ከአዲስ አበባ ወደ ዋሽንግተን ዲሲ የሚመበር የኢትዮጵያ አየር መንገድ ላይ ከባለቤቴ ጋር የተመደበልልን ቦታ ቀደም ብለን ይዘናል፡፡
ግዙፉ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለቀጣይ አሰራ ሁለት ሰዓታት ለሚያደርገው ጉዞ ዝግጅቱን አጧጡፎታል፡፡
እኔና ባለቤቴ መቀመጫችንን የሚጋራውን ሶስተኛውን ሰው ስንጠብቅ አንዲት በአምሳዎቹ መጨረሻ ላይ የሚገኙ ሰው ከተፍ አሉ፡፡ በእጃቸው ከዘራ በሌላኛው እጃቸው የሚጎተት ሻንጣ ይዘዋል፡፡
ሻንጣቸውን ከላይ የሚገኘው ማስቀመጫ ላይ እንዳኖርላቸው ለጠየቁኝ እርዳታ ፈጠን ብዬ ተቀብዬ ሰቀልኩኝ፡፡
ምስጋናዬን ተቀብዬ ከመቀመጤ መዳረሻችን ስንደርስ ካወረድክላቸው በኃላ ላግዞት፣ ልግፍ አንዳትል አለች፡፡
ደግሞ ምን ችግር አለው፡፡ የሀገሬ ሰው ባግዝ፡፡ አንድ ሁለት ተባባልን፡፡
ቀጥላ ይህንን የአንዲት ተሳፋሪ ታሪክ አጫወተችኝ፡፡
አንድ መዳረሻውን ዱባይ ያደረገ አውሮፕላን ውስጥ ከእኔ ቀጥሎ አንዲት ተለቅ ያለች ሴት ትመጠጣና የያዘቸውን የእጅ ቦርሳ ከላይ ባለው የእቃ ማስቀመጫ ላይ እንዳኖርላት ትጠይቀኛለች፡፡ ነገር ግን ከእኔ ትይዩ ተቀምጦ የነበረው ሰው ቀልጠፍ ብሎ ተቀብሎ የተጠየኩትን ድጋፍ አደረገ፡፡
ሴትዩዋ ከጎኔ መቀመጫዋን ካመቻቸችና መታጠቂያ ቀበቶዋን ካሰረች በኃላ አክብሮት የተሞላ ወሬ ጀመረችኝ፡፡ በረራችን አንደተጀመረ ብዙም ሳንጓዝ ሆዷን ቁርጠት እንዳጣደፋት ነገረችኝ፡፡ የበረራ አስተናጋጅ ጠርቼ አባካችሁን እርዷት አልኩኝ፡፡ እነሱም መጥተው ድጋፍ አደረጉ፡፡ ከዚያች ቅፅበት ጀምሮ ሴትዩዋ ልጄ እያለች እኔን መጥራት ጀመረች፡፡ ያው ላደረጉት ነገር ይሆናል ብዬ ተቀበልኩ፡፡ ሁሉም ሰው አብረን እንደሆንን ማሰብ ጀመረ፡፡
ልክ ዱባይ ስንደርስ መጀመሪያ ሻንጣውን በማስቀመጥ የረዳት ሰው ሻንጣውን ካወረደላት በኃላ ወደእኔ ጠጋ ብሎ በፍጥነት ከሴትዮዋ እንድርቅና ለበረራ አስተናጋጆቹ አብረን እንዳልሆንን እንዳሳውቃቸው ነገረኝ፡፡
ማስጠንቀቂያው ዋጋ አልነበረውም፡፡
የበረራ አስተናጋጆቹ ከሴትዮዋ ጋር ያለንን ግንኙነት ጠየቁኝ፡፡ እዚሁ አውሮፕላን ላይ መገናኘታችንን ተናገርኩ፡፡ ሴትዮዋ የእጅ ቦርሳዋን እንዳግዛት ለመነችኝ፡፡ ትንሽ ተወዛገብኩ፡፡ ያ ሰው በምልክት እንዳላግዛት አልፎም የበረራ አስተናጋጆቹ አገዛ መጠየቅ እንደሚቻል በቃል ተናገረኝ፡፡
ስሜቱ ቀላል አልነበረም ድንገት የታመመ ሰው አግዙኝ ሲል ጥሎ መሄድ ግን የሰውየውን ምክር ተቀብዬ ዊልቼር እንድትጠብቅ አድርጌ ትቻት መራመዴን ቀጠልኩ፡፡ በደቂቃዎች ውስጥ ከባድ ረብሻ ተፈጠረ፡፡ ከመጣላት ዊልቸሩ ላይ ቦርሳዋን ይዛ ለመራመድ ስትሞክር የኤርፖርት ፖሊስ በቁጥጥር ስር አዋላት፡፡
ከመቅፅበት ልጄ ልጄ እያለች ወደእኔ መጣራት ጀመረች፡፡ ጥያት እየሄድኩ እንደሆነ ወነጀለችኝ፡፡
ለካንስ ሴትዮዋ ከህገወጥ አደንዛዥ እፅ ዝውውር በተያያዘ ተይዛ ነው፡፡
እኔም ተያዝኩ፡፡ የሆነውን አስረዳው፡፡ ፖሊስ ሙሉ ስሜን እንድትናገር ጠየቃት፡፡ መጥራት አልቻለችም፡፡ ቦርሳዬ ተበረበረ፡፡ አሻራዬ ተመሳከረ፡፡ ምንም አይነት ትስስሮች ማግኘት ስላልተቻለ በመጨረሻ ነፃ ወጣው፡፡
ይህ ገጠመኝ በህይወቴ ትልቁን ትምህርት አስተማረኝ፡፡ በጉዞ ላይ ምንም አንኳ ሰውን መርዳት ጥሩ ቢሆንም ቅሉ የራስ ሻንጣ የራስ ነው፡፡ የሰው ሻንጣ ደግሞ የሰው፡፡
ታሪኩን ሰምቼ ስጨርስ ከጎኔ የተቀመጡትን ሴትዬዋን ተመለከትኩ፡፡
ከአስራ ሁለት ሰዓት በረራ በኃላ ስንደርስ አንደመጀመሪያው ሳይሆን በግማሽ ልቤ የሰቀልኩትን ቦርሳ አውርጄ ሰጠውኝ፡፡
አመሰገኑኝ፡፡
የገረመኝ መዳረሻችን የሆነው Washington Dulles International Airport የተቀበለን ባለማቋረጥ የሚነገረው የሰው ሻንጣ እንዳትይዙ፣ እንዳትረዱ . . . የሚለው ማስጠንቀቂያ ነበር፡፡
መልካም ሁኑ ግን ህይወታችሁ መልካምነታችሁን ብቻ ዋጋ ሊያስከፍለው ይችላልና መጠንቀቁ አይከፋም፡፡
ደግ አይለፍችሁ❤️
@wegoch
@wegoch
@paappii
By Tesfaye Haile
ግዙፉ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለቀጣይ አሰራ ሁለት ሰዓታት ለሚያደርገው ጉዞ ዝግጅቱን አጧጡፎታል፡፡
እኔና ባለቤቴ መቀመጫችንን የሚጋራውን ሶስተኛውን ሰው ስንጠብቅ አንዲት በአምሳዎቹ መጨረሻ ላይ የሚገኙ ሰው ከተፍ አሉ፡፡ በእጃቸው ከዘራ በሌላኛው እጃቸው የሚጎተት ሻንጣ ይዘዋል፡፡
ሻንጣቸውን ከላይ የሚገኘው ማስቀመጫ ላይ እንዳኖርላቸው ለጠየቁኝ እርዳታ ፈጠን ብዬ ተቀብዬ ሰቀልኩኝ፡፡
ምስጋናዬን ተቀብዬ ከመቀመጤ መዳረሻችን ስንደርስ ካወረድክላቸው በኃላ ላግዞት፣ ልግፍ አንዳትል አለች፡፡
ደግሞ ምን ችግር አለው፡፡ የሀገሬ ሰው ባግዝ፡፡ አንድ ሁለት ተባባልን፡፡
ቀጥላ ይህንን የአንዲት ተሳፋሪ ታሪክ አጫወተችኝ፡፡
አንድ መዳረሻውን ዱባይ ያደረገ አውሮፕላን ውስጥ ከእኔ ቀጥሎ አንዲት ተለቅ ያለች ሴት ትመጠጣና የያዘቸውን የእጅ ቦርሳ ከላይ ባለው የእቃ ማስቀመጫ ላይ እንዳኖርላት ትጠይቀኛለች፡፡ ነገር ግን ከእኔ ትይዩ ተቀምጦ የነበረው ሰው ቀልጠፍ ብሎ ተቀብሎ የተጠየኩትን ድጋፍ አደረገ፡፡
ሴትዩዋ ከጎኔ መቀመጫዋን ካመቻቸችና መታጠቂያ ቀበቶዋን ካሰረች በኃላ አክብሮት የተሞላ ወሬ ጀመረችኝ፡፡ በረራችን አንደተጀመረ ብዙም ሳንጓዝ ሆዷን ቁርጠት እንዳጣደፋት ነገረችኝ፡፡ የበረራ አስተናጋጅ ጠርቼ አባካችሁን እርዷት አልኩኝ፡፡ እነሱም መጥተው ድጋፍ አደረጉ፡፡ ከዚያች ቅፅበት ጀምሮ ሴትዩዋ ልጄ እያለች እኔን መጥራት ጀመረች፡፡ ያው ላደረጉት ነገር ይሆናል ብዬ ተቀበልኩ፡፡ ሁሉም ሰው አብረን እንደሆንን ማሰብ ጀመረ፡፡
ልክ ዱባይ ስንደርስ መጀመሪያ ሻንጣውን በማስቀመጥ የረዳት ሰው ሻንጣውን ካወረደላት በኃላ ወደእኔ ጠጋ ብሎ በፍጥነት ከሴትዮዋ እንድርቅና ለበረራ አስተናጋጆቹ አብረን እንዳልሆንን እንዳሳውቃቸው ነገረኝ፡፡
ማስጠንቀቂያው ዋጋ አልነበረውም፡፡
የበረራ አስተናጋጆቹ ከሴትዮዋ ጋር ያለንን ግንኙነት ጠየቁኝ፡፡ እዚሁ አውሮፕላን ላይ መገናኘታችንን ተናገርኩ፡፡ ሴትዮዋ የእጅ ቦርሳዋን እንዳግዛት ለመነችኝ፡፡ ትንሽ ተወዛገብኩ፡፡ ያ ሰው በምልክት እንዳላግዛት አልፎም የበረራ አስተናጋጆቹ አገዛ መጠየቅ እንደሚቻል በቃል ተናገረኝ፡፡
ስሜቱ ቀላል አልነበረም ድንገት የታመመ ሰው አግዙኝ ሲል ጥሎ መሄድ ግን የሰውየውን ምክር ተቀብዬ ዊልቼር እንድትጠብቅ አድርጌ ትቻት መራመዴን ቀጠልኩ፡፡ በደቂቃዎች ውስጥ ከባድ ረብሻ ተፈጠረ፡፡ ከመጣላት ዊልቸሩ ላይ ቦርሳዋን ይዛ ለመራመድ ስትሞክር የኤርፖርት ፖሊስ በቁጥጥር ስር አዋላት፡፡
ከመቅፅበት ልጄ ልጄ እያለች ወደእኔ መጣራት ጀመረች፡፡ ጥያት እየሄድኩ እንደሆነ ወነጀለችኝ፡፡
ለካንስ ሴትዮዋ ከህገወጥ አደንዛዥ እፅ ዝውውር በተያያዘ ተይዛ ነው፡፡
እኔም ተያዝኩ፡፡ የሆነውን አስረዳው፡፡ ፖሊስ ሙሉ ስሜን እንድትናገር ጠየቃት፡፡ መጥራት አልቻለችም፡፡ ቦርሳዬ ተበረበረ፡፡ አሻራዬ ተመሳከረ፡፡ ምንም አይነት ትስስሮች ማግኘት ስላልተቻለ በመጨረሻ ነፃ ወጣው፡፡
ይህ ገጠመኝ በህይወቴ ትልቁን ትምህርት አስተማረኝ፡፡ በጉዞ ላይ ምንም አንኳ ሰውን መርዳት ጥሩ ቢሆንም ቅሉ የራስ ሻንጣ የራስ ነው፡፡ የሰው ሻንጣ ደግሞ የሰው፡፡
ታሪኩን ሰምቼ ስጨርስ ከጎኔ የተቀመጡትን ሴትዬዋን ተመለከትኩ፡፡
ከአስራ ሁለት ሰዓት በረራ በኃላ ስንደርስ አንደመጀመሪያው ሳይሆን በግማሽ ልቤ የሰቀልኩትን ቦርሳ አውርጄ ሰጠውኝ፡፡
አመሰገኑኝ፡፡
የገረመኝ መዳረሻችን የሆነው Washington Dulles International Airport የተቀበለን ባለማቋረጥ የሚነገረው የሰው ሻንጣ እንዳትይዙ፣ እንዳትረዱ . . . የሚለው ማስጠንቀቂያ ነበር፡፡
መልካም ሁኑ ግን ህይወታችሁ መልካምነታችሁን ብቻ ዋጋ ሊያስከፍለው ይችላልና መጠንቀቁ አይከፋም፡፡
ደግ አይለፍችሁ❤️
@wegoch
@wegoch
@paappii
By Tesfaye Haile