የት ላይ ነህ?
ለትግሉ አስተዋጽኦ እያደረክ ነው ወይስ ትግሉን እየጎተትክ? በሚያሰባስብና ህብረት በሚፈጥር ተግባር ላይ ነህ ወይስ በከፋፋይ አጀንዳ ተጠምደሃል? ቤትህ ወይም ካፌ ውስጥ ወይም ቢሮ ተቀምጠህ በማህበራዊ ሚዲያ እያዋጋህ ነው ወይስ ለትግሉ በሚጠቅም ተግባር ላይ ተሰማርተሃል? “የሎጅስቲክ ድጋፍ እንዳናደርግ አልተባበር አሉ! ድጋፍ የማድረግ ፍላጎት አለኝ ግን መንገዱን አጣሁት” ወዘተ ወዘተ እያልክ ምክንያት እየደረደርክና ራስክን እየሸወድክ ነው ወይስ በምትችለው መንገድ ድጋፍ እያደረክ? “የትግሉ መሰናክሎች የዚህ አካባቢ ሰዎች ናቸው፣ የትግሉ ነቀርሳ እከሌ ነው” ምንትስ ምንትስ እያልክ በማይጠቅም እንቶ ፈንቶ ላይ ተሰማርተሃል ወይስ የምትችለውን እያደረክ ነው? ችግሩ በእኔና በቤተሰቤ ላይ ካልደረሰ ችግር የለም ብለህ ተቀምጠሃል ወይስ የወገኔ ጥቃት ጥቃቴ ነው ብለህ በምትችለው መንገድ ትግሉን እየደገፍክ ነው? ወገናዊነቴ ለህዝቤ ነው ብለህ ትግሉንና ታጋዮችን እየደገፍክ ነው ወይስ የግለሰቦች ጭፍራ ነህ? ሶፋ ላይ ተጋድመህ የድል ዜና እየቃረምክ ነው ወይስ ቲክቶክ ላይ ተጥደህ ከንቱ ወሬ እያግበሰበስክ? የት ላይ ነህ? ምን ላይ ነሽ?
የገባንበትን የሕልውና ትግል ከማሸነፍ ውጪ አማራጭ የለም፡፡ ከዚያው ውጪ ያለው አማራጭ (አማራጭ ከተባለ) ሞት ነው፡፡ ውርደት ነው፡፡ ባርነት ነው!
ስለሆነም ለዚህ ትግል ሁላችንም በምንችለው መንገድ ሁሉ አስተዋጽኦ ማድረግ አለብን፡፡ ጦርነት በጣም ውድ ተግባር (expensive venture) ነው፡፡ ብዙ ገንዘብ ይጠይቃል፡፡ ብዙ ሀብት ይጠይቃል፡፡ ከፍተኛ ሎጂስቲክስ ያስፈልገዋል፡፡ ጦርነትን በድል ለመወጣት ወሳኝ ከሆኑ ጉዳዮች አንዱ ሎጅስቲክስ ነው፡፡ ስለሆነም ሁላችንም የምንችለውን አስተዋጽኦ ማድረግ ይጠበቅብናል፡፡
ዝም የተሰኙት ብዙሃን (the silenced majority) ትግሉን መቀላቀል አለባቸው፡፡ በሚችሉት መንገድ ሁሉ አስተዋጽኦ ማድረግ አለባቸው፡፡ እነ እከሌ ይሰሩታል ብሎ ነገር የለም፡፡ አንተ ያልሰራኸውን ሌላው እንዲሰራው ለምን ትጠብቃለህ? የእነ እከሌ ወንድሞች ይዋጉ ብሎ ነገር የለም፡፡ የአንተ ወንድም መስዋዕትነት ለመክፈል የፈራውን ሌላው ለምን ይከፍላል? ምክንያት መደርደር አያስፈልግም፡፡ መፍትሄው አንድ ብቻ ነው፡፡ የትግሉ አካል መሆን፡፡ ጨርቄን ማቄንን ማስወገድ፡፡ በፈተና መፅናት!!!
የአማራ ብሄርተኝነት ይለምልም!!!
ለትግሉ አስተዋጽኦ እያደረክ ነው ወይስ ትግሉን እየጎተትክ? በሚያሰባስብና ህብረት በሚፈጥር ተግባር ላይ ነህ ወይስ በከፋፋይ አጀንዳ ተጠምደሃል? ቤትህ ወይም ካፌ ውስጥ ወይም ቢሮ ተቀምጠህ በማህበራዊ ሚዲያ እያዋጋህ ነው ወይስ ለትግሉ በሚጠቅም ተግባር ላይ ተሰማርተሃል? “የሎጅስቲክ ድጋፍ እንዳናደርግ አልተባበር አሉ! ድጋፍ የማድረግ ፍላጎት አለኝ ግን መንገዱን አጣሁት” ወዘተ ወዘተ እያልክ ምክንያት እየደረደርክና ራስክን እየሸወድክ ነው ወይስ በምትችለው መንገድ ድጋፍ እያደረክ? “የትግሉ መሰናክሎች የዚህ አካባቢ ሰዎች ናቸው፣ የትግሉ ነቀርሳ እከሌ ነው” ምንትስ ምንትስ እያልክ በማይጠቅም እንቶ ፈንቶ ላይ ተሰማርተሃል ወይስ የምትችለውን እያደረክ ነው? ችግሩ በእኔና በቤተሰቤ ላይ ካልደረሰ ችግር የለም ብለህ ተቀምጠሃል ወይስ የወገኔ ጥቃት ጥቃቴ ነው ብለህ በምትችለው መንገድ ትግሉን እየደገፍክ ነው? ወገናዊነቴ ለህዝቤ ነው ብለህ ትግሉንና ታጋዮችን እየደገፍክ ነው ወይስ የግለሰቦች ጭፍራ ነህ? ሶፋ ላይ ተጋድመህ የድል ዜና እየቃረምክ ነው ወይስ ቲክቶክ ላይ ተጥደህ ከንቱ ወሬ እያግበሰበስክ? የት ላይ ነህ? ምን ላይ ነሽ?
የገባንበትን የሕልውና ትግል ከማሸነፍ ውጪ አማራጭ የለም፡፡ ከዚያው ውጪ ያለው አማራጭ (አማራጭ ከተባለ) ሞት ነው፡፡ ውርደት ነው፡፡ ባርነት ነው!
ስለሆነም ለዚህ ትግል ሁላችንም በምንችለው መንገድ ሁሉ አስተዋጽኦ ማድረግ አለብን፡፡ ጦርነት በጣም ውድ ተግባር (expensive venture) ነው፡፡ ብዙ ገንዘብ ይጠይቃል፡፡ ብዙ ሀብት ይጠይቃል፡፡ ከፍተኛ ሎጂስቲክስ ያስፈልገዋል፡፡ ጦርነትን በድል ለመወጣት ወሳኝ ከሆኑ ጉዳዮች አንዱ ሎጅስቲክስ ነው፡፡ ስለሆነም ሁላችንም የምንችለውን አስተዋጽኦ ማድረግ ይጠበቅብናል፡፡
ዝም የተሰኙት ብዙሃን (the silenced majority) ትግሉን መቀላቀል አለባቸው፡፡ በሚችሉት መንገድ ሁሉ አስተዋጽኦ ማድረግ አለባቸው፡፡ እነ እከሌ ይሰሩታል ብሎ ነገር የለም፡፡ አንተ ያልሰራኸውን ሌላው እንዲሰራው ለምን ትጠብቃለህ? የእነ እከሌ ወንድሞች ይዋጉ ብሎ ነገር የለም፡፡ የአንተ ወንድም መስዋዕትነት ለመክፈል የፈራውን ሌላው ለምን ይከፍላል? ምክንያት መደርደር አያስፈልግም፡፡ መፍትሄው አንድ ብቻ ነው፡፡ የትግሉ አካል መሆን፡፡ ጨርቄን ማቄንን ማስወገድ፡፡ በፈተና መፅናት!!!
የአማራ ብሄርተኝነት ይለምልም!!!