ምን እንደሚፈጠር አላውቅም፤ ስልክ መደወልም ሁሉም ነገር ያስፈራል " ስትል ጭንቀት ላይ እንደሆነች እና ማውራት እንደሚከብዳት ተናግራለች።
መረጃው የቢቢሲ አማርኛው አገልግሎት ነው።
@tikvahethiopia