ዛሬ የካቲት 19 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 9:33 ሰዓት ላይ በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ-ከተማ ወረዳ 2 ካራ ቆሬ በተለምዶ ቢቂላ መናፈሻ እየተባለ በሚጠራዉ አካባቢ ለፍራሽ መስሪያ የሚሆኑ ግብአቶች በተከማቹበት መጋዘን ላይ የእሳት አደጋ ተከስቷል።
የእሳት አደጋዉን ሙሉ በሙሉ ለመቆጣጠር የአደጋ ጊዜ ሰራተኞችና የጸጥታ አካላት እንዲሁም የአካባቢዉ ህብረተሰብ በአደረጉት ርብርብ እሳቱ በአቅራቢያዉ ወዳለዉ መስጂድ እና ሌሎች መኖሪያና ንግድ ቤቶች እንዳይዛመት ማድረግ መቻሉን የእሳትና አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን አሳውቋል።
በእሳት አደጋዉ በሰዉ ላይ የደረሰ ጉዳት የለም።
@tikvahethmagazine
የእሳት አደጋዉን ሙሉ በሙሉ ለመቆጣጠር የአደጋ ጊዜ ሰራተኞችና የጸጥታ አካላት እንዲሁም የአካባቢዉ ህብረተሰብ በአደረጉት ርብርብ እሳቱ በአቅራቢያዉ ወዳለዉ መስጂድ እና ሌሎች መኖሪያና ንግድ ቤቶች እንዳይዛመት ማድረግ መቻሉን የእሳትና አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን አሳውቋል።
በእሳት አደጋዉ በሰዉ ላይ የደረሰ ጉዳት የለም።
@tikvahethmagazine