"ወደ ሀገሬ እንዳልገባ ተከልክያለሁ" ያሉት አቶ ልደቱ አያሌው በሌላ ሀገር አየር መንገድ አማካኝነት ወደ #ኢትዮጵያ እንደሚጓዙ ገለጹ!
በ #አሜሪካ የነበሩት ፖለቲከኛው አቶ ልደቱ አያሌው "ወደ ሀገሬ እንዳልገባ ተከልክያለሁ" ሲሉ ወደ ኢትዮጵያ መጓዝ እንዳልቻሉ ተናግረዋል።ነገር ግን ይህ በኢትዮጵያ አየር መንገድ ሊያደርጉት የነበረው ጉዞ በኢትዮጵያ ኤምባሲ በኩል እንደጣለባቸው የተገለጸላቸው የጉዞ ዕገዳ ቢኖርም፣ በሌላ ሀገር አየር መንገድ አማካኝነት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚጓዙ ለቢቢሲ ገልጸዋል።
ወደ ኢትዮጵያ ለመጓዝ ለየካቲት 3/2017 ዓ.ም. የአውሮፕላን ቲኬት ቆርጠው በአትላንታ አየር ማረፊያ ቢገኙም መሳፈር እንዳልቻሉ አስታውቀዋል።"ቲኬቱ የተረጋገጠ ነው።ፖስፖርቴም ለሚቀጥሉት 11 ወራት የሚያገለግል ነው" ሲሉ ለቢቢሲ የተናገሩት አቶ ልደቱ፤ ነገር ግን አየር ማረፊያ ሲደርሱ "በአሜሪካ የኢትዮጵያን ኤምባሲን" አነጋግረው ልዩ ፈቃድ ካላገኙ መጓዝ እንደማይችሉ እንደተናገራቸው ገልፀዋል።
አክለው ከሥራ አስኪያጁ [የአየር መንገድ] የተሰጣቸው ምላሽ "እገዳ ስተለጣለብህ እኛ ምንም ማድረግ አንችልም" የሚል እንደሆነ ጠቁመው "አሜሪካ ለሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ አመልክተህ በእነሱ በኩል እገዳው ካልተነሳልህ መብረር አትችልም" መባላቸውን አስታውቀዋል።"በሌላ አየር መንገድ ቲኬት ለመቁረጥ እየተዘጋጀሁ ነው። አዲስ አበባ ስደርስ ደግሞ የሚሆነው አያለሁ።ወደ ሀገር እንዳልገባ ለመከልከል የሚያስችል ምንም ዓይነት ሕግ የለም" ብለዋል።
https://t.me/voa_amharic1
https://t.me/voa_amharic1
በ #አሜሪካ የነበሩት ፖለቲከኛው አቶ ልደቱ አያሌው "ወደ ሀገሬ እንዳልገባ ተከልክያለሁ" ሲሉ ወደ ኢትዮጵያ መጓዝ እንዳልቻሉ ተናግረዋል።ነገር ግን ይህ በኢትዮጵያ አየር መንገድ ሊያደርጉት የነበረው ጉዞ በኢትዮጵያ ኤምባሲ በኩል እንደጣለባቸው የተገለጸላቸው የጉዞ ዕገዳ ቢኖርም፣ በሌላ ሀገር አየር መንገድ አማካኝነት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚጓዙ ለቢቢሲ ገልጸዋል።
ወደ ኢትዮጵያ ለመጓዝ ለየካቲት 3/2017 ዓ.ም. የአውሮፕላን ቲኬት ቆርጠው በአትላንታ አየር ማረፊያ ቢገኙም መሳፈር እንዳልቻሉ አስታውቀዋል።"ቲኬቱ የተረጋገጠ ነው።ፖስፖርቴም ለሚቀጥሉት 11 ወራት የሚያገለግል ነው" ሲሉ ለቢቢሲ የተናገሩት አቶ ልደቱ፤ ነገር ግን አየር ማረፊያ ሲደርሱ "በአሜሪካ የኢትዮጵያን ኤምባሲን" አነጋግረው ልዩ ፈቃድ ካላገኙ መጓዝ እንደማይችሉ እንደተናገራቸው ገልፀዋል።
አክለው ከሥራ አስኪያጁ [የአየር መንገድ] የተሰጣቸው ምላሽ "እገዳ ስተለጣለብህ እኛ ምንም ማድረግ አንችልም" የሚል እንደሆነ ጠቁመው "አሜሪካ ለሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ አመልክተህ በእነሱ በኩል እገዳው ካልተነሳልህ መብረር አትችልም" መባላቸውን አስታውቀዋል።"በሌላ አየር መንገድ ቲኬት ለመቁረጥ እየተዘጋጀሁ ነው። አዲስ አበባ ስደርስ ደግሞ የሚሆነው አያለሁ።ወደ ሀገር እንዳልገባ ለመከልከል የሚያስችል ምንም ዓይነት ሕግ የለም" ብለዋል።
https://t.me/voa_amharic1
https://t.me/voa_amharic1