ኢትዮጵያ ያለባትን ዕዳ የምትከፍልበትን መንገድ ለማመቻቸት ከአበዳሪዎች ጋር የምታደርገው ድርድር «የመጨረሻ ደረጃ» ላይ መድረሱን የገንዘብ ሚንስትሩ አህመድ ሺዴ ተናገሩ።
አህመድ ሺዴ ይህን ያሉት ከዓለም የገንዘብ ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ክሪስቲና ጆርጂዬቫ ጋር አዲስ አበባ ውስጥ ከተነጋገሩ በኋላ ትናንት እሁድ በሰጡት መግለጫ ነው።ኢትዮጵያ በኤኮኖሚ የበለጸጉ ሃገራት ጥምረት በቡድን 20 አነሳሽነት ዕዳዋ መልሶ እንዲዋቀር ለረዥም ጊዜ ብርቱ ጥረት ስታደርግ መቆየቷን ሮይተርስ ዘግቧል።
ጥረቱ ዉጤት ሳያስገኝ አዝጋሚ ሆኖ መቀጠሉን የጠቀሰው ዘገባው በጎርጎርሳዊው 2023 ከአበዳሪ ሃገራት በቦንድ ሽያጭ የተበደረችውን (ዩሮ ቦንድ) እና መክፈል የሚጠበቅባትን ወለድ መክፈል ባለመቻሏ የውጭ ዕዳ ወለድ መክፈል ከተሳናቸው ሦስት የአፍሪቃ ሃገራት አንዷ ተብላ ተሰይማለች።ሚንስትሩ አህመድ ሺዴ በጋራ የጋዜጣዊ መግለጫ ወቅት እንዳሉት ``ዕዳውን መልሶ ለማዋቀር የሚደረገው ድርድር የመጨረሻ ደረጃ ላይ ደርሷል።``
ኢትዮጵያ ባለፈው የሰኔ ወር መጨረሻ ያለባት የውጭ ዕዳ 28.9 ቢሊዮን ዶላር ደርሷል። ከዚህ ውስጥ ግማሽ ያህሉ አይ ኤም ኤፍ፣ የዓለም ባንክ እና የአፍሪካ ልማት ባንክ ያሉ የባለ ብዙ ወገን አበዳሪዎች ዕዳ መሆኑን ዘገባው አመልክቷል።የዓለም የገንዘብ ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ክርሲቲና ጆርጂዮቫ በዚሁ ጊዜ እንዳሉት የኢትዮጵያን ዕዳ መልሶ ማዋቀር ጉዳይ በቀዳሚነት ከያዟቸው ጉዳዮቻቸው አንዱ መሆኑን አንስተዋል።ኢትዮጵያ ባለፈው የሀምሌ ወር ከዓለም የገንዘብ ድርጅት ጋር የ3.4 ቢሊዮን ዶላር አዲስ የመዋዕለ ነዋይ መርኃ ግብር ስምምነት ደርሳለች።
https://t.me/voa_amharic1
https://t.me/voa_amharic1
አህመድ ሺዴ ይህን ያሉት ከዓለም የገንዘብ ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ክሪስቲና ጆርጂዬቫ ጋር አዲስ አበባ ውስጥ ከተነጋገሩ በኋላ ትናንት እሁድ በሰጡት መግለጫ ነው።ኢትዮጵያ በኤኮኖሚ የበለጸጉ ሃገራት ጥምረት በቡድን 20 አነሳሽነት ዕዳዋ መልሶ እንዲዋቀር ለረዥም ጊዜ ብርቱ ጥረት ስታደርግ መቆየቷን ሮይተርስ ዘግቧል።
ጥረቱ ዉጤት ሳያስገኝ አዝጋሚ ሆኖ መቀጠሉን የጠቀሰው ዘገባው በጎርጎርሳዊው 2023 ከአበዳሪ ሃገራት በቦንድ ሽያጭ የተበደረችውን (ዩሮ ቦንድ) እና መክፈል የሚጠበቅባትን ወለድ መክፈል ባለመቻሏ የውጭ ዕዳ ወለድ መክፈል ከተሳናቸው ሦስት የአፍሪቃ ሃገራት አንዷ ተብላ ተሰይማለች።ሚንስትሩ አህመድ ሺዴ በጋራ የጋዜጣዊ መግለጫ ወቅት እንዳሉት ``ዕዳውን መልሶ ለማዋቀር የሚደረገው ድርድር የመጨረሻ ደረጃ ላይ ደርሷል።``
ኢትዮጵያ ባለፈው የሰኔ ወር መጨረሻ ያለባት የውጭ ዕዳ 28.9 ቢሊዮን ዶላር ደርሷል። ከዚህ ውስጥ ግማሽ ያህሉ አይ ኤም ኤፍ፣ የዓለም ባንክ እና የአፍሪካ ልማት ባንክ ያሉ የባለ ብዙ ወገን አበዳሪዎች ዕዳ መሆኑን ዘገባው አመልክቷል።የዓለም የገንዘብ ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ክርሲቲና ጆርጂዮቫ በዚሁ ጊዜ እንዳሉት የኢትዮጵያን ዕዳ መልሶ ማዋቀር ጉዳይ በቀዳሚነት ከያዟቸው ጉዳዮቻቸው አንዱ መሆኑን አንስተዋል።ኢትዮጵያ ባለፈው የሀምሌ ወር ከዓለም የገንዘብ ድርጅት ጋር የ3.4 ቢሊዮን ዶላር አዲስ የመዋዕለ ነዋይ መርኃ ግብር ስምምነት ደርሳለች።
https://t.me/voa_amharic1
https://t.me/voa_amharic1