ዳንጎቴ ግሩፕ በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንቱን ከሲሚንቶ አልፎ ወደ ስኳር ምርት ላይ አመራ!
በቅርቡ በአፍሪካ ውስጥ ካሉት ትላልቅ የኢንዱስትሪ ፕሮጀክቶች አንዱ የሆነውን ግዙፉን የዳንጎቴ ማጣሪያ ፋብሪካን ካስጀመረ በኋላ፣ ዳንጎቴ ግሩፕ በኢትዮጵያ ያለውን የኢንቨስትመንት አይነቱን በከፍተኛ ደረጃ እያሰፋ መሆኑን አስታውቋል።
የግሪፑ ለቀመንበርና ስራ አስፈፃሚ አሊኮ ዳንጎቴ የአገሪቱ እየተሻሻለ የመጣውን የኢንቨስትመንት ምቹ ሁኔታ እና በቅርቡ ከጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ጋር ያደረጓቸውን ውጤታማ ውይይቶች ተከትሎ በአዳዲስ ፕሮጀክቶች ላይ ለመሳተፍ ማቀዱን ገልጿል።
በናይጄሪያ የ 60,000 ሄክታር ስኳር እርሻ በማልማት ያገኘውን ልምድ በመጠቀም ኩባንያው በኦሞ ኩራዝ ስኳር ኩባንያ ውስጥ ኢንቨስት እንደሚያደርግ ጠቁሟል።
ወደፊትም ዳንጎቴ ግሩፕ የአገሪቱ የተፈጥሮ ጋዝ ክምችት ልማት ላይ በመመስረት የእርሻ ምርታማነትን ለማሳደግ ያለመ የማዳበሪያ ማምረቻ ፋብሪካ በኢትዮጵያ ለመመስረት እንቅድ እንዳለው ካፒታል ሰምታለች።
Via Capital
@YeneTube @FikerAssefa
በቅርቡ በአፍሪካ ውስጥ ካሉት ትላልቅ የኢንዱስትሪ ፕሮጀክቶች አንዱ የሆነውን ግዙፉን የዳንጎቴ ማጣሪያ ፋብሪካን ካስጀመረ በኋላ፣ ዳንጎቴ ግሩፕ በኢትዮጵያ ያለውን የኢንቨስትመንት አይነቱን በከፍተኛ ደረጃ እያሰፋ መሆኑን አስታውቋል።
የግሪፑ ለቀመንበርና ስራ አስፈፃሚ አሊኮ ዳንጎቴ የአገሪቱ እየተሻሻለ የመጣውን የኢንቨስትመንት ምቹ ሁኔታ እና በቅርቡ ከጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ጋር ያደረጓቸውን ውጤታማ ውይይቶች ተከትሎ በአዳዲስ ፕሮጀክቶች ላይ ለመሳተፍ ማቀዱን ገልጿል።
በናይጄሪያ የ 60,000 ሄክታር ስኳር እርሻ በማልማት ያገኘውን ልምድ በመጠቀም ኩባንያው በኦሞ ኩራዝ ስኳር ኩባንያ ውስጥ ኢንቨስት እንደሚያደርግ ጠቁሟል።
ወደፊትም ዳንጎቴ ግሩፕ የአገሪቱ የተፈጥሮ ጋዝ ክምችት ልማት ላይ በመመስረት የእርሻ ምርታማነትን ለማሳደግ ያለመ የማዳበሪያ ማምረቻ ፋብሪካ በኢትዮጵያ ለመመስረት እንቅድ እንዳለው ካፒታል ሰምታለች።
Via Capital
@YeneTube @FikerAssefa