ድሮን እና ትግላችን!
ፋሽስታዊው ቡድን የፋኖን ውጊያ መቋቋም አልቻለም፡፡ ከሶስት ቀናት ወደ ሶስት ወራት፣ ከሶስት ወራት ወደ ስድስት ወር እያስረዘሙ አርበኛነቱን ለማሸነፍ ባለ በሌለ አቅማቸው ዘመቱ፡፡ ሁለት ጊዜ የአስቸኳይ ጊዜ አወጁ፡፡ በመላው ኢትዮጵያ ያሉ አማራዎችን ማሰር፣ መዝረፍና ማሸማቀቅ ስራቸው ሆነ፡፡ ይህ ሁሉ ተደርጎም ፋኖን ማሸነፍ አልተቻለም፡፡ ማሸነፍም ፈፅሞ አይቻልም፡፡ የፋኖ ትግል የመላው አማራ ትግል ነውና፡፡ ትግላችን የእውነትና የፍትህ ነውና፡፡
ያሰበው ያልተሳካለት ፋሽስታዊ ቡድን የድሮን ጭፍጨፋው ቀጥሎበታል፡፡ ንጹሃንን እየጨፈጨፈ ነው፡፡ የአማራን መሰረተ ልማት እያወደመ ነው፡፡ አላማው አማራን ማደህየት ነው፡፡ አማራን ማንበርከክ ነው፡፡ አላማው አማራን መበቀል ነው፡፡
ጠላት ጠላት ነውና ስራውን እየሰራ ነው፡፡ የእኛን ትግል የሚጠቅም ስራ የሚጠበቀው ከእኛው ከራሳችን ነው፡፡ ልብ እንበል፤ አንድ ችግር በአንድ ምክንያት እንደማይመጣው ሁሉ መፍትሄውም አንድ አይደለም፡፡ ስለሆነም የተለያዩና ተመጋጋቢ ስትራቴጂዎችን ነድፈን መንቀሳቀስ ይገባናል፡-
1/ የቴክኖሎጂና የኢንጅነሪንግ ምሩቃንና ባለሙያዎች ትግሉን እንዲቀላቀሉ ሰፊ ስራ እንስራ፡፡ በፀረ ድሮን ረገድ ከፍተኛ የሆነ ስራ መስራት ይጠበቅብናል፡፡ ሌሎች የነፃነት ታጋዮች እንዴት እንዲህ አይነቱን ጥቃት መቋቋም እንደቻሉ ልምድ እንቅሰም፡፡ ጊዜውና ሁኔታው የሚጠይቀውን የቴክኖሎጂ አቅም እንገንባ፡፡
2/ አላስፈላጊ መሰባሰብን እናስወግድ፡፡ በተለይ ከሞባይል ስልክ ጋር የተያያዘ ሁኔታችን መልክ መያዝ ያለበት ነው፡፡ “ሳይደግስ አይጣላም” ነውና ይህ ፈተና አርበኛውን ከስልክ የሚያላቅቀው ይሆናል፡፡ መላቀቅም ይገባዋል፡፡ የመገናኛ ሬዲዮ መያዝ የሚገባቸው በስርአት ተለይተውና የእነሱ ደህንነት ተጠብቆ ሌላው ታጋይ ከስልክ መላቀቅ ይገባዋል፡፡ ስልክ በመያዙ የሚያጣው እንጅ የሚያገኘው ነገር የለም፡፡
3/ እንደተሳካላቸው ሌሎች የሽምቅ ተዋጊ ድርጅቶች እኛም ጠላት በማይችለው ሁኔታና ጊዜ እንንቀሳቀስ፡፡ ብዙዎቹ የሽምቅ ተዋጊ ድርጅቶች በማታ፣ በክረምት እና ጠላት በማያስበው ጊዜና ሁኔታ የሚያጠቁት ራሳቸውን ከጥቃት ለመከላከል ጭምር ነው፡፡ ይህን እውነታ ሃቅ የፋኖ አርበኞቻችን ያጡታል ብለን አናምንም፡፡ ለማስታወስ ያክል ብቻ ነው፡፡
4/ በዲያስፖራ ያሉ አማራዎች የፋሽቱን በድሮን የታገዘ ጭፍጨፋ ሳንሰላች ሁልጊዜም በሰልፍና በሌላውም የተቃውሞ መንገድ ጠላትን የማጋለጥ ስራ መስራት ይገባቸዋል፡፡ የአብይን በደም የጨቀዬ ማንነት በአለም አደባባይ እናጋልጠው፡፡ ተስፋ ሳንቆርጥ ሁልጊዜም ለውጥ እስከምናመጣ እንታገል፡፡ በዚህ ረገድ የትግራይ ዲያስፖራ የሰራውን ተአምራዊ ስራ ማስታወስ ይገባል፡፡
5/ ማህበራዊ ሚዲያውን (በተለይም ትዊተር ወዘተ) በድንብ በመጠቀም የፋሽስቱን ቡድን ገፅታ እርቃኑን እናስቀረው፡፡ ሁልጊዜም የተቀናጀ ዘመቻ እናካሂድ፡፡ ይህን ዘመቻ በተለይ ጋዜጠኞች በደንብ ሊመሩት ይችላሉ፡፡ ይገባልም፡፡
እነዚህንና ሌሎችንም የተቀናጁ ስትራቴጂዎች ተመጋጋቢ በሆነ መንገድ በመተግበር አገዛዙን እርቃኑን ማስቀረትና ባለድል መሆን ይገባናል፡፡ ይህን ጦርነት ማሸነፍ ምርጫ ሳይሆን ግዴታ ነው!
ጊዜው የስራ ነው!
የአማራ ብሄርተኝነት ይለምልም!!!
ፋሽስታዊው ቡድን የፋኖን ውጊያ መቋቋም አልቻለም፡፡ ከሶስት ቀናት ወደ ሶስት ወራት፣ ከሶስት ወራት ወደ ስድስት ወር እያስረዘሙ አርበኛነቱን ለማሸነፍ ባለ በሌለ አቅማቸው ዘመቱ፡፡ ሁለት ጊዜ የአስቸኳይ ጊዜ አወጁ፡፡ በመላው ኢትዮጵያ ያሉ አማራዎችን ማሰር፣ መዝረፍና ማሸማቀቅ ስራቸው ሆነ፡፡ ይህ ሁሉ ተደርጎም ፋኖን ማሸነፍ አልተቻለም፡፡ ማሸነፍም ፈፅሞ አይቻልም፡፡ የፋኖ ትግል የመላው አማራ ትግል ነውና፡፡ ትግላችን የእውነትና የፍትህ ነውና፡፡
ያሰበው ያልተሳካለት ፋሽስታዊ ቡድን የድሮን ጭፍጨፋው ቀጥሎበታል፡፡ ንጹሃንን እየጨፈጨፈ ነው፡፡ የአማራን መሰረተ ልማት እያወደመ ነው፡፡ አላማው አማራን ማደህየት ነው፡፡ አማራን ማንበርከክ ነው፡፡ አላማው አማራን መበቀል ነው፡፡
ጠላት ጠላት ነውና ስራውን እየሰራ ነው፡፡ የእኛን ትግል የሚጠቅም ስራ የሚጠበቀው ከእኛው ከራሳችን ነው፡፡ ልብ እንበል፤ አንድ ችግር በአንድ ምክንያት እንደማይመጣው ሁሉ መፍትሄውም አንድ አይደለም፡፡ ስለሆነም የተለያዩና ተመጋጋቢ ስትራቴጂዎችን ነድፈን መንቀሳቀስ ይገባናል፡-
1/ የቴክኖሎጂና የኢንጅነሪንግ ምሩቃንና ባለሙያዎች ትግሉን እንዲቀላቀሉ ሰፊ ስራ እንስራ፡፡ በፀረ ድሮን ረገድ ከፍተኛ የሆነ ስራ መስራት ይጠበቅብናል፡፡ ሌሎች የነፃነት ታጋዮች እንዴት እንዲህ አይነቱን ጥቃት መቋቋም እንደቻሉ ልምድ እንቅሰም፡፡ ጊዜውና ሁኔታው የሚጠይቀውን የቴክኖሎጂ አቅም እንገንባ፡፡
2/ አላስፈላጊ መሰባሰብን እናስወግድ፡፡ በተለይ ከሞባይል ስልክ ጋር የተያያዘ ሁኔታችን መልክ መያዝ ያለበት ነው፡፡ “ሳይደግስ አይጣላም” ነውና ይህ ፈተና አርበኛውን ከስልክ የሚያላቅቀው ይሆናል፡፡ መላቀቅም ይገባዋል፡፡ የመገናኛ ሬዲዮ መያዝ የሚገባቸው በስርአት ተለይተውና የእነሱ ደህንነት ተጠብቆ ሌላው ታጋይ ከስልክ መላቀቅ ይገባዋል፡፡ ስልክ በመያዙ የሚያጣው እንጅ የሚያገኘው ነገር የለም፡፡
3/ እንደተሳካላቸው ሌሎች የሽምቅ ተዋጊ ድርጅቶች እኛም ጠላት በማይችለው ሁኔታና ጊዜ እንንቀሳቀስ፡፡ ብዙዎቹ የሽምቅ ተዋጊ ድርጅቶች በማታ፣ በክረምት እና ጠላት በማያስበው ጊዜና ሁኔታ የሚያጠቁት ራሳቸውን ከጥቃት ለመከላከል ጭምር ነው፡፡ ይህን እውነታ ሃቅ የፋኖ አርበኞቻችን ያጡታል ብለን አናምንም፡፡ ለማስታወስ ያክል ብቻ ነው፡፡
4/ በዲያስፖራ ያሉ አማራዎች የፋሽቱን በድሮን የታገዘ ጭፍጨፋ ሳንሰላች ሁልጊዜም በሰልፍና በሌላውም የተቃውሞ መንገድ ጠላትን የማጋለጥ ስራ መስራት ይገባቸዋል፡፡ የአብይን በደም የጨቀዬ ማንነት በአለም አደባባይ እናጋልጠው፡፡ ተስፋ ሳንቆርጥ ሁልጊዜም ለውጥ እስከምናመጣ እንታገል፡፡ በዚህ ረገድ የትግራይ ዲያስፖራ የሰራውን ተአምራዊ ስራ ማስታወስ ይገባል፡፡
5/ ማህበራዊ ሚዲያውን (በተለይም ትዊተር ወዘተ) በድንብ በመጠቀም የፋሽስቱን ቡድን ገፅታ እርቃኑን እናስቀረው፡፡ ሁልጊዜም የተቀናጀ ዘመቻ እናካሂድ፡፡ ይህን ዘመቻ በተለይ ጋዜጠኞች በደንብ ሊመሩት ይችላሉ፡፡ ይገባልም፡፡
እነዚህንና ሌሎችንም የተቀናጁ ስትራቴጂዎች ተመጋጋቢ በሆነ መንገድ በመተግበር አገዛዙን እርቃኑን ማስቀረትና ባለድል መሆን ይገባናል፡፡ ይህን ጦርነት ማሸነፍ ምርጫ ሳይሆን ግዴታ ነው!
ጊዜው የስራ ነው!
የአማራ ብሄርተኝነት ይለምልም!!!