“ የሊቢያ ፖሊሶች ተጨዋቾችን ደብድበዋል “ የቤኒን አሰልጣኝ
የቤኒን ብሔራዊ ቡድን ከሊቢያ ጋር በነበረው የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ የምድብ ጨዋታ ወቅት ጥቃት እንደደረሰበት የቡድኑ አሰልጣኝ ጌርኖት ሮህር ተናግረዋል።
ብሔራዊ ቡድኑ በሊቢያ በነበረው ቆይታ ባልተገባ መልኩ ከመልበሻ ቤት እንዳይወጣ ተደርጎ እንደነበር ተዘግቧል።
የቡድኑ አሰልጣኝ ጌርኖት ሮህር ለመገናኛ ብዙሃን በሰጡት ቃል የሊቢያ ፖሊሶች የቤኒን ተጨዋቾች እና አሰልጣኝን በዱላ መደብደባቸውን አስታውቀዋል።
የቢኒን ብሔራዊ ቡድን ከሊቢያ ጋር ያደረገውን ጨዋታ አቻ መውጣቱን ተከትሎ ለአፍሪካ ዋንጫ ማለፉን ማረጋገጡ አይዘነጋም።
ሊቢያ በቅርቡ በናይጄሪያ ብሔራዊ ቡድን ላይ ባደረጉት ያልተገባ ድርጊት በፎርፌ ሶስት ነጥብ እና ሶስት ጎል እንደተሰጠባቸው ይታወሳል።
@tikvahethsport @kidusyoftahe
የቤኒን ብሔራዊ ቡድን ከሊቢያ ጋር በነበረው የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ የምድብ ጨዋታ ወቅት ጥቃት እንደደረሰበት የቡድኑ አሰልጣኝ ጌርኖት ሮህር ተናግረዋል።
ብሔራዊ ቡድኑ በሊቢያ በነበረው ቆይታ ባልተገባ መልኩ ከመልበሻ ቤት እንዳይወጣ ተደርጎ እንደነበር ተዘግቧል።
የቡድኑ አሰልጣኝ ጌርኖት ሮህር ለመገናኛ ብዙሃን በሰጡት ቃል የሊቢያ ፖሊሶች የቤኒን ተጨዋቾች እና አሰልጣኝን በዱላ መደብደባቸውን አስታውቀዋል።
የቢኒን ብሔራዊ ቡድን ከሊቢያ ጋር ያደረገውን ጨዋታ አቻ መውጣቱን ተከትሎ ለአፍሪካ ዋንጫ ማለፉን ማረጋገጡ አይዘነጋም።
ሊቢያ በቅርቡ በናይጄሪያ ብሔራዊ ቡድን ላይ ባደረጉት ያልተገባ ድርጊት በፎርፌ ሶስት ነጥብ እና ሶስት ጎል እንደተሰጠባቸው ይታወሳል።
@tikvahethsport @kidusyoftahe