ዩክሬን የሆነ ቀን የሩሲያ ልትሆን ትችላለች - ትራምፕ
የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ “የሆነ ቀን ዩክሬን የሩሲያ ልትሆን ትችላለች” ሲሉ ተናግረዋል።
ፕሬዚዳንቱ ከሩሲያ ዩክሬን ጦርነት ጋር በተያያዘ በሰጡት ቃለ መጠይቅ ዋሺንግተን ተኩስ አቁም እንዲደረስ ፍላጎት እንዳላት ገልጸዋል።
በሰጡት አስተያየትም “ሀገራቱ ሥምምነት ላይ ሊደርሱም ላይደርሱም ይችላሉ፤ ዩክሬንም የሆነ ቀን የሩሲያ ልትሆነም ላትሆንም ትችላለች” ብለዋል።
ከተኩስ አቁሙ ጋር በተያያዘ በሩሲያ በኩል ዝግጁነት እንደሌለ ከፎክስ ጋር በነበራቸው ቆይታ ተናግረዋል።
ዩክሬንም ከሥምምነቱ ጋር በተያያዘ ከአሜሪካ ጋር በቅርበት የመስራት ፍላጎት እንዳላት በተደጋጋሚ ስትገልጽ ቆይታለች።
ትራምፕም አሜሪካ ለዩክሬን ለምትሰጠው ድጋፍ በማዕድን መልክ ካሳ እንደምትፈልግ አስገንዝበዋል።
https://t.me/voa_amharic1
https://t.me/voa_amharic1
የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ “የሆነ ቀን ዩክሬን የሩሲያ ልትሆን ትችላለች” ሲሉ ተናግረዋል።
ፕሬዚዳንቱ ከሩሲያ ዩክሬን ጦርነት ጋር በተያያዘ በሰጡት ቃለ መጠይቅ ዋሺንግተን ተኩስ አቁም እንዲደረስ ፍላጎት እንዳላት ገልጸዋል።
በሰጡት አስተያየትም “ሀገራቱ ሥምምነት ላይ ሊደርሱም ላይደርሱም ይችላሉ፤ ዩክሬንም የሆነ ቀን የሩሲያ ልትሆነም ላትሆንም ትችላለች” ብለዋል።
ከተኩስ አቁሙ ጋር በተያያዘ በሩሲያ በኩል ዝግጁነት እንደሌለ ከፎክስ ጋር በነበራቸው ቆይታ ተናግረዋል።
ዩክሬንም ከሥምምነቱ ጋር በተያያዘ ከአሜሪካ ጋር በቅርበት የመስራት ፍላጎት እንዳላት በተደጋጋሚ ስትገልጽ ቆይታለች።
ትራምፕም አሜሪካ ለዩክሬን ለምትሰጠው ድጋፍ በማዕድን መልክ ካሳ እንደምትፈልግ አስገንዝበዋል።
https://t.me/voa_amharic1
https://t.me/voa_amharic1