የኢትዮጵያ “ፈታኝ” የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ “አስደናቂ ውጤቶች” ይዞ የሚመጣ ነው ሲሉ የአይኤምኤፍ ኃላፊ ተናገሩ!
የአለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) ዋና ዳይሬክተር ክሪስታሊና ጆርጂዬቫ፣ ኢትዮጵያ እያካሄደች ያለችውን የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ በተግዳሮቶች የተሞላ መሆኑን አስታውቀው፣ የኢኮኖሚ ማሻያው “ፈታኝ” ሲሉ በመግለጽ “ጊዜ የሚወስድ” መሆኑንም ጠቁመዋል።
የአለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም ዋና ዳይሬክተር ክሪስታሊና ጆርጂዬቫ በኢትዮጵያ ለሁለት ቀናት ጉብኝት አካሂደዋል፤ በጉብኝታቸውም ጠ/ሚኒስትር አብይ አህመድን (ዶ/ር) ጨምሮ ከተለያዩ የሀገሪቱ ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር መክረዋል።
የማሻሻያ እርምጃዎቹ መካከል “አንዳንዶች ቀድሞውኑ ግልጽ እየሆኑ ነው” ያሉት ዳይሬክተሯ “ህብረተሰቡም በኢኮኖሚ ማሻሻያው ላይ አንድ በመሆን ሊደግፍ ይገባል” ሲሉ አሳስበዋል።
ባለፈው አመት 2024 ኢትዮጵያ ያስመዘገበችው የ8 ነጥብ አንድ በመቶ የኢኮኖሚ እድገት ተቋማቸው ተንብዮት ከነበረው የስድስት ነጥብ አንድ በመቶ እድገት ብልጫ ያለው መሆኑን በመጥቀስ "ኢትዮጵያ የምትኮራበት ብዙ ነገር አለ" ሲሉ አስታውቀዋል።
የኢኮኖሚ መርሃ ግብሩ ኢትዮጵያ ለቀጣይ የኢኮኖሚ እድገትና መረጋጋት ያላትን ቁርጠኝነት በማሳየት ለሌሎች የአህጉሪቱ ሀገራት ተምሳሌት እንድትሆን ያደርጋታል ብለዋል።
በተለይም የፊስካል ፖሊሲዉን በማሳደግ፣ የኢኮኖሚዉን መዋቅራዊ ችግሮችን በመፍታት እና ኢንቨስትመንትን በማበረታታት የዜጎችን የኑሮ ደረጃን የሚያሻሻሽል መሆኑን ተናግረዋል።
https://t.me/voa_amharic1
https://t.me/voa_amharic1
የአለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) ዋና ዳይሬክተር ክሪስታሊና ጆርጂዬቫ፣ ኢትዮጵያ እያካሄደች ያለችውን የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ በተግዳሮቶች የተሞላ መሆኑን አስታውቀው፣ የኢኮኖሚ ማሻያው “ፈታኝ” ሲሉ በመግለጽ “ጊዜ የሚወስድ” መሆኑንም ጠቁመዋል።
የአለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም ዋና ዳይሬክተር ክሪስታሊና ጆርጂዬቫ በኢትዮጵያ ለሁለት ቀናት ጉብኝት አካሂደዋል፤ በጉብኝታቸውም ጠ/ሚኒስትር አብይ አህመድን (ዶ/ር) ጨምሮ ከተለያዩ የሀገሪቱ ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር መክረዋል።
የማሻሻያ እርምጃዎቹ መካከል “አንዳንዶች ቀድሞውኑ ግልጽ እየሆኑ ነው” ያሉት ዳይሬክተሯ “ህብረተሰቡም በኢኮኖሚ ማሻሻያው ላይ አንድ በመሆን ሊደግፍ ይገባል” ሲሉ አሳስበዋል።
ባለፈው አመት 2024 ኢትዮጵያ ያስመዘገበችው የ8 ነጥብ አንድ በመቶ የኢኮኖሚ እድገት ተቋማቸው ተንብዮት ከነበረው የስድስት ነጥብ አንድ በመቶ እድገት ብልጫ ያለው መሆኑን በመጥቀስ "ኢትዮጵያ የምትኮራበት ብዙ ነገር አለ" ሲሉ አስታውቀዋል።
የኢኮኖሚ መርሃ ግብሩ ኢትዮጵያ ለቀጣይ የኢኮኖሚ እድገትና መረጋጋት ያላትን ቁርጠኝነት በማሳየት ለሌሎች የአህጉሪቱ ሀገራት ተምሳሌት እንድትሆን ያደርጋታል ብለዋል።
በተለይም የፊስካል ፖሊሲዉን በማሳደግ፣ የኢኮኖሚዉን መዋቅራዊ ችግሮችን በመፍታት እና ኢንቨስትመንትን በማበረታታት የዜጎችን የኑሮ ደረጃን የሚያሻሻሽል መሆኑን ተናግረዋል።
https://t.me/voa_amharic1
https://t.me/voa_amharic1