የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለከተማ ትምህርት ጽህፈት ቤት በመምህራን እና በትምህርት ባለሙያዎች የተሰሩ የጥናትና ምርምር ስራዎች ጽብረቃ አካሄደ።
(ጥር 23/2017 ዓ.ም) የጽብረቃ መድረኩ "በጥናትና ምርምር የበለጸገ ትምህርት ለላቀ የተማሪዎች ውጤት" በሚል መሪ ቃል የተካሄደ ሲሆን በመርሀግብሩ በክፍለ ከተማው ከሚገኙ እንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ ርዕሳነ መምህራንን ጨምሮ ሱፐርቫይዘሮችና የወረዳ ትምህርት ጽህፈት የመምህራንና የትምህርት አመራር ልማት ቡድን መሪዎች ተሳታፊ ሆነዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የአጠቃላይ ትምህርት ጥናትና ምርምር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ዮሀንስ ተስፋዬ(ዶክተር) በመርሀ ግብሩ መክፈቻ ባስተላለፉት መልዕክት የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ትምህርት ጽህፈት ቤት በመማር ማ ስማር ሂደቱ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመቅረፍ በማሰብ በመምህራን እና በትምህርት ባለሙያዎች የሚሰሩ የጥናትና ምርምር ስራዎች ጽብረቃ የሚደረግበትን መድረክ በማዘጋጀት ስራዎቹ እውቅና እንዲያገኙ ማድረጉ የሚያስመሰግነው ተግባር መሆኑን ጠቀመው ቢሮው በትምህርት ቤትም ሆነ በክፍለ ከተማ ደረጃ የሚሰሩ የጥናትና ምርምር ስራዎች ለሚፈለገው አላማ እንዲውሉ ተገቢውን ድጋፍና ክትትል የሚያደርግ መሆኑን አመላክተዋል።
(ጥር 23/2017 ዓ.ም) የጽብረቃ መድረኩ "በጥናትና ምርምር የበለጸገ ትምህርት ለላቀ የተማሪዎች ውጤት" በሚል መሪ ቃል የተካሄደ ሲሆን በመርሀግብሩ በክፍለ ከተማው ከሚገኙ እንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ ርዕሳነ መምህራንን ጨምሮ ሱፐርቫይዘሮችና የወረዳ ትምህርት ጽህፈት የመምህራንና የትምህርት አመራር ልማት ቡድን መሪዎች ተሳታፊ ሆነዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የአጠቃላይ ትምህርት ጥናትና ምርምር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ዮሀንስ ተስፋዬ(ዶክተር) በመርሀ ግብሩ መክፈቻ ባስተላለፉት መልዕክት የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ትምህርት ጽህፈት ቤት በመማር ማ ስማር ሂደቱ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመቅረፍ በማሰብ በመምህራን እና በትምህርት ባለሙያዎች የሚሰሩ የጥናትና ምርምር ስራዎች ጽብረቃ የሚደረግበትን መድረክ በማዘጋጀት ስራዎቹ እውቅና እንዲያገኙ ማድረጉ የሚያስመሰግነው ተግባር መሆኑን ጠቀመው ቢሮው በትምህርት ቤትም ሆነ በክፍለ ከተማ ደረጃ የሚሰሩ የጥናትና ምርምር ስራዎች ለሚፈለገው አላማ እንዲውሉ ተገቢውን ድጋፍና ክትትል የሚያደርግ መሆኑን አመላክተዋል።