የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለከተማ ትምህርት ጽህፈት ቤት የስራ አስተባባሪ አቶ ተስፋዬ አቤቤ በበኩላቸው በመርሀ ግብሩ በ2017ዓ.ም በስድስት ወራት ውስጥ በትምህርት ቤትና በክፍለ ከተማ ደረጃ የተሰሩ የጥናትና ምርምር ስራዎች መቅረባቸውን ገልጸው የጥናትና ምርምር ስራዎቹ በትምህርት ሴክተሩ የሚስተዋሉ ችግሮችን መቅረፍ እንዲቻል አቅጣጫ ጠቋሚ የሆኑ የመፍትሄ ሀሳቦች የሚቀርቡባቸው በመሆኑ ጽህፈት ቤቱ ለዘርፉ የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን አስገንዝበዋል::
በጽብረቃ መርሀግብሩ በመምህራን እና በትምህርት ባለሙያዎች የተሰሩ ስምንት የጥናትና ምርምር ስራዎች መቅረባቸውን የጽህፈት ቤቱ የመምህራንና የትምህርት አመራር ልማት ቡድን መሪ አቶ ተሾመ ዘውዴ ጠቅሰው ከቀረቡት ስራዎች ውስጥ በዳኞች በሚሰጥ ነጥብ የተሻለ ሆኖ የሚመረጠው አንድ የጥናትና ምርምር ስራ ወደ ትምህርት ቢሮ እንደሚላክ አስታውቀዋል።
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacaebc
በጽብረቃ መርሀግብሩ በመምህራን እና በትምህርት ባለሙያዎች የተሰሩ ስምንት የጥናትና ምርምር ስራዎች መቅረባቸውን የጽህፈት ቤቱ የመምህራንና የትምህርት አመራር ልማት ቡድን መሪ አቶ ተሾመ ዘውዴ ጠቅሰው ከቀረቡት ስራዎች ውስጥ በዳኞች በሚሰጥ ነጥብ የተሻለ ሆኖ የሚመረጠው አንድ የጥናትና ምርምር ስራ ወደ ትምህርት ቢሮ እንደሚላክ አስታውቀዋል።
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacaebc