እርግማን የለብንም!
ለሁሉም ነገር ባህልን ተጠያቂ የማድረግ (cultural determinism) ነገር አለ፡፡ ይህ በተለይ በእኛ ዘንድ በስፋት የሚስተዋል ችግር ነው፡፡ “ተረግመናል፤ አንድ መሆን ያልቻልነው ስለተረገምን ነው፣ የትብብር ባህል ስለሌለን ነው፣ አብሮ መብላት እንጅ አብሮ መስራት አንችልበትም” ወዘተ ይባላል፡፡ ከዚህም አልፎ “መቼም አንድ ልንሆን አንችልም!” እስከማለት ይኬዳል፡፡
መሰረተ-ቢስ አመለካከት ነው፡፡ አንደኛ አላዘመነውም እንጅ ከፍተኛ የሆነ የትብብር ባህል ያለን ህዝብ ነን፡፡ ይህን ለመገንዘብ ብዙሃኑን ህዝባችንን (አርሶ አደሩን) ማየት ነው፡፡ ያለ ደቦ፣ ያለ ወንፈል፣ ያለ ወበራ፣ ያለ ደባይት ወዘተ የሚሰራ አርሶ አደር አለ ወይ? አርሶ አደራችን ከፍተኛ የሆነ የትብብር ባህል ያለው ነው፡፡ በእርስ በርስ መደጋገፍና መረዳዳት የታወቀ ህዝብ ነው፡፡ በየአካባቢው ብዙ ዘመናት ያስቆጠሩ የአብሮ አደግ ማህበራት ያሉ መሆናቸውን መዘንጋት አይገባም፡፡ ስለሆነም ካሳደግነው እርሾው አለ፡፡
በሌላ በኩል፣ በዘመናዊው የድርጅት ግንባታ ታሪካችን ውስጥም ቢሆን፣ እስካሁን ጥሩ የትብብር መንፈስ ፈጥረን ጠንካራ ድርጅቶችን መገንባት አልቻልንም ማለት ዛሬ መገንባት አንችልም ማለት አይደለም፡፡ ትላንት አልተባበርንም ማለት ዛሬ መተባበር አንችልም ማለት አይደለም፡፡ ትላንት ጠንካራ የፖለቲካ፣ የሲቪክና የሚዲያ ተቋማትን መገንባት አልቻልንም ማለት ዛሬ መገንባት አንችልም ማለት አይደለም፡፡ ባህል የሚቀየር ነገር መሆኑ ይግባን፡፡ ባህል የሚሻሻል ነገር መሆኑን እንረዳ፡፡
ስለዚህ ስለ እርግማን የሚወራውን ከንቱ ትንተና እንተወው፡፡ ውሃ አይቋጥርም፡፡ የእንዲህ አይነት አመለካከት እስረኛ አንሁን፡፡ የሚበጀው ለተቋም ግንባታ የሚረዱ እሴቶችን መኮትኮት ነው፡፡ የሚበጀው ከሌሎች ብቻ ሳይሆን ከራሳችንም (ከውድቀታችንም ከስኬታችንም) መማር ነው፡፡ ትምህርት ቀስሞ ወደ ተቋም ግንባታ መግባት ነው፡፡
ጊዜው የስራ ነው!
የአማራ ብሄርተኝነት ይለምልም!!!
ለሁሉም ነገር ባህልን ተጠያቂ የማድረግ (cultural determinism) ነገር አለ፡፡ ይህ በተለይ በእኛ ዘንድ በስፋት የሚስተዋል ችግር ነው፡፡ “ተረግመናል፤ አንድ መሆን ያልቻልነው ስለተረገምን ነው፣ የትብብር ባህል ስለሌለን ነው፣ አብሮ መብላት እንጅ አብሮ መስራት አንችልበትም” ወዘተ ይባላል፡፡ ከዚህም አልፎ “መቼም አንድ ልንሆን አንችልም!” እስከማለት ይኬዳል፡፡
መሰረተ-ቢስ አመለካከት ነው፡፡ አንደኛ አላዘመነውም እንጅ ከፍተኛ የሆነ የትብብር ባህል ያለን ህዝብ ነን፡፡ ይህን ለመገንዘብ ብዙሃኑን ህዝባችንን (አርሶ አደሩን) ማየት ነው፡፡ ያለ ደቦ፣ ያለ ወንፈል፣ ያለ ወበራ፣ ያለ ደባይት ወዘተ የሚሰራ አርሶ አደር አለ ወይ? አርሶ አደራችን ከፍተኛ የሆነ የትብብር ባህል ያለው ነው፡፡ በእርስ በርስ መደጋገፍና መረዳዳት የታወቀ ህዝብ ነው፡፡ በየአካባቢው ብዙ ዘመናት ያስቆጠሩ የአብሮ አደግ ማህበራት ያሉ መሆናቸውን መዘንጋት አይገባም፡፡ ስለሆነም ካሳደግነው እርሾው አለ፡፡
በሌላ በኩል፣ በዘመናዊው የድርጅት ግንባታ ታሪካችን ውስጥም ቢሆን፣ እስካሁን ጥሩ የትብብር መንፈስ ፈጥረን ጠንካራ ድርጅቶችን መገንባት አልቻልንም ማለት ዛሬ መገንባት አንችልም ማለት አይደለም፡፡ ትላንት አልተባበርንም ማለት ዛሬ መተባበር አንችልም ማለት አይደለም፡፡ ትላንት ጠንካራ የፖለቲካ፣ የሲቪክና የሚዲያ ተቋማትን መገንባት አልቻልንም ማለት ዛሬ መገንባት አንችልም ማለት አይደለም፡፡ ባህል የሚቀየር ነገር መሆኑ ይግባን፡፡ ባህል የሚሻሻል ነገር መሆኑን እንረዳ፡፡
ስለዚህ ስለ እርግማን የሚወራውን ከንቱ ትንተና እንተወው፡፡ ውሃ አይቋጥርም፡፡ የእንዲህ አይነት አመለካከት እስረኛ አንሁን፡፡ የሚበጀው ለተቋም ግንባታ የሚረዱ እሴቶችን መኮትኮት ነው፡፡ የሚበጀው ከሌሎች ብቻ ሳይሆን ከራሳችንም (ከውድቀታችንም ከስኬታችንም) መማር ነው፡፡ ትምህርት ቀስሞ ወደ ተቋም ግንባታ መግባት ነው፡፡
ጊዜው የስራ ነው!
የአማራ ብሄርተኝነት ይለምልም!!!